ሕያዋኑ ፍጡራንና የእግዚአብሔር ክብር
1በሠላሳኛው ዓመት፣1፥1 ወይም ዓመቴ በአራተኛው ወር፣ በአምስተኛው ቀን፣ በኮቦር ወንዝ አጠገብ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ፣ ሰማያት ተከፈቱ፤ እኔም የእግዚአብሔርን ራእይ አየሁ።
2ንጉሡ ዮአኪን በተማረከ በአምስተኛው ዓመት፣ በአምስተኛው ቀን፣ 3በባቢሎናውያን1፥3 ወይም በከለዳውያን ምድር በኮቦር ወንዝ አጠገብ፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ቡዝ ልጅ፣1፥3 ወይም ወደ ካህኑ ቡዝ ልጅ ወደ ሕዝቅኤል ወደ ካህኑ ወደ ሕዝቅኤል መጣ፤ በዚያ የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረች።
4እኔም አየሁ፤ ስመለከትም፣ እነሆ ዐውሎ ነፋስ ከሰሜን በኩል መጣ፤ ይኸውም በታላቅ ብርሃን የተከበበ፣ መብረቅን የሚረጭ ታላቅ ደመና ነበረ፤ የእሳቱም መኻል የጋለ ብረት ይመስል ነበር። 5በእሳቱም ውስጥ የአራት ሕያዋን ፍጡራን አምሳያ ነበረ፤ መልካቸውም የሰው ቅርጽ ይመስል ነበር። 6እያንዳንዳቸውም አራት አራት ፊትና አራት አራት ክንፍ ነበራቸው። 7እግራቸው ቀጥ ያለ ነበር፤ ኰቴያቸውም እንደ ጥጃ ኰቴ ያለ ሲሆን፣ እንደ ተወለወለ ናስም ያብለጨልጭ ነበር። 8በአራቱ ጐኖቻቸው ባሉት ክንፎቻቸው ሥር የሰው እጅ ነበራቸው። አራቱም ፊቶችና ክንፎች ነበሯቸው፤ 9ክንፎቻቸውም እርስ በርስ ይነካኩ ነበር። እያንዳንዱም ቀጥ ብሎ ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላቸውም ዞር ብለው አይመለከቱም ነበር።
10ፊታቸውም እንዲህ ነበር፤ አራቱም እያንዳንዳቸው የሰው ፊት ነበራቸው፤ በቀኝ በኩል የአንበሳ ፊት፣ በግራ በኩልም የበሬ ፊት ነበራቸው፤ እያንዳንዳቸውም ደግሞ የንስር ፊት ነበራቸው። 11እንግዲህ ፊታቸው ይህን ይመስል ነበር፤ ክንፋቸውም ወደ ላይ ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ክንፍ ነበራቸው፤ የእያንዳንዱም ክንፍ የሌላውን ክንፍ ይነካ ነበር፤ ሁለቱ ክንፎቻቸው ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ነበር። 12እያንዳንዱ ቀጥ ብሎ ወደ ፊት ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላም ሳይዞር መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄድ ነበር። 13የሕያዋን ፍጡራኑ መልክም እንደሚነድ የከሰል ፍምና የተቀጣጠለ ችቦ ይመስል ነበር፤ በፍጡራኑ መካከል እሳት ወዲያ ወዲህ ይንቀሳቀስ ነበር፤ ብርሃኑም ደማቅ ነበር፤ ከእሳቱም ውስጥ መብረቅ ይወጣ ነበር። 14ፍጡራኑም እንደ መብረቅ ብልጭታ ፍጥነት ወዲያ ወዲህ ይወረወሩ ነበር።
15ሕያዋን ፍጡራኑን ስመለከታቸው፣ አራት ፊቶች ባሉት በእያንዳንዱ ፍጡር አጠገብ አንዳንድ መንኰራኵር በምድር ላይ አየሁ። 16የመንኰራኵሮቹ መልክና አሠራር እንዲህ ነበር፤ እንደ ቢረሌ ያንጸባርቁ ነበር፤ የአራቱም ቅርጽ ተመሳሳይ ሆኖ፤ እያንዳንዱ መንኰራኵር በመንኰራኵር ውስጥ ተሰክቶ የተሠራ ይመስል ነበር። 17በሚሄዱበት ጊዜም፣ ፍጡራኑ ወደሚዞሩበት ወደ አራቱ አቅጣጫ ሁሉ መንቀሳቀስ ይችሉ ነበር፤ ፍጡራኑ በሚሄዱበትም ጊዜ መንኰራኵሮቹ ወዲያና ወዲህ1፥17 ወይም ወደ ሌላ አይሉም ነበር። 18የመንኰራኵሮቹ ክብ ጠርዝ ረዥምና አስፈሪ ነበር፤ የአራቱም መንኰራኵሮች ክብ ጠርዝ ዙሪያውን በዐይኖች የተሞላ ነበር።
19ሕያዋኑ ፍጡራን ሲንቀሳቀሱ፣ በአጠገባቸው ያሉ መንኰራኵሮችም ይንቀሳቀሱ ነበር፤ ሕያዋኑ ፍጡራን ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ መንኰራኵሮቹም አብረዋቸው ከፍ ከፍ ይሉ ነበር። 20መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄዳሉ፤ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ፤ 21ፍጡራኑ ሲንቀሳቀሱ ይንቀሳቀሳሉ፤ ፍጡራኑ ቀጥ ብለው ሲቆሙ እነርሱም ይቆማሉ፤ ፍጡራኑ ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ።
22ከሕያዋኑ ፍጡራን ራስ በላይ የሚያስፈራና፤ እንደ በረዶ የሚያንጸባርቅ ጠፈር የሚመስል ነገር ነበር። 23ከጠፈሩም በታች የአንዱ ክንፍ ወደ ሌላው ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዱም ሰውነቱን የሚሸፍንበት ሁለት ክንፍ ነበረው። 24ፍጡራኑ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የክንፎቻቸውን ድምፅ ሰማሁ፤ ድምፁም እንደሚጐርፍ ውሃ ጩኸት፣ ሁሉን እንደሚችል1፥24 በዕብራይስጡ ሻዳይ ይላል አምላክ ድምፅና እንደ ሰራዊት ውካታ ነበር። መንቀሳቀሳቸውን ሲያቆሙም ክንፎቻቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር።
25መንቀሳቀሳቸውን አቁመው ክንፎቻቸውን ዝቅ እንዳደረጉ፣ ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ድምፅ ተሰማ። 26ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ከፍ ብሎ የሰንፔር1፥26 ወይም ላፒስ ላዙሊ ዙፋን የሚመስል ነገር ነበር፤ በዙፋኑም ላይ የሰው መልክ የሚመስል ነበር። 27ወገቡ ከሚመስለው ጀምሮ ወደ ላይ በእሳት መካከል እንዳለ የጋለ ብረት፣ ከወገቡም በታች እሳት ይመስል እንደ ነበር አየሁ፤ ደማቅ ብርሃንም በዙሪያው ነበር። 28በዝናብ ቀን በደመና ውስጥ እንደሚታየው ቀስተ ደመና በዙሪያው ያለው ጸዳል እንዲሁ ነበር።
ይህም የእግዚአብሔር ክብር መልክ አምሳያ ነበረ። ባየሁትም ጊዜ በግንባሬ ተደፋሁ፤ የአንድ ተናጋሪን ድምፅ ሰማሁ።
以西结的异象
1第三十年四月五日,我正在迦巴鲁河畔被掳的人当中,忽然天开了,我看见了上帝的异象。 2那是约雅斤王被掳第五年的四月五日, 3就在迦勒底人境内的迦巴鲁河畔,耶和华的话特别传给了布西的儿子以西结祭司,耶和华的能力1:3 “能力”希伯来文是“手”。降在他身上。
4在异象中,我看见一阵狂风从北方刮来,随后有一大朵云闪耀着火光,四周环绕着灿烂的光芒,火的中心像发光的金属。 5火中有四个像人形的活物, 6每个活物有四张不同的面孔和四个翅膀。 7他们的腿是直的,脚如同牛犊的蹄,都亮如磨光的铜。 8四面的翅膀下都有人的手,四个活物都有脸和翅膀, 9翅膀彼此相连。他们移动时不必转身,各朝前面移动。 10四个活物的面孔是这样的:正面是人的脸,右面是狮子的脸,左面是牛的脸,后面是鹰的脸。 11他们的翅膀向上展开,每个活物的一对翅膀与其他活物的翅膀相连,另外一对翅膀遮蔽身体。 12耶和华的灵往哪里去,他们也往哪里去,移动时不用转身。 13四个活物的形象如燃烧的火炭,又像火把。活物之间有火上下移动,发出耀眼的闪电。 14这些活物像闪电一样往来飞驰。
15当我观看这些活物的时候,发现每个活物旁边的地上都有一个轮子。 16四个轮子的形状和结构都一样,好像轮套轮,如同闪耀的绿宝石。 17他们可以向四面移动,移动时轮子不必转向。 18轮圈高而可畏,周围布满了眼睛。 19活物行走,轮子也在旁边行走;活物上升,轮子也上升。 20灵往哪里去,活物也往哪里去,轮子也跟着往哪里去,因为活物的灵在轮子里。 21活物行走,轮子也行走;活物站立不动,轮子也站立不动;活物上升,轮子也跟着上升,因为活物的灵在轮子里。
22活物的头上好像铺展着茫茫的穹苍,如同顶着耀眼的水晶。 23穹苍下四个活物伸展翅膀,彼此相对,各用两个翅膀遮蔽身体。 24他们移动时,翅膀发出的响声如洪涛之声,既像全能者的声音,又像军队的呐喊。活物站住的时候,便将翅膀垂下。 25他们站立垂下翅膀时,有声音从他们头顶的穹苍之上传来。
26在他们头顶的穹苍之上仿佛有蓝宝石的宝座,有一位形状像人的高高坐在宝座上。 27我看到祂的腰部以上好像烧红发亮的金属,好像有火四面环绕。腰部以下如同火焰。祂周围有耀眼的光辉, 28仿佛雨天云中的彩虹。
这是耶和华荣耀的形象。我一看见,便俯伏在地,随后听见有说话的声音。