ዘፍጥረት 4 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 4:1-26

ቃየንና አቤል

1አዳም ሚስቱን ሔዋንን ተገናኛት፤ እርሷም ፀንሳ ቃየንን4፥1 ቃየን የሚለው ስም ማምጣት ወይም ማግኘት የሚል ትርጕም ካላቸው የዕብራይስጥ ቃላት ጋር ተመሳሳይ ድምፅ አለው ወለደች፤ “በእግዚአብሔር (ያህዌ) ርዳታ ወንድ ልጅ አገኘሁ” አለች። 2ደግሞም ወንድሙን አቤልን ወለደች።

አቤል የበግ እረኛ፣ ቃየንም ዐራሽ ነበር። 3በአንድ ወቅት፣ ቃየን ከምድር ፍሬ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት አቀረበ። 4አቤልም መጀመሪያ ከተወለዱት በጎች መካከል ስባቸውን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ። እግዚአብሔር (ያህዌ) ወደ አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ፤ 5በቃየንና በመሥዋዕቱ ግን አልተደሰተም፤ ስለዚህ ቃየን ክፉኛ ተናደደ፤ ፊቱም ጠቈረ።

6እግዚአብሔር አምላክም (ያህዌ ኤሎሂም) ቃየንን እንዲህ አለው፤ “ለምን ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቈረ? 7መልካም ብታደርግ ተቀባይነትን አታገኝምን? መልካም ባታደርግ ግን፣ ኀጢአት በደጅህ እያደባች ናት፤ ልታሸንፍህ ትፈልጋለች፤ አንተ ግን ተቈጣጠራት።”

8ቃየንም ወንድሙን አቤልን፣ “እስቲ ና፤ ወደ መስኩ እንውጣ”4፥8 እስቲ ና፣ ወደ መስኩ እንውጣ የሚለው ሐረግ በኦሪተ ሳምራውያን፣ በሰብዓ ሊቃናት፣ በቩልጌትና፣ በሱርስት የሚገኝ ሲሆን በማሶሬቲክ ጽሑፍ ውስጥ ግን የለም አለው፤ በመስኩም ሳሉ፣ ቃየን ወንድሙን አቤልን አጠቃው፤ ገደለውም።

9ከዚያም፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ቃየንን፣ “ወንድምህ አቤል የት ነው?” አለው።

ቃየንም፣ “አላውቅም፤ እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝን?” ሲል መለሰ።

10እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲህ አለ፤ “ምንድን ነው ያደረግኸው? የወንድምህ ደም ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል። 11እንግዲህ የተረገምህ ነህ፤ የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀበል አፏን ከከፈተችው መሬት ትሰደዳለህ። 12ብታርሳትም ፍሬዋን አትለግስህም፤ በምድር ላይ ኰብላይና ተንከራታች ትሆናለህ።” 13ቃየንም እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዲህ አለው፤ “ቅጣቴ ልሸከመው ከምችለው በላይ ነው። 14እነሆ፤ ዛሬ ከምድሪቱ አባረርኸኝ፤ ከፊትህም እሸሸጋለሁ፤ በምድር ላይ ኰብላይና ተንከራታች እሆናለሁ፤ የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል።”

15እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን፣ “የለም! እንደርሱ አይሆንም፤4፥15 ዕብራይሰጡ ከሰብዓ ሊቃናት፣ ከቩልጌትና ከሱርስቱ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን፣ ዕብራይስጡ ግን መልካም ይለዋል። ማንም ቃየንን ቢገድል፣ ሰባት ዕጥፍ የበቀል ቅጣት ይቀበላል” አለው፤ ስለዚህ፣ ያገኘው ሁሉ እንዳይገድለው እግዚአብሔር (ያህዌ) በቃየን ላይ ምልክት አደረገለት። 16ቃየንም ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ወጥቶ ሄዶ፣ ከዔድን በስተ ምሥራቅ በምትገኝ ኖድ4፥16 ኖድ ማለት መቅበዝበዝ ማለት ነው (12 እና 14 ይመ)። በተባለች ምድር ተቀመጠ።

17ቃየን ሚስቱን ተገናኛት፤ እርሷም ፀንሳ ሄኖክን ወለደች። ቃየን የቈረቈረውን ከተማ በልጁ ስም ሄኖክ ብሎ ጠራው። 18ሄኖክ ኢራድን ወለደ፤ ኢራድም መሑያኤልን፣ መሑያኤልም ማቱሣኤልን፣ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ።

19ላሜሕ ሁለት ሚስቶች አገባ፤ የአንደኛዋ ስም ዓዳ፣ የሁለተኛዋም ጺላ ነበር። 20ዓዳ ያባልን ወለደች፤ እርሱም በድንኳን ለሚኖሩ ከብት አርቢዎች አባት ነበረ። 21ወንድሙም ዩባል ይባላል፤ እርሱም የበገና ደርዳሪዎችና የዋሽንት ነፊዎች አባት ነበረ። 22ሴላም ደግሞ ቱባልቃይን የተባለ ወንድ ልጅ ነበራት፤ እርሱም ከብረትና ከናስ ልዩ ልዩ መሣሪያዎችን እየቀረጸ የሚሠራ ነበር። የቱባልቃይን እኅት ናዕማ ትባል ነበር።

23ላሜሕ ሚስቶቹን እንዲህ አላቸው፤

“ዓዳና ጺላ ሆይ ስሙኝ፤

የላሜሕ ሚስቶች ሆይ አድምጡኝ፤

አንድ ሰው ቢያቈስለኝ፣

ጕልማሳው ቢጐዳኝ፣ ገደልሁት፤4፥23 ወይም እገድላለሁ

24ቃየንን የሚገድል ሰባት ጊዜ ቅጣት ካገኘው፣

የላሜሕ ገዳይማ ሰባ ሰባት ጊዜ ቅጣት ያገኘዋል።”

25አዳም እንደ ገና ሚስቱን ተገናኛት፤ እርሷም ወንድ ልጅ ወለደች። “ቃየን በገደለው በአቤል ፈንታ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ምትክ ሰጠኝ” ስትል ስሙን ሴት4፥25 ሴት ማለት ሰጠ ሳይሆን አይቀርም። ብላ ጠራችው። 26ለሴትም ደግሞ ወንድ ልጅ ተወለደለት፤ ስሙንም ሄኖስ አለው።

በዚያም ዘመን ሰዎች የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ስም መጥራት4፥26 ወይም ማወጅ ጀመሩ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

创世记 4:1-26

该隐和亚伯

1亚当和他妻子夏娃同房,夏娃便怀孕,生了该隐。她说:“耶和华让我得了一个男孩。” 2后来,夏娃又生了该隐的弟弟亚伯。长大后,亚伯做了牧羊人,该隐做了农夫。

3到了收成的时候,该隐把地里的出产当祭物献给耶和华, 4亚伯也把羊群中头生的羊及其最肥美的部分献给耶和华。耶和华悦纳亚伯和他的祭物, 5却不悦纳该隐和他的祭物。该隐便非常恼火,面带怒容。 6耶和华问该隐:“你为什么恼火?为什么面带怒容? 7如果你做得对,难道不会蒙悦纳吗?如果你做得不对,罪就蹲在你的门口要控制你,但你必须制服罪。”

8该隐对弟弟亚伯说:“我们去田间吧!”4:8 我们去田间吧!”参照七十士译本,希伯来文无此句。他们在田间的时候,该隐动手打亚伯,把他杀了。

9后来,耶和华问该隐:“你弟弟亚伯在哪里?”他说:“我不知道!难道我是弟弟的看护人吗?” 10耶和华说:“你做了什么事?你弟弟的血从地里向我哭诉。 11地张开口从你手上接受了你弟弟的血,你在地上必受咒诅。 12你种地,地却不会再为你长出任何东西,你必在地上四处漂泊。” 13该隐对耶和华说:“这惩罚太重!我承受不了。 14今天你把我赶出去,使我不能再见你的面。我在地上四处漂泊,见到我的人都会杀我。” 15耶和华对他说:“不会的,因为凡杀你的,必遭受七倍的报应。”于是,耶和华在该隐身上留下一个记号,免得见到他的人杀他。 16该隐离开耶和华,来到伊甸东边的挪得住下来。

该隐的后代

17该隐和妻子同房,他的妻子就怀孕,生了以诺该隐建了一座城,用他儿子的名字给这城取名叫以诺18以诺以拿以拿米户雅利米户雅利玛土撒利玛土撒利拉麦19拉麦娶了两个妻子,一个叫亚大,另一个叫洗拉20亚大生了亚八亚八是游牧民族的祖先, 21亚八的弟弟犹八是吹奏乐器之人的鼻祖。 22洗拉生了土八·该隐,他是打造各种铜铁器具的匠人4:22 他是打造各种铜铁器具的匠人”或译“他是铜匠、铁匠的祖先”。,他的妹妹叫拿玛

23一天,拉麦对他的两个妻子说:

亚大洗拉,你们听我的声音;

拉麦的妻子啊,侧耳听我的话,

有人伤我,我杀了他,

青年打我,我宰了他。

24该隐的遭受七倍的报应,

拉麦的遭受七十七倍的报应。”

塞特和以挪士

25亚当又与妻子夏娃同房,夏娃生了一个儿子,取名叫塞特,因为她说:“上帝赐我另一个儿子来代替亚伯,因为该隐杀了他。” 26塞特生了一个儿子,给他取名叫以挪士。那时候,人才开始求告耶和华。