ዘፀአት 40 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 40:1-38

የማደሪያውን ድንኳን መትከል

1ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ 2“ማደሪያውን ይኸውም የመገናኛውን ድንኳን በወሩ የመጀመሪያ ቀን ትከለው፤ 3የምስክሩን ታቦት በውስጡ አኑር፤ ታቦቱንም በመጋረጃው ጋርደው። 4ጠረጴዛውንም ወደ ውስጥ አምጥተህ ዕቃዎቹን በላዩ ላይ አሰናዳ፤ ከዚያም መቅረዙን አስገብተህ መብራቶቹን በቦታቸው አስቀምጥ። 5የዕጣኑን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ፊት ለፊት አስቀምጠው፤ ከማደሪያውም መግቢያ ላይ መጋረጃውን አድርግ።

6“የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውን በማደሪያው መግቢያ ፊት ለፊት፣ በመገናኛው ድንኳን አስቀምጠው። 7የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አኑርበት፤ ውሃም አኑርበት። 8በዙሪያውም የአደባባዩን ቅጥር ትከል፤ መጋረጃውንም በአደባባዩ መግቢያ ላይ አድርገው።

9“ቅብዐ ዘይቱን ወስደህ ማደሪያውንና በውስጡ ያለውን ሁሉ ቅባ፤ እርሱንና ዕቃውን ሁሉ ቀድስ፤ የተቀደሰም ይሆናል። 10ከዚያም የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንና ዕቃዎቹን ሁሉ ቅባ፤ መሠዊያውን ቀድስ፣ እጅግም የተቀደሰ ይሆናል። 11የመታጠቢያው ሰንና ማስቀመጫውን ቅባ፤ ቀድሳቸውም።

12“አሮንና ወንዶች ልጆቹን ወደ መገናኛው ድንኳን መግቢያ አምጥተህ በውሃ ዕጠባቸው። 13ከዚያም አሮንን የተቀደሰውን ልብስ አልብሰው፤ ካህን ሆኖ ያገለግለኝ ዘንድ ቅባው፤ ቀድሰውም። 14ወንዶች ልጆቹን አምጥተህ ሸሚዝ አልብሳቸው። 15ካህናት ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ ልክ አባታቸውን እንደ ቀባህ ቅባቸው፤ መቀባታቸውም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ለሚቀጥል ክህነት ነው።” 16ሙሴ ሁሉንም ነገር ልክ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው አደረገ።

17እንዲሁም በሁለተኛው ዓመት፣ የመጀመሪያው ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን የማደሪያው ድንኳን ተተከለ። 18ሙሴ የማደሪያውን ድንኳን በተከለ ጊዜ፣ መቆሚያዎቹን በቦታቸው አኖረ፤ ወጋግራዎቹን አቆመ፤ አግዳሚዎቹን አስገባ፤ ምሰሶዎቹንም ተከለ። 19ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ድንኳኑን በማደሪያው ላይ፣ መደረቢያውንም በድንኳኑ ላይ ዘረጋው።

20ምስክሩን ወስዶ በታቦቱ ውስጥ አስቀመጠው፤ መሎጊያዎቹንም ከታቦቱ ጋር አያያዛቸው፤ የስርየት መክደኛውንም በላዩ ላይ አደረገው። 21ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘው ታቦቱን ወደ ማደሪያው ድንኳን አስገብቶ መከለያ መጋረጃውን ሰቀለ፤ የምስክሩንም ታቦት ጋረደው።

22ሙሴ ጠረጴዛውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ፣ ከማደሪያው በስተ ሰሜን ከመጋረጃው ውጭ አኖረው፤ 23እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም ኅብስቱን በላዩ ላይ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አኖረ።

24መቅረዙን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከጠረጴዛው ትይዩ ከማደሪያው ድንኳን በስተ ደቡብ በኩል አኖረው፤ 25እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መብራቶቹን በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አበራ።

26ሙሴ የወርቅ መሠዊያውን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ከመጋረጃው ፊት ለፊት አኖረው፤ 27እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም መልካም መዐዛ ያለውን ዕጣን አጠነበት። 28ከዚያም መጋረጃውን በማደሪያው ድንኳን መግቢያ ላይ ሰቀለው።

29የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንም በማደሪያው፣ በመገናኛው ድንኳን መግቢያ ላይ አኖረው፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) እንዳዘዘውም የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን መሥዋዕት በላዩ ላይ አቀረበ።

30የመታጠቢያውን ሰን በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አስቀመጠ፤ ለመታጠቢያም ውሃ አደረገበት፤ 31ሙሴና አሮን፣ ወንዶች ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡበት ነበር። 32እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዳዘዘው ወደ መገናኛው ድንኳን በገቡና ወደ መሠዊያው በቀረቡ ቍጥር ይታጠቡ ነበር።

33ከዚያም ሙሴ በማደሪያውና በመሠዊያው ዙሪያ አደባባዩን ተከለ፤ በአደባባዩም መግቢያ ላይ መጋረጃውን ሰቀለ፤ እንደዚህ አድርጎ ሙሴ ሥራውን ፈጸመ።

የእግዚአብሔር ክብር

34ከዚያም ደመናው የመገናኛውን ድንኳን ሸፈነ፤ የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ሞላ። 35ደመናው በላዩ ላይ ስለ ነበረና የእግዚአብሔርም (ያህዌ) ክብር ማደሪያውን ስለ ሞላው፣ ሙሴ ወደ መገናኛው ድንኳን መግባት አልቻለም።

36በእስራኤላውያን ጕዞ ሁሉ ደመናው ከማደሪያው ላይ በተነሣ ጊዜ፣ ይጓዙ ነበር፤ 37ደመናው ካልተነሣ ግን፣ እስከሚነሣበት ቀን ድረስ አይጓዙም ነበር። 38ስለዚህ በጕዟቸው ሁሉ ወቅት፣ በእስራኤል ቤት ፊት ሁሉ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ደመና በቀን ከማደሪያው በላይ፣ በሌሊትም እሳቱ በደመናው ውስጥ ነበር።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 40:1-38

การตั้งพลับพลา

1แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโมเสสว่า 2“จงตั้งพลับพลาคือเต็นท์นัดพบขึ้นในวันแรกของเดือนที่หนึ่ง 3ตั้งหีบพันธสัญญาในพลับพลา ขึงม่านกั้นบังหีบไว้ 4ยกโต๊ะเข้ามาตั้งวางภาชนะต่างๆ ลงบนโต๊ะ ตั้งคันประทีป แล้วตั้งตะเกียง 5วางแท่นทองคำสำหรับเผาเครื่องหอมตรงหน้าหีบพันธสัญญา ขึงม่านกั้นทางเข้าพลับพลา

6“จงวางแท่นเผาเครื่องบูชาตรงหน้าทางเข้าพลับพลาหรือเต็นท์นัดพบ 7วางอ่างล้างระหว่างเต็นท์นัดพบกับแท่นบูชา ใส่น้ำไว้ในอ่าง 8ตั้งลานพลับพลาโดยรอบ ขึงม่านตรงทางเข้าลานพลับพลา

9“จงเอาน้ำมันเจิมพลับพลาและเจิมของทุกอย่างในพลับพลา เจิมภาชนะเครื่องใช้ต่างๆ เพื่อชำระให้บริสุทธิ์ แล้วพลับพลานั้นจะบริสุทธิ์ 10แล้วเจิมแท่นบูชาและภาชนะเครื่องใช้ประจำแท่นเพื่อชำระแท่นนั้น และแท่นนั้นจะบริสุทธิ์ที่สุด 11เจิมอ่างชำระและฐานรอง เป็นการชำระให้บริสุทธิ์

12“จงนำอาโรนและบุตรชายของเขามาตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ เอาน้ำชำระกายพวกเขา 13จากนั้นให้อาโรนสวมเครื่องแต่งกายบริสุทธิ์ เจิมเขา และชำระเขาให้บริสุทธิ์เพื่อปฏิบัติหน้าที่ปุโรหิตรับใช้เรา 14จงนำบรรดาบุตรชายของเขาเข้ามาและให้สวมเสื้อตัวใน 15เจิมพวกเขาเช่นเดียวกับที่เจิมอาโรน เพื่อพวกเขาจะปฏิบัติหน้าที่ปุโรหิตรับใช้เรา การเจิมนี้เป็นการสถาปนาความเป็นปุโรหิตสืบไปทุกชั่วอายุ” 16โมเสสก็ทำทุกสิ่งตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

17ดังนั้นพวกเขาจึงได้ตั้งพลับพลาขึ้นในวันแรกของเดือนที่หนึ่งปีที่สอง 18โมเสสตั้งพลับพลาขึ้นโดยวางฐาน เอาไม้ฝาตั้งขึ้นแล้วสอดคานขวางและตั้งเสา 19จากนั้นคลี่ผ้าเต็นท์และเครื่องคลุมเหนือพลับพลาตามพระบัญชาขององค์พระผู้เป็นเจ้า

20เขาเอาแผ่นจารึกพันธสัญญาใส่ไว้ในหีบพันธสัญญา สอดคานหามเข้ากับหีบ และเอาพระที่นั่งกรุณาปิดหีบ 21แล้วเขานำหีบพันธสัญญาไปตั้งในพลับพลา และขึงม่านกั้นปิดหีบพันธสัญญาไว้ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

22โมเสสวางโต๊ะในเต็นท์นัดพบข้างนอกม่านที่ด้านทิศเหนือของพลับพลา 23และตั้งขนมปังไว้บนโต๊ะต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

24เขาตั้งคันประทีปตรงกันข้ามกับโต๊ะในเต็นท์นัดพบทางด้านทิศใต้ของพลับพลา 25และตั้งตะเกียงต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

26โมเสสวางแท่นทองคำไว้ในเต็นท์นัดพบตรงหน้าม่าน 27แล้วเผาเครื่องหอมบนแท่นนั้น ตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาไว้ 28จากนั้นเขากั้นม่านตรงทางเข้าพลับพลา

29แล้วเขาวางแท่นบูชาใกล้ทางเข้าพลับพลาหรือเต็นท์นัดพบ จากนั้นจึงถวายเครื่องเผาบูชา เครื่องธัญบูชาตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชา

30เขาวางอ่างชำระระหว่างเต็นท์นัดพบกับแท่นบูชา ใส่น้ำเพื่อชำระล้าง 31โมเสสและอาโรนกับบรรดาบุตรชายล้างมือและเท้าที่นั่น 32คราวใดที่พวกเขาเข้าใกล้แท่นบูชาหรือเข้าไปในเต็นท์นัดพบ ก็ล้างมือและเท้าตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงบัญชาโมเสสไว้

33แล้วโมเสสกั้นลานรอบพลับพลาและแท่น จากนั้นขึงม่านตรงทางเข้าลานพลับพลา เป็นอันว่าโมเสสทำงานเสร็จเรียบร้อย

พระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้า

34แล้วมีเมฆเคลื่อนลงมาปกคลุมเต็นท์นัดพบ และพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้าปกคลุมทั่วพลับพลา 35โมเสสไม่สามารถเข้าไปในเต็นท์นัดพบเพราะที่นั่นมีเมฆหนา และพระเกียรติสิริขององค์พระผู้เป็นเจ้าปกคลุมทั่วพลับพลา

36ตลอดการเดินทาง เมื่อใดที่เมฆซึ่งอยู่เหนือพลับพลาลอยขึ้น ชนอิสราเอลก็ออกเดินทาง 37แต่ถ้าเมฆนั้นไม่ลอยขึ้น พวกเขาก็ไม่ออกเดินทางจนกว่าเมฆจะเคลื่อน 38เมฆขององค์พระผู้เป็นเจ้าลอยอยู่เหนือพลับพลาในยามกลางวัน และในยามกลางคืนก็มีไฟอยู่ในเมฆ ประจักษ์แก่ตาชนอิสราเอลทั้งปวงตลอดการเดินทาง