ዮሐንስ 14 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ዮሐንስ 14:1-31

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን አበረታታ

1“ልባችሁ አይጨነቅ፤ በእግዚአብሔር እመኑ14፥1 ወይም እናንተ በእግዚአብሔር ታምናላችሁ፤ በእኔም ደግሞ እመኑ። 2በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። 3ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ። 4እኔ ወደምሄድበትም ስፍራ የሚያደርሰውን መንገድ ታውቃላችሁ።”

ወደ አብ የሚያደርሰው መንገድ

5ቶማስም፣ “ጌታ ሆይ፤ ወዴት እንደምትሄድ አናውቅም፤ ታዲያ፣ መንገዱን እንዴት ማወቅ እንችላለን?” አለው።

6ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “መንገዱ እኔ ነኝ፤ እውነትና ሕይወትም እኔው ነኝ፤ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። 7እኔን ብታውቁኝ ኖሮ አባቴንም ባወቃችሁት ነበር።14፥7 አንዳንድ የጥንት ቅጆች በርግጥ እኔን ብታውቁ አባቴንም ታውቃላችሁ ይላሉ። ከአሁን ጀምሮ ግን ታውቁታላችሁ፤ አይታችሁታልም።”

8ፊልጶስም፣ “ጌታ ሆይ፤ አብን አሳየንና ይበቃናል” አለው።

9ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “አንተ ፊልጶስ! ይህን ያህል ጊዜ ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቷል፤ እንዴትስ፣ ‘አብን አሳየን’ ትላለህ? 10እኔ በአብ እንዳለሁ፣ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? የምነግራችሁ ቃል ከራሴ አይደለም፤ ነገር ግን ሥራውን የሚሠራው በእኔ የሚኖረው አብ ነው። 11እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ ስነግራችሁ እመኑኝ፤ ሌላው ቢቀር ስለ ድንቅ ሥራዎቹ እንኳ እመኑ። 12እውነት እላችኋለሁ፤ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ ይሠራል፤ እንዲያውም እኔ ወደ አብ ስለምሄድ፣ ከእነዚህም የሚበልጥ ያደርጋል። 13አብ በወልድ እንዲከብር፣ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለሁ፤ 14ማንኛውንም ነገር በስሜ ብትለምኑኝ፣ እኔ አደርገዋለሁ።

ስለ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠ ተስፋ

15“ብትወድዱኝ ትእዛዜን ትጠብቃላችሁ። 16እኔ አብን እለምናለሁ፤ እርሱም ከእናንተ ጋር ለዘላለም የሚኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ 17እርሱም የእውነት መንፈስ ነው፤ ዓለም ስለማያየውና ስለማያውቀው ሊቀበለው አይችልም። እናንተ ግን፣ አብሯችሁ ስለሚኖርና በውስጣችሁ ስለሚሆን14፥17 አንዳንድ የጥንት ቅጆች በውስጣችሁ ስላለ ይላሉ። ታውቁታላችሁ። 18ወላጅ እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። 19ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ዓለም ከቶ አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ። እኔ ሕያው ስለሆንሁ እናንተም ሕያዋን ትሆናላችሁ። 20እኔ በአባቴ እንዳለሁ፣ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ፣ እኔም ደግሞ በእናንተ እንዳለሁ በዚያ ቀን ትረዳላችሁ። 21የሚወድደኝ ትእዛዜን ተቀብሎ የሚጠብቅ ነው፤ የሚወድደኝንም አባቴ ይወድደዋል፤ እኔም እወድደዋለሁ፤ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”

22ከዚያም የአስቆሮቱ ያልሆነው ይሁዳ፣ “ጌታ ሆይ፤ ታዲያ፣ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ የምትገልጠው እንዴት ነው?” አለው።

23ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “የሚወድደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወድደዋል፤ ወደ እርሱ እንመጣለን፤ ከእርሱም ጋር እንኖራለን። 24የማይወድደኝ ቃሌን አይጠብቅም። ይህ የምትሰሙት ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።

25“አሁን ከእናንተ ጋር እያለሁ ይህን ሁሉ ነግሬአችኋለሁ፤ 26አብ በስሜ የሚልከው አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ ግን ሁሉን ነገር ያስተምራችኋል፤ እኔ የነገርኋችሁንም ሁሉ ያሳስባችኋል። 27ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጣችሁ አይደለም። ልባችሁ አይጨነቅ፤ አይፍራም።

28“ ‘እሄዳለሁ፤ ተመልሼም ወደ እናንተ እመጣለሁ’ ማለቴን ሰምታችኋል፤ ብትወድዱኝስ አብ ከእኔ ስለሚበልጥ ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር፤ 29የተናገርሁት ሲፈጸም እንድታምኑ፣ ከመሆኑ በፊት አሁን ነግሬአችኋለሁ። 30የዚህ ዓለም ገዥ ስለሚመጣ ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም። እርሱም በእኔ ላይ ሥልጣን የለውም፤ 31ነገር ግን እኔ አብን እንደምወድድ፣ አባቴ ያዘዘኝንም እንደማደርግ ዓለም እንዲያውቅ ነው።

“ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי יוחנן 14:1-31

1”אל תתנו מקום לדאגה בלבבכם; האמינו באלוהים והאמינו בי. 2בבית אבי מעונות רבים, ואני הולך להכין לכם מקום. לולא היה הדבר נכון, לא הייתי מספר לכם זאת. 3לאחר שהכול יהיה מוכן אחזור ואקח אתכם אלי, כדי שתהיו תמיד במקום שבו אני נמצא. 4אתם יודעים לאן אני הולך וכיצד להגיע לשם.“

5”לא, איננו יודעים לאן אתה הולך“, קרא תומא. ”כיצד אתה מצפה שנדע את הדרך?“

6אולם ישוע ענה: ”אני עצמי הדרך, האמת והחיים. איש אינו יכול לבוא אל האב אלא באמצעותי. 7אילו ידעתם מי אני, הייתם יודעים גם מיהו אבי. מעתה ואילך אתם מכירים אותו וגם ראיתם אותו.“

8”אדוני, הראה לנו את האב ונסתפק בכך“, ביקש פיליפוס. 9אולם ישוע השיב: ”פיליפוס, לאחר שהייתי אתכם במשך כל הזמן הזה, עדיין אינך יודע מי אני? מי שראה אותי ראה את אבי, אם כן מדוע מבקש אתה לראותו? 10האם אינך מאמין שאני חי באבי, ושאבי חי בי? אין אלה המילים שלי, כי אם של אבי השוכן בקרבי והפועל דרכי.

11”האמינו לי שאני חי באבי ואבי חי בי; האמינו לי לפחות בזכות הנסים והנפלאות שחוללתי. 12אני אומר לכם בכנות וברצינות: כל מי שמאמין בי יוכל לעשות את כל מה שאני עושה, ואף הרבה יותר מזה, כי אני הולך אל אבי. 13אעשה למענכם כל מה שתבקשו בשמי, כדי שהאב יכובד בבנו. 14אכן, אעשה את כל מה שתבקשו בשמי.

15”אם אתם אוהבים אותי, שמעו בקולי; 16ואני אבקש מאבי שיתן לכם יועץ אחר שלא יעזוב אתכם לעולם – 17את רוח הקודש והאמת. רוב האנשים בעולם אינם יכולים לקבל את רוח הקודש, מפני שאינם מכירים אותו ואינם מעונינים בו כלל. אולם אתם מכירים אותו, כי עתה הוא נמצא אתכם ובקרוב אף ישכון בקרבכם. 18לא אעזוב אתכם כיתומים; אני אחזור אליכם. 19בעוד זמן קצר העולם כבר לא יראה אותי, אך אתם תראו אותי, כי אני חי וגם אתם תחיו. 20ביום ההוא תדעו שאני שוכן באבי, אתם שוכנים בי ואני בכם. 21כל השומע בקולי אוהב אותי; על כן אבי ואני נאהב אותו, ואני אתוודע אליו.“

22יהודה תלמידו (לא איש־קריות) פנה אליו: ”אדוני, מדוע רוצה אתה להתוודע אלינו בלבד, אל תלמידיך, ולא אל העולם כולו?“

23”מפני שאגלה את עצמי רק למי שאוהב אותי ושומע בקולי“, השיב ישוע. ”גם אבי יאהב את מי שאוהב אותי, ואנחנו נשכון בתוכו. 24מי שאינו שומע בקולי אינו אוהב אותי. זכרו, אין אלה דברי, כי אם דברי אבי אשר שלחני. 25אני אומר לכם דברים אלה כל עוד אני נמצא אתכם. 26כאשר אבי ישלח בשמי את המנחם, את רוח הקודש, הוא ילמד אתכם דברים רבים ויזכיר לכם כל מה שאמרתי.

27”אני משאיר לכם שלווה ושלום. לא לפי מושגי העולם, אלא שלומי שלי. לכן אל תפחדו ואל תדאגו. 28זכרו את מה שאמרתי לכם: אני הולך עכשיו, אולם אשוב אליכם. אם אתם באמת אוהבים אותי, תשמחו לשמוע שאני חוזר אל אבי, כי הוא גדול ממני. 29אני מספר לכם את כל הדברים האלה לפני התרחשותם, כדי שתאמינו בי כאשר הם יתרחשו.

30‏-31”לא נותר לי זמן רב לדבר אליכם, כי שר הרשע של העולם הזה מתקרב. הוא אינו יכול לגבור עלי, אך על העולם לדעת שאני אוהב את אבי; משום כך אני עושה כל מה שאבי מצווה עלי. הבה נלך מכאן.“