ዘፀአት 9 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 9:1-35

የእንስሳት ዕልቂት

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ወደ ፈርዖን ሂድና እንዲህ በለው፤ ‘የዕብራውያን አምላክ (ኤሎሂም) እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለው ይህ ነው፤ “ያመልኩኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።” 2አሁንም እንዳይሄዱ ብታደርግና ብትከለክላቸው፣ 3የእግዚአብሔር (ያህዌ) እጅ በመስክ ላይ ባሉት እንስሳት፣ በፈረሶችህና በአህዮችህ፣ በግመሎችህና በቀንድ ከብቶችህ፣ በበጎችህና በፍየሎችህ ላይ አስከፊ መቅሠፍት ያመጣብሃል። 4ነገር ግን እግዚአብሔር (ያህዌ) በእስራኤልና በግብፅ እንስሳት መካከል ልዩነት ያደርጋል፤ ይኸውም የእስራኤል የሆነ ማንኛውም እንስሳ እንዳይሞት ነው።’ ”

5እግዚአብሔር (ያህዌ) ጊዜን ወስኖ፣ እንዲህ አለ፤ “በነገው ዕለት እግዚአብሔር (ያህዌ) በምድሪቱ ላይ ይህን ያደርጋል።” 6በማግሥቱም እግዚአብሔር (ያህዌ) ነገሩን ፈጸመው፤ የግብፃውያን እንስሳት በሙሉ ዐለቁ፤ ነገር ግን የእስራኤላውያን ከሆኑት እንስሳት አንድም አልሞተም። 7ፈርዖን ያጣሩ ዘንድ ሰዎች ልኮ ከእስራኤላውያኑ እንስሳት አንድም እንኳ አለመሞቱን ተገነዘበ። ያም ሆኖ ልቡ እንደ ደነደነ ስለ ነበር፣ ሕዝቡን አልለቀቀም።

የዕባጭ መቅሠፍት

8ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን አላቸው፤ “ከምድጃው ዕፍኝ ዐመድ ወስዳችሁ፣ ሙሴ በፈርዖን ፊት ወደ ሰማይ ይበትነው። 9በግብፅ ምድር ሁሉ ትቢያ ይሆናል፤ በምድሪቱ ሁሉ በሚገኙት ሰዎችና እንስሳት ላይ መግል የያዘ ዕባጭ ይወጣል።”

10ስለዚህ ከምድጃው ዐመድ ወስደው በፈርዖን ፊት ቆሙ፤ ሙሴም ወደ ሰማይ በተነው፤ መግል የያዘ ዕባጭም በሰዎችና በእንስሳት ላይ ወጣ። 11በእነርሱና በግብፃውያን ሁሉ ላይ ዕባጭ ወጥቶ ስለ ነበር፣ አስማተኞቹ በሙሴ ፊት መቆም አልቻሉም። 12እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን የፈርዖንን ልብ አደነደነ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሙሴ እንደ ተናገረውም፣ ሙሴንና አሮንን መስማት አልፈለገም።

የበረዶ መቅሠፍት

13ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ማልደህ በጧት ተነሣ፤ ከፈርዖን ፊት ቀርበህ እንዲህ በለው፤ የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሂም) የሚለው ይህ ነው፤ ‘ያመልኩኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ፤ 14አለዚያ በአንተ በሹማምትህና በሕዝብህ ላይ የመቅሠፍቴን መዓት ሁሉ አሁን አወርድብሃለሁ፤ ይኸውም በምድር ሁሉ እንደ እኔ ያለ ማንም እንደሌለ ታውቅ ዘንድ ነው። 15አሁን እጄን ዘርግቼ አንተንና ሕዝብህን ከገጸ ምድር ሊያጠፋችሁ በሚችል መቅሠፍት በመታኋችሁ ነበር። 16ነገር ግን ኀይሌን እንዳሳይህና ስሜም በምድር ዙሪያ ሁሉ እንዲታወቅ ለዚህ አስነሥቼሃለሁ።9፥16 ወይም፣ ለዚህ ምሕረቴን አሳይቼሃለሁ 17እስካሁንም በሕዝቤ ላይ እንደ ተነሣህ ነው፤ ይሄዱም ዘንድ አትለቅቃቸውም። 18ስለዚህ ነገ በዚህ ጊዜ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በግብፅ ላይ ወርዶ የማያውቅ አስከፊ የበረዶ ማዕበል እልካለሁ። 19ከብቶችህና በመስክ ላይ ያለህ ማንኛውም ነገር ወደ መጠለያ ይገቡ ዘንድ አሁን ትእዛዝ ስጥ፤ ምክንያቱም በረዶው ወደ መጠለያ ባልገቡትና በመስክ ላይ በቀሩት በማንኛውም ሰውና እንስሳት ላይ ወርዶባቸው ስለሚሞቱ ነው።’ ”

20የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ቃል የፈሩት የፈርዖን ሹማምት፣ ባሮቻቸውንና ከብቶቻቸውን ለማስገባት ተጣደፉ። 21የእግዚአብሔርን (ያህዌ) ቃል ችላ ያሉት ግን ባሮቻቸውንና ከብቶቻቸውን በመስክ ላይ እንደ ነበሩ ተዉአቸው።

22ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ “በመላዪቱ የግብፅ ምድር ባሉት ሰዎች፣ በእንስሳት እንዲሁም በምድሪቱ ላይ በሚበቅሉት ነገሮች ሁሉ ላይ በረዶ እንዲወርድ እጅህን ወደ ሰማይ አንሣ” አለው። 23ሙሴ በትሩን ወደ ሰማይ ባነሣ ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነጐድጓድና በረዶ አወረደ፤ መብረቅም በምድሪቱ ላይ ሆነ። እግዚአብሔር (ያህዌ) በግብፅ ምድር በረዶ አዘነበ፤ 24በረዶ ወረደ፤ መብረቅም አብረቀረቀ፤ ግብፅ አገር ከሆነችበት ዘመን አንሥቶ በምድሪቱ ሁሉ እንደዚህ ያለ አስከፊ ማዕበል ሆኖ አያውቅም። 25በመላው ግብፅ በረዶ በመስክ ላይ ያለውን ሁሉ፣ ሰዎችንና እንስሳትንም መታ፤ በመስክ ላይ የበቀለውን ሁሉ አጠፋ፤ ዛፉን ሁሉ ባዶ አስቀረ። 26በረዶ ያልወረደበት ቢኖር እስራኤላውያን የሚኖሩበት የጌሤም ምድር ብቻ ነበር።

27ከዚያም ፈርዖን ሙሴንና አሮንን አስጠራ፤ እንዲህም አላቸው፤ “አሁንስ በድያለሁ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ትክክል ነው፤ እኔና ሕዝቤ ግን ስተናል። 28መብረቅና በረዶ በዝቶብናልና ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸልዩልን፤ እንድትሄዱ እለቃችኋለሁ፤ ከዚህ በኋላ በዚህ የመኖር ግዴታ የለባችሁም።”

29ሙሴም መልሶ፣ “ከከተማዋ በወጣሁ ጊዜ፣ እጆቼን ለጸሎት ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) እዘረጋለሁ፤ አንተም ምድር የእግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ሆነች ታውቅ ዘንድ መብረቁ ያቆማል፤ ከእንግዲህ በኋላ በረዶ አይኖርም። 30ሆኖም አንተና ሹማምትህ አሁንም ቢሆን እግዚአብሔር (ያህዌ) አምላክን እንደማትፈሩ ዐውቃለሁ።”

31ተልባው አብቦ፣ ገብሱም ፍሬ ይዞ ስለ ነበር፣ ተልባውና ገብሱ ከጥቅም ውጭ ሆኑ። 32ስንዴውና አጃው ግን በዚያ ወቅት ባለማፍራቱ አልጠፋም ነበር።

33ከዚያም ሙሴ ከፈርዖን ተለይቶ ከከተማው ወጣ። እጁን ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ዘረጋ፤ ነጐድጓዱና በረዶው ቆመ፤ ዝናቡም በምድሪቱ ላይ መዝነቡን አቆመ። 34ፈርዖንም ዝናቡ፣ በረዶውና ነጐድጓዱ መቆሙን ባየ ጊዜ እንደ ገና በደለ፤ እርሱና ሹማምቱ ልባቸውን አደነደኑ። 35ስለዚህ የፈርዖን ልብ ደነደነ፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሙሴ እንደ ተናገረውም እስራኤላውያን ይሄዱ ዘንድ አልለቀቃቸውም።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 9:1-35

ภัยพิบัติที่เกิดกับฝูงสัตว์

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงไปหาฟาโรห์และกล่าวกับเขาว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าของชนฮีบรูตรัสว่า “จงปล่อยประชากรของเราไปเพื่อพวกเขาจะได้นมัสการเรา” 2หากเจ้าไม่ยอมปล่อยพวกเขาไปและยังคงหน่วงเหนี่ยวไว้ 3พระหัตถ์ขององค์พระผู้เป็นเจ้าจะนำภัยพิบัติอันน่าสะพรึงกลัวมาสู่ฝูงสัตว์ของเจ้าในท้องทุ่ง ไม่ว่าจะเป็นฝูงม้า ลา อูฐ วัว แกะและแพะ 4แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทำให้เกิดความแตกต่างระหว่างฝูงสัตว์ของอิสราเอลกับของอียิปต์ เพื่อว่าสัตว์ของชาวอิสราเอลจะไม่ตายแม้แต่ตัวเดียว’ ”

5องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกำหนดเวลาและตรัสว่า “ในวันพรุ่งนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทำสิ่งนี้ในแผ่นดินอียิปต์” 6และองค์พระผู้เป็นเจ้าก็ทรงกระทำเช่นนั้นในวันต่อมา ฝูงสัตว์ของชาวอียิปต์พากันล้มตายหมด ส่วนฝูงสัตว์ของอิสราเอลไม่ตายแม้แต่ตัวเดียว 7ฟาโรห์ส่งคนไปตรวจสอบและพบว่าสัตว์ของอิสราเอลไม่ตายเลยสักตัว แต่ฟาโรห์ก็ยังคงมีพระทัยแข็งกระด้างและไม่ยอมปล่อยประชากรอิสราเอลไป

ภัยพิบัติจากฝี

8องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงตรัสกับโมเสสและอาโรนว่า “จงกอบเขม่าจากเตาขึ้นมาและให้โมเสสซัดขึ้นไปในอากาศต่อหน้าฟาโรห์ 9เขม่านั้นจะกลายเป็นฝุ่นละเอียดฟุ้งตลบไปทั่วดินแดนอียิปต์ ทำให้เกิดฝีแตกลามตามตัวผู้คนและสัตว์ทั่วแผ่นดิน”

10ดังนั้นเขาทั้งสองจึงนำเขม่าจากเตาไปเข้าเฝ้าฟาโรห์ แล้วโมเสสก็ซัดเขม่าขึ้นไปในอากาศ ทำให้เกิดเป็นฝีแตกลามทั่วตัวคนและสัตว์ 11บรรดานักเล่นอาคมไม่อาจยืนสู้หน้าโมเสสได้ เพราะฝีขึ้นที่ตัวพวกเขาเหมือนชาวอียิปต์ทั้งปวงด้วย 12แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้ฟาโรห์มีพระทัยแข็งกระด้างไม่ยอมฟังโมเสสและอาโรน ดังที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสไว้กับโมเสส

ภัยพิบัติจากลูกเห็บ

13องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงตื่นแต่เช้ามืดไปเข้าเฝ้าฟาโรห์และบอกเขาว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าของชนฮีบรูตรัสดังนี้ว่า จงปล่อยประชากรของเราไปเพื่อพวกเขาจะได้นมัสการเรา 14มิฉะนั้นครั้งนี้เราจะส่งภัยพิบัติอย่างรุนแรงมายังเจ้า ข้าราชการและราษฎรของเจ้า เพื่อเจ้าจะได้รู้ว่าทั่วพิภพนี้ไม่มีผู้ใดเสมอเหมือนเรา 15แม้ในขณะนี้เราจะเหยียดมือออกทำลายเจ้าและประชากรของเจ้าด้วยภัยพิบัติที่จะกวาดล้างเจ้าจากแผ่นดินโลกก็ได้ 16แต่เราได้ยกเจ้าให้เป็นใหญ่9:16 หรือเราได้ไว้ชีวิตเจ้าก็เพื่อจุดประสงค์ข้อนี้เอง คือเพื่อเราจะได้สำแดงฤทธิ์อำนาจของเราแก่เจ้า และเพื่อนามของเราจะเลื่องลือไปทั่วโลก 17เจ้ายังตั้งตัวเป็นศัตรูกับประชากรของเราและไม่ยอมปล่อยพวกเขาไป 18เพราะฉะนั้นในวันพรุ่งนี้เวลานี้ เราจะส่งพายุลูกเห็บมากระหน่ำอียิปต์อย่างรุนแรงที่สุด อย่างที่ไม่เคยเกิดขึ้นมาก่อนนับตั้งแต่ก่อตั้งประเทศมา 19ฉะนั้นเจ้าจงสั่งให้ต้อนฝูงสัตว์และนำทุกสิ่งที่เจ้ามีในท้องทุ่งเข้าที่กำบัง เพราะคนหรือสัตว์ใดๆ ที่ยังคงอยู่นอกชายคาจะถูกลูกเห็บซัดถึงตาย’ ”

20เหล่าข้าราชการของฟาโรห์ที่เกรงกลัวพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ารีบนำข้าทาสและฝูงสัตว์เข้ามาอยู่ใต้ชายคา 21ส่วนคนที่ไม่ใส่ใจพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าก็ปล่อยข้าทาสบริวารและฝูงสัตว์ไว้ในท้องทุ่ง

22แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงชูมือขึ้นฟ้าเพื่อจะมีลูกเห็บตกทั่วดินแดนอียิปต์ ตกลงมาบนผู้คน สัตว์ และบนพืชพันธุ์ทั้งหมดที่อยู่ในท้องทุ่งของอียิปต์” 23เมื่อโมเสสชูไม้เท้าขึ้นสู่ท้องฟ้า องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบันดาลให้เกิดฟ้าแลบฟ้าร้อง ฟ้าผ่าและพายุลูกเห็บตกลงมา ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำให้พายุลูกเห็บตกลงในดินแดนอียิปต์ 24ลูกเห็บตกลงมาและมีฟ้าแลบฟ้าร้อง พายุในคราวนี้ร้ายแรงที่สุดในอียิปต์ตั้งแต่สร้างชาติมา 25ลูกเห็บตกลงมาทั่วแผ่นดินอียิปต์ กระหน่ำใส่ทุกสิ่งทุกอย่างที่อยู่กลางแจ้งทั้งคนและสัตว์ ทำลายพืชพันธุ์ทั้งสิ้นในท้องทุ่งและต้นไม้ทุกต้นหักโค่น 26เว้นแต่ดินแดนโกเชนซึ่งชาวอิสราเอลอาศัยอยู่ ไม่มีลูกเห็บตกเลย

27แล้วฟาโรห์เรียกโมเสสกับอาโรนให้มาเข้าเฝ้าและตรัสกับเขาว่า “คราวนี้เราได้ทำบาป องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นฝ่ายถูก เราและประชาชนของเราเป็นฝ่ายผิด 28ช่วยวิงวอนองค์พระผู้เป็นเจ้าให้หยุดฟ้าคะนองและพายุลูกเห็บเถิด แล้วเราจะปล่อยพวกเจ้าไปทันที พวกเจ้าไม่ต้องอยู่อีกต่อไป”

29โมเสสทูลว่า “เมื่อข้าพระบาทออกจากเมืองไปแล้ว ข้าพระบาทจะชูมืออธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วฟ้าคะนองและลูกเห็บก็จะหยุด เพื่อฝ่าพระบาทจะได้ทรงทราบว่าโลกนี้เป็นขององค์พระผู้เป็นเจ้า 30แต่ข้าพระบาทก็ทราบว่าฝ่าพระบาทกับข้าราชการจะยังคงไม่ยำเกรงพระเจ้าพระยาห์เวห์”

31(ต้นป่านและข้าวบาร์เลย์ถูกทำลายย่อยยับ เพราะข้าวบาร์เลย์ชูรวงแล้วและต้นป่านก็กำลังออกดอก 32แต่ข้าวสาลีและข้าวสแปลต์ไม่ถูกทำลายไป เพราะสุกช้ากว่า)

33แล้วโมเสสจึงทูลลาฟาโรห์ออกไปนอกเมือง เขาชูมือขึ้นฟ้าทูลขอองค์พระผู้เป็นเจ้าพายุฟ้าคะนอง และลูกเห็บก็หยุด ฝนก็หยุดตก 34เมื่อฟาโรห์เห็นทุกอย่างสงบลงแล้ว พระองค์ก็ทำบาปอีก คือพระองค์และข้าราชการของพระองค์ทำใจแข็งกระด้าง 35เป็นอันว่าฟาโรห์มีพระทัยแข็งกระด้างไม่ยอมให้ประชากรอิสราเอลออกไป เป็นจริงตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสผ่านโมเสสไว้แล้ว