ዘፀአት 8 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 8:1-32

የጓጕንቸር መቅሠፍት

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “ወደ ፈርዖን ዘንድ ሄደህ፣ እንዲህ በለው፤ ‘እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለው ይህ ነው፤ “እኔን ያመልኩኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ። 2እነርሱን ለመልቀቅ እንቢ ብትል አገርህን ሁሉ በጓጕንቸር መቅሠፍት እመታዋለሁ። 3አባይ በጓጕንቸሮች ይሞላል፤ ወጥተውም ወደ ቤተ መንግሥትህና ወደ መኝታ ክፍልህ፣ ወደ ዐልጋህም ወደ ሹማምቶችህና ወደ ሕዝብህ ቤቶች፣ ወደ ምድጆችህና ወደ ቡሃቃዎችህ ይገባሉ። 4ጓጕንቸሮቹ ወደ አንተና ወደ ሕዝብህ ወደ ሹማምትህም ሁሉ ይመጡባችኋል።” ’ ”

5ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፣ “አሮንን፣ ‘በትርህን ይዘህ በምንጮች፣ በቦዮችና በኵሬዎች ላይ እጅህን ዘርጋ፤ ጓጕንቸሮችም በግብፅ ምድር ላይ እንዲወጡ አድርግ’ ” በለው።

6አሮንም በግብፅ ውሆች ላይ እጁን ዘረጋ፤ ጓጕንቸሮችም ወጥተው ምድሪቱን ሸፈኑ። 7ሆኖም ግን አስማተኞቹ በድብቅ ጥበባቸው ተመሳሳይ ነገር ሠሩ፤ እነርሱም በግብፅ ምድር ላይ ጓጕንቸሮች እንዲወጡ አደረጉ።

8ፈርዖንም ሙሴንና አሮንን አስጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ ጓጕንቸሮቹን ከእኔና ከሕዝቤ ያርቅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸልዩልኝ፤ ከዚያም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕትን ትሠዉ ዘንድ ሕዝቡ እንዲሄዱ እፈቅዳለሁ።

9ሙሴም ፈርዖንን፣ “በአባይ ወንዝ ካሉት በቀር ከአንተና ከቤቶችህ ጓጕንቸሮቹ እንዲወገዱ ለአንተ፣ ለሹማምትህና ለሕዝብህ የምንጸልይበትን ጊዜ እንድትወስን ለአንተ ትቸዋለሁ” አለው።

10ፈርዖንም፣ “ነገ ይሁን” አለው። ሙሴም እንዲህ ብሎ መለሰ፤ “እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ያለ ማንም እንደሌለ ታውቅ ዘንድ አንተ እንዳልኸው ይሆናል። 11ጓጕንቸሮቹም ከአንተና ከቤቶችህ፣ ከሹማምትህና ከሕዝብህ ተወግደው በአባይ ወንዝ ብቻ ይወሰናሉ።”

12ሙሴና አሮን ከፈርዖን ዘንድ ከተመለሱ በኋላ፣ በፈርዖን ላይ እግዚአብሔር (ያህዌ) ስላመጣቸው ጓጕንቸሮች ሙሴ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጮኸ። 13እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴ እንደ ለመነው አደረገ፤ ጓጕንቸሮቹም በየቤቱ ውስጥ፣ በየዐጥር ግቢውና በየሜዳው ሞቱ። 14በአንድ ላይ ሰብስበው ከመሯቸው፤ ምድሪቱም ከረፋች። 15ፈርዖን ችግሩ ጋብ ማለቱን ባየ ጊዜ ግን ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተናገረው ልቡን በማደንደን ሙሴንና አሮንን አልሰማቸውም።

የተባይ መቅሠፍት

16ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን፣ “አሮንን ‘በትርህን ሰንዝረህ የምድርን ትቢያ ምታ’ በለው፤ ከዚያም በግብፅ ምድር ያለው ትቢያ ሁሉ ተናካሽ ትንኝ ይሆናል” አለው። 17እነርሱም እንዲሁ አደረጉ፣ አሮን በትሩን እንደ ያዘ እጁን ሲዘረጋና የምድሩን ትቢያ ሲመታ፣ በግብፅ ምድር ያለው ትቢያ ሁሉ ተናካሽ ትንኝ ሆነ። ሰውንም ሆነ እንስሳውን ተናካሽ ትንኝ ወረረው። 18ነገር ግን አስማተኞቹ በድብቅ ጥበባቸው ተናካሽ ትንኞችን ለመፍጠር ሲሞክሩ አልቻሉም። ተናካሽ ትንኞቹም ከሰውና ከእንስሳው ላይ አልወረዱም ነበር። 19አስማተኞቹም ፈርዖንን፣ “ይህ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ጣት ነው” አሉት፤ ነገር ግን የፈርዖን ልብ ደንድኖ ስለ ነበር፣ ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተናገረው አልሰማቸው አለ።

የዝንብ መቅሠፍት

20ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “በጧት ተነሥተህ ፈርዖን ወደ ውሃ በሚወርድበት ጊዜ ከፊቱ ቀርበህ እንዲህ በለው፤ ‘እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለው ይህ ነው፤ ያመልኩኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ። 21ሕዝቤ እንዲሄዱ ባትለቅቃቸው፣ በአንተና በሹማምትህ ላይ፣ በሕዝብህና በቤቶችህ ላይ የዝንብ መንጋ እሰድዳለሁ። ያረፉበት መሬት እንኳ ሳይቀር፣ የግብፃውያን ቤቶች ሁሉ ዝንብ ብቻ ይሆናሉ።

22“ ‘በዚያች ዕለት ግን ሕዝቤ የሚኖርባትን የጌሤምን ምድር የተለየች አደርጋታለሁ፤ እኔ እግዚአብሔር (ያህዌ) በዚህች ምድር እንዳለሁ ታውቅ ዘንድ የዝንብ መንጋ በዚያ አይኖርም። 23በሕዝቤና በሕዝብህ መካከል ልዩነት አደርጋለሁ፤ ይህ ታምራዊ ምልክት ነገ ይሆናል8፥23 የሰብዓ ሊቃናቱና የቫልጌቱ ትርጕም እንዲሁ ሲሉ፣ ዕብራይስጡ ግን ነገ ዐርነት ይሆናል ይላል።።’ ”

24እግዚአብሔርም (ያህዌ) እንዲሁ አደረገ፤ አስጨናቂ የዝንብ መንጋ በፈርዖን ቤተ መንግሥትና በሹማምቱ ቤቶች ላይ ወረደ፤ መላው የግብፅ ምድር ከዝንቡ የተነሣ ተበላሽቶ ነበር።

25ከዚያም ፈርዖን ሙሴንና አሮንን አስጠርቶ፣ “ሂዱና በዚሁ ምድር ለአምላካችሁ ሠዉ” አላቸው።

26ሙሴ ግን እንዲህ አለ፤ “ይህ ትክክል አይሆንም፤ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የምናቀርበው መሥዋዕት በግብፃውያን ዘንድ አስጸያፊ ነው፤ ታዲያ በእነርሱ ዐይን አስጸያፊ የሆነውን መሥዋዕት ብናቀርብ አይወግሩንምን? 27ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) እርሱ እንዳዘዘን መሥዋዕት ለመሠዋት ወደ ምድረ በዳ የሦስት ቀን መንገድ መሄድ አለብን።”

28ፈርዖንም፣ “ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) በምድረ በዳ መሥዋዕት እንድትሠዉ እፈቅድላችኋለሁ፤ ነገር ግን ርቃችሁ እንዳትሄዱ። ለእኔም ጸልዩልኝ” አላቸው።

29ሙሴም እንዲህ አለ፤ “ከአንተ እንደ ተለየሁ ወዲያውኑ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) እጸልያለሁ፤ ነገም ዝንቡ ሁሉ ከፈርዖን፣ ከሹማምቱና ከሕዝቡ ይወገዳል። ብቻ ሕዝቡ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት እንዲሠዉ ባለመፍቀድ ከዚህ ቀደም ፈርዖን አታልሎ እንዳደረገው አሁንም እንዳያደርግ ርግጠኛ ይሁን።”

30ከዚያም ሙሴ ከፈርዖን ተለይቶ ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ጸለየ። 31እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴ የለመነውን አደረገ። የዝንቡም መንጋ ከፈርዖን፣ ከሹማምቱና ከሕዝቡ ተወገደ፤ አንድም ዝንብ እንኳ አልቀረም። 32በዚህም ጊዜ እንኳ ፈርዖን ልቡን አደነደነ እንጂ፣ ሕዝቡን አልለቀቀም።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 8:1-32

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “จงไปหาฟาโรห์และบอกเขาว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า จงปล่อยประชากรของเราไปเพื่อพวกเขาจะได้นมัสการเรา 2ถ้าเจ้าไม่ยอม เราจะส่งฝูงกบขึ้นมารังควานทั่วดินแดนของเจ้า 3จะมีกบเต็มแม่น้ำไนล์ มันจะกรูกันเข้าไปในวัง ในห้องนอนจนถึงบนเตียงของเจ้า และมันจะเข้าไปในบ้านของเหล่าข้าราชการของเจ้า และบนตัวประชากรของเจ้า มันจะเข้าไปในเตาปิ้งขนมและอ่างผสมแป้งของเจ้า 4ฝูงกบนั้นจะขึ้นมาที่ตัวเจ้าและข้าราชการกับราษฎรของเจ้า’ ”

5แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “เจ้าจงบอกอาโรนว่า ‘ท่านจงชูไม้เท้าขึ้นเหนือแม่น้ำ ห้วย หนอง คลอง บึง แล้วจะมีกบขึ้นทั่วแดนอียิปต์’ ”

6ดังนั้นอาโรนจึงยื่นมือออกเหนือห้วงน้ำของอียิปต์ แล้วกบก็ขึ้นมาจนเต็มแผ่นดิน 7แต่พวกนักเล่นอาคมก็ใช้ศาสตร์อันลี้ลับของตนทำให้กบขึ้นมาบนแผ่นดินอียิปต์ได้ด้วยเหมือนกัน

8ฟาโรห์รับสั่งให้โมเสสและอาโรนมาเข้าเฝ้าแล้วตรัสว่า “ช่วยวิงวอนองค์พระผู้เป็นเจ้าให้เอากบออกไปจากเราและประชากรของเรา แล้วเราจะปล่อยประชากรของเจ้าออกไปถวายเครื่องบูชาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า”

9โมเสสทูลฟาโรห์ว่า “โปรดบอกข้าพระบาทว่าฝ่าพระบาทประสงค์จะให้ข้าพระบาทอธิษฐานกำจัดกบออกจากพระราชวังของฝ่าพระบาท บ้านเรือนของข้าราชการและประชากรของฝ่าพระบาทเมื่อใด ยกเว้นกบที่ยังคงมีอยู่ในแม่น้ำไนล์”

10ฟาโรห์ตรัสว่า “วันพรุ่งนี้”

โมเสสทูลตอบว่า “จะเป็นไปตามที่ฝ่าพระบาทตรัส เพื่อฝ่าพระบาทจะได้ทราบว่าไม่มีผู้ใดเสมอเหมือนพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระบาททั้งหลาย 11ฝูงกบจะไปจากฝ่าพระบาท บ้านเรือนของพวกฝ่าพระบาท ข้าราชการและประชากรของฝ่าพระบาท แต่มันจะอยู่ในแม่น้ำไนล์เท่านั้น”

12หลังจากโมเสสกับอาโรนกลับออกมาจากการเข้าเฝ้าฟาโรห์แล้ว โมเสสร้องทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าเกี่ยวกับฝูงกบที่พระองค์ทรงนำมายังฟาโรห์ 13และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำตามคำทูลของโมเสส กบตายเกลื่อนบ้านเกลื่อนลานและทุ่งนา 14ชาวอียิปต์เอากบตายมาสุมเป็นกองพะเนิน ส่งกลิ่นเหม็นตลบทั่วดินแดน 15แต่เมื่อฟาโรห์ทรงเห็นว่าความทุกข์ร้อนบรรเทาลงแล้วก็กลับมีพระทัยแข็งกระด้างไม่ยอมรับฟังโมเสสกับอาโรนอีก เป็นไปตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้

ภัยพิบัติจากริ้น

16องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “เจ้าจงบอกอาโรนว่า ‘ท่านจงยื่นไม้เท้าออกและตีฝุ่นบนพื้นดิน’ แล้วฝุ่นทั่วดินแดนอียิปต์จะกลายเป็นริ้น” 17พวกเขาก็ทำเช่นนั้น และเมื่ออาโรนยื่นมือข้างที่ถือไม้เท้าออกแล้วตีฝุ่นบนพื้นดิน ฝุ่นทั่วดินแดนอียิปต์ก็กลายเป็นฝูงริ้นขึ้นมาตอมคนและสัตว์ 18แต่เมื่อพวกนักเล่นอาคมพยายามจะใช้ศาสตร์อันลี้ลับของตนทำเลียนแบบก็ทำไม่ได้ ริ้นตอมทั้งคนและสัตว์

19นักเล่นอาคมจึงทูลฟาโรห์ว่า “นี่เป็นผลจากนิ้วพระหัตถ์ของพระเจ้า” แต่ฟาโรห์พระทัยแข็งกระด้างไม่ยอมฟัง เป็นไปตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสไว้

ภัยพิบัติจากเหลือบ

20องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า “เจ้าจงลุกขึ้นแต่เช้ามืดไปคอยพบฟาโรห์ที่ริมฝั่งแม่น้ำและบอกเขาว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า จงปล่อยประชากรของเราไปเพื่อพวกเขาจะได้นมัสการเรา 21ถ้าเจ้าไม่ยอมปล่อยประชากรของเราไป เราจะส่งฝูงเหลือบมาตอมตัวเจ้า ตอมข้าราชการและราษฎรของเจ้า และเข้าไปในวังในบ้านของพวกเจ้า บ้านของชาวอียิปต์ และแม้แต่พื้นดินก็จะเต็มไปด้วยฝูงเหลือบ

22“ ‘แต่ในวันนั้นเราจะทำกับดินแดนโกเชนที่ประชากรของเราอาศัยอยู่ต่างออกไป ที่นั่นจะไม่มีฝูงเหลือบเลย เพื่อเจ้าจะได้รู้ว่าเราคือองค์พระผู้เป็นเจ้าสถิตอยู่เหนือแผ่นดินนี้ 23เราจะแยกให้เห็นความแตกต่าง8:23 ภาษาฮีบรูว่าเราจะนำการช่วยกู้ระหว่างประชากรของเราและประชากรของเจ้า หมายสำคัญนี้จะเกิดขึ้นในวันพรุ่งนี้’ ”

24แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำตามนั้น ฝูงเหลือบจำนวนมหาศาลกรูเข้าไปในพระราชวังของฟาโรห์และบ้านเรือนของข้าราชการ และฝูงเหลือบได้สร้างความเสียหายทั่วดินแดนอียิปต์

25แล้วฟาโรห์จึงรับสั่งให้โมเสสกับอาโรนมาเข้าเฝ้าแล้วตรัสว่า “จงไปถวายเครื่องบูชาแด่พระเจ้าของเจ้าในดินแดนนี้”

26แต่โมเสสทูลว่า “การทำเช่นนั้นไม่ถูกต้อง เครื่องบูชาที่พวกข้าพระบาทถวายแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระบาทเป็นที่รังเกียจของชาวอียิปต์ และหากพวกข้าพระบาทถวายเครื่องบูชาซึ่งเป็นที่น่ารังเกียจในสายตาของพวกเขาที่นี่ จะไม่ถูกพวกเขาเอาหินขว้างตายหรือ? 27ข้าพระบาททั้งหลายจำเป็นต้องเดินทางสามวันเข้าไปในถิ่นกันดารเพื่อถวายเครื่องบูชาแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพระบาทที่นั่นตามที่พระเจ้าทรงบัญชา”

28ฟาโรห์ตรัสว่า “เราจะให้พวกเจ้าไปถวายเครื่องบูชาแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของเจ้าในถิ่นกันดาร แต่ว่าพวกเจ้าอย่าไปไกลนัก บัดนี้จงอ้อนวอนพระเจ้าเพื่อเราด้วย”

29แล้วโมเสสทูลว่า “ทันทีที่จากไป ข้าพระบาทจะกราบทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าและในวันพรุ่งนี้ฝูงเหลือบจะไปจากฝ่าพระบาท ข้าราชการและประชากรของฝ่าพระบาท แต่ขอฝ่าพระบาทอย่าได้ทรงกลับคำมั่นที่จะปล่อยชนอิสราเอลออกไปถวายเครื่องบูชาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าอีก”

30แล้วโมเสสจึงทูลลาฟาโรห์และอธิษฐานต่อองค์พระผู้เป็นเจ้า 31องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงกระทำตามที่โมเสสทูลขอ ฝูงเหลือบก็ละจากฟาโรห์ ข้าราชการ และราษฎรของพระองค์ ไม่เหลือเหลือบแม้สักตัวเดียว 32แต่ครั้งนี้ก็เช่นกัน ฟาโรห์มีพระทัยแข็งกระด้างอีกและไม่ยอมปล่อยชนอิสราเอลไป