ዘፀአት 38 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 38:1-31

የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያ

38፥1-7 ተጓ ምብ – ዘፀ 27፥1-8

1ከፍታው ሦስት ክንድ38፥1 ርዝመቱ 1.3 ሜትር ያህል ማለት ነው። የሆነ የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያ ከግራር ዕንጨት ሠሩ38፥1 ወይም ሥራ፤ ርዝመቱ አምስት ክንድ፣ ወርዱ አምስት ክንድ የሆነ ባለ አራት ማእዘን ነበረ። 2ቀንዶቹና መሠዊያው አንድ ወጥ ይሆኑ ዘንድ በአራቱም ማእዘኖች ላይ አራት ቀንድ ሠሩ፤ መሠዊያውንም በናስ ለበጡት። 3ዕቃዎቹንም ሁሉ ይኸውም ምንቸቶቹን፣ መጫሪያዎቹን፣ መርጫ ጐድጓዳ ሳሕኖቹን፣ ሜንጦዎቹንና የእሳት መያዣዎቹን ከናስ ሠሯቸው። 4ለመሠዊያውም ከጠርዝ በታች ሆኖ ከመሠዊያው ግማሽ ቁመት ላይ የሚሆን የናስ ፍርግርግ ማንደጃ ሠሩ። 5ለናሱ ፍርፍርግ ማንደጃ አራት ማእዘኖች መሎጊያዎቹን እንዲይዙ የናስ ቀለበቶችን ሠሩ። 6መሎጊያዎቹን ከግራር ዕንጨት ሠርተው በናስ ለበጧቸው። 7መሠዊያውን ለመሸከም በመሠዊያው ጐኖች ይሆኑ ዘንድ መሎጊያዎቹን በቀለበቶቹ ውስጥ አስገቧቸው፤ ውስጡንም ክፍት በማድረግ ከሳንቃዎች ሠሩት።

የመታጠቢያው ሳሕን

8የናስ መታጠቢያ ሳሕንና የናስ መቆሚያውን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ ከሚያገለግሉት ሴቶች መስተዋት ሠሩት።

አደባባዩ

38፥9-20 ተጓ ምብ – ዘፀ 27፥9-19

9ቀጥሎም አደባባዩን ሠሩ፤ የደቡቡ ክፍል ርዝመት አንድ መቶ ክንድ38፥9 ወደ 46 ሜትር ያህል ነው። ሲሆን፣ በቀጭኑ ከተፈተለ በፍታ የተሠሩ መጋረጃዎች ነበሩት፤ 10ሃያ ምሰሶዎችና ሃያ የናስ መቆሚያዎች፣ የብር ኵላቦችና በምሰሶዎቹ ላይ ዘንጎች ነበሩት። 11የሰሜኑም ክፍል ቁመቱ አንድ መቶ ክንድ ነበር፤ ሃያ ምሰሶዎችና ሃያ የናስ መቆሚያዎች፣ የብር ኵላቦችና በምሰሶዎቹም ላይ ዘንጎች ነበሩት።

12የምዕራቡ ጫፍ ወርዱ አምሳ ክንድ38፥12 ወደ 23 ሜትር ያህል ነው። ነበር፤ ዐሥር ምሰሶዎችና ዐሥር መቆሚያዎች እንዲሁም የብር ኵላቦችና በምሰሶዎቹም ላይ ዘንጎች ያሉት መጋረጃዎች ነበሩት። 13በፀሓይ መውጫ በኩል ያለው የምሥራቁም ጫፍ ወርዱ አምሳ ክንድ ነበር። 14ከሦስት ምሰሶዎችና ከሦስት መቆሚያዎች ጋር ርዝመታቸው ዐሥራ አምስት ክንድ38፥14 ወደ 6.9 ሜትር ያህል ነው። የሆኑ መጋረጃዎች በአንድ በኩል ባለው መግቢያ ላይ ነበሩ፤ 15ከሦስት ምሰሶዎችና ከሦስት መቆሚያዎች ጋር ርዝመታቸው ዐሥራ አምስት ክንድ የሆኑ መጋረጃዎች በአደባባዩ መግቢያ በሌላው በኩል ነበሩ።

16በአደባባዩ ዙሪያ ያሉት መጋረጃዎች በሙሉ በቀጭኑ ከተፈተለ በፍታ የተሠሩ ነበሩ። 17የምሰሶዎቹ መቆሚያዎች ናስ ነበሩ፤ ኵላቦቹና በምሰሶዎቹ ላይ ያሉት ዘንጎች ከብር የተሠሩ ነበሩ፤ ጫፎቻቸውም በብር ተለብጠው ነበር፤ ስለዚህ የአደባባዩ ምሰሶዎች ሁሉ የብር ዘንጎች ነበሯቸው።

18በአደባባዩ መግቢያ ላይ ያለው መጋረጃ ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከቀይ ማግና የጥልፍ ባለሙያ ከጠለፈው፣ በቀጭኑ ከተፈተለ በፍታ የተሠራ ነበር፤ ቁመቱ ሃያ ክንድ38፥18 ወደ 9 ሜትር ያህል ነው።፣ እንደ አደባባዩ መጋረጃዎች ከፍታው አምስት ክንድ ነበረ፤ 19አራት ምሰሶዎችና አራት መቆሚያዎች ነበሩት፤ ኵላቦቻቸውና ዘንጎቻቸው የብር ሲሆኑ፣ ጫፎቻቸው በብር ተለብጠው ነበር። 20የማደሪያው ድንኳንና የአደባባዩ ዙሪያ ካስማዎች ሁሉ ከናስ የተሠሩ ነበሩ።

ለአገልግሎት የዋሉ ዕቃዎች

21ለማደሪያው ድንኳን፣ ይኸውም ለምስክሩ ድንኳን ሙሴ ባዘዘው፣ በካህኑ በአሮን ልጅ በኢታማር መሪነት ሌዋውያኑ በጻፉት መሠረት የዕቃዎቹ ቍጥር ይህ ነው። 22ከይሁዳ ነገድ የሆር የልጅ ልጅ፣ የኡሪ ልጅ የሆነው ባስልኤል፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ አደረገ። 23ከእርሱም ጋር ከዳን ነገድ የሆነው የአሂሳሚክ ልጅ ኤልያብ፣ ዕቅድ አውጭና የእጅ ጥበብ ባለሙያ፣ በሰማያዊ፣ በሐምራዊ፣ በቀይ ማግና በቀጭን በፍታ ጥልፍ ጠላፊ ነበር። 24ለመቅደሱ ሥራ ሁሉ ከመወዝወዙ ስጦታ በመቅደሱ ሰቅል መሠረት የዋለው ጠቅላላ ወርቅ ሃያ ዘጠኝ መክሊትና ሰባት መቶ ሠላሳ ሰቅል38፥24 የወርቁ መጠን ወደ አንድ ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ነበረ።

25በቈጠራው ወቅት ተቈጥረው ከነበሩት ማኅበረ ሰብ የተገኘው ብር ለመቅደሱ ሰቅል አንድ መቶ መክሊትና አንድ ሺሕ ሰባት መቶ ሰባ አምስት ሰቅሎች38፥25 የብሩ መጠን 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ነበሩ። 26ከተቈጠሩት ጋር አብረው ከሆኑት ሃያና ከሃያ ዓመት በላይ የሆናቸው ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ሰዎች የሰጡት እንደ መቅደሱ ሰቅል ሚዛን በአንድ ሰው አንድ ቤካ ይኸውም ግማሽ ሰቅል38፥26 ወደ 5.5 ግራም ያህል ነው። ነበረ። 27አንድ መቶ የብር መክሊቶች38፥27 ወደ 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። የመቅደሱንና የመጋረጃዎቹን መቆሚያዎች ለመሥራት አገልግሎት ላይ ውለው ነበር፤ ይኸውም ከአንድ መቶ መክሊቶች አንድ መቶ መቆሚያዎች ሲሆን፣ ለእያንዳንዱ መቆሚያ አንድ መክሊት ማለት ነው። 28አንድ ሺሕ ሰባት መቶ ሰባ አምስት ሰቅሎችን38፥28 ወደ 20 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ለምሰሶዎቹ ኵላቦች፣ የምሰሶዎቹን ዐናት ለመለበጥና ዘንጎቻቸውንም ለመሥራት አገልግሎት ላይ ውለው ነበር።

29ከመወዝወዙ ስጦታ የሆነው ናስ ሰባ መክሊትና ሁለት ሺሕ አራት መቶ ሰቅል38፥29 የናሱ መጠን 2.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ነበረ። 30ለመገናኛው ድንኳን መግቢያ ለናስ መሠዊያው ከናስ መጫሪያው፣ ለዕቃዎቹም ሁሉ መቆሚያዎቹን ለመሥራት አገልግሎት ላይ አውለውት ነበር፤ 31ለአደባባዩ ዙሪያ፣ ለመግቢያው እንዲሁም ለማደሪያው ድንኳን ካስማዎች ሁሉና ለአደባባዩ ዙሪያ ሁሉ እንዲሁ አገልግሎት ላይ አውለውት ነበር።

Thai New Contemporary Bible

อพยพ 38:1-31

แท่นบูชา

(อพย.27:1-8)

1เขาทำแท่นเผาเครื่องบูชาจากไม้กระถินเทศ รูปสี่เหลี่ยมจัตุรัสขนาดกว้างยาวด้านละ 5 ศอก สูง 3 ศอก38:1 คือ กว้างยาวประมาณด้านละ 2.3 เมตร สูงประมาณ 1.3 เมตร 2ทำเชิงงอนที่มุมทั้งสี่ของแท่นเป็นเนื้อเดียวกับตัวแท่น และใช้ทองสัมฤทธิ์หุ้มรอบแท่น 3และทำภาชนะทุกชิ้นของแท่นบูชาด้วยทองสัมฤทธิ์ ทั้งหม้อใส่เถ้า ทัพพี อ่างประพรม ขอเกี่ยวเนื้อและถาดรองไฟ 4เขาทำตะแกรงทองสัมฤทธิ์สำหรับวางที่ด้านในของแท่น ใต้ขอบบนอยู่ระดับกลางแท่น 5เขาหล่อห่วงทองสัมฤทธิ์ที่มุมทั้งสี่ของตะแกรงทองสัมฤทธิ์สำหรับสอดคานหาม 6เขาทำคานหามจากไม้กระถินเทศหุ้มด้วยทองสัมฤทธิ์ 7และสอดคานนั้นไว้ในห่วงข้างแท่นเพื่อใช้หาม เขาทำแท่นนั้นด้วยไม้กระดาน ให้ภายในกลวง

อ่างสำหรับล้างชำระ

8เขาทำอ่างทองสัมฤทธิ์และฐานรองทองสัมฤทธิ์จากกระจกเงาของพวกผู้หญิงที่ปรนนิบัติตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ

ลานพลับพลา

(อพย.27:9-19)

9จากนั้นเขาทำลานพลับพลา มีผ้าลินินเนื้อดีเป็นม่านปิดทางด้านทิศใต้ ม่านคลี่ออกกว้าง 100 ศอก38:9 คือ ประมาณ 46 เมตร เช่นเดียวกับข้อ 11 10มีเสายี่สิบต้นปักบนฐานรองรับยี่สิบฐานทำด้วยทองสัมฤทธิ์ และมีตะขอเงินติดกับราวเงินสำหรับแขวนม่านติดอยู่กับเสา 11ผนังด้านทิศเหนือยาว 100 ศอกเช่นกัน มีเสายี่สิบต้นพร้อมฐานรองรับทำจากทองสัมฤทธิ์ยี่สิบฐาน และมีตะขอเงินและราวเงินสำหรับแขวนม่านติดอยู่กับเสา

12ด้านทิศตะวันตกมีม่านกว้าง 50 ศอก38:12 คือ ประมาณ 23 เมตร เช่นเดียวกับข้อ 13และมีเสาสิบต้นปักบนฐานทั้งสิบ และมีตะขอเงินกับราวเงินสำหรับแขวนม่านติดอยู่กับเสา 13ด้านทิศตะวันออกก็กว้าง 50 ศอกเช่นกัน 14ด้านหนึ่งของทางเข้ามีม่านยาว 15 ศอก38:14 คือ ประมาณ 6.9 เมตร เช่นเดียวกับข้อ 15เกี่ยวบนเสาสามต้นซึ่งปักบนฐานสามฐาน 15อีกด้านหนึ่งของทางเข้าสู่ลานพลับพลามีม่านยาว 15 ศอกเกี่ยวบนเสาสามต้นซึ่งปักบนฐานสามฐาน 16ม่านรอบลานพลับพลาทั้งหมดทอด้วยผ้าลินินเนื้อดี 17ฐานรองรับเสาทำจากทองสัมฤทธิ์ ตะขอและราวขึงม่านล้วนทำจากเงิน หัวเสาก็หุ้มด้วยเงิน ดังนั้นเสาทุกต้นของลานพลับพลามีปลอกทำด้วยเงิน

18ม่านกั้นทางเข้าลานพลับพลาทั้งหมดทำจากผ้าลินินเนื้อดี ปักอย่างวิจิตรด้วยด้ายสีน้ำเงิน ม่วง และแดง กว้าง 20 ศอก สูง 5 ศอก38:18 คือ กว้างประมาณ 9 เมตร สูงประมาณ 2.3 เมตร เช่นเดียวกับผ้าม่านผนังลานพลับพลา 19มีเสาค้ำสี่ต้นพร้อมฐานทองสัมฤทธิ์สี่ฐาน ตะขอและราวขึงม่านทำด้วยเงิน หัวเสาก็เป็นเงิน 20หลักหมุดทั้งหมดของพลับพลาและลานพลับพลาโดยรอบทำด้วยทองสัมฤทธิ์

วัสดุที่ใช้

21สิ่งเหล่านี้คือรายการวัสดุที่ใช้สำหรับพลับพลา ที่ตั้งของหีบพันธสัญญา ซึ่งโมเสสสั่งให้คนเลวีบันทึกไว้ ภายใต้การกำกับดูแลของอิธามาร์บุตรชายของปุโรหิตอาโรน 22(เบซาเลลบุตรชายของอูรีซึ่งเป็นบุตรชายของเฮอร์จากเผ่ายูดาห์ได้ทำทุกสิ่งตามที่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสสั่งโมเสส 23ผู้ช่วยของเขาคือโอโฮลีอับบุตรชายของอาหิสะมัคจากเผ่าดาน เขาก็เป็นช่างฝีมือและนักออกแบบและเป็นช่างปักด้วยด้าย สีน้ำเงิน ม่วง และแดงลงบนผ้าลินินเนื้อดี) 24ทองคำทั้งหมดจากเครื่องบูชายื่นถวายซึ่งใช้ในงานสถานนมัสการมีน้ำหนักประมาณ 1 ตัน38:24 ภาษาฮีบรูว่า 29 ตะลันต์ 730 เชเขลตามเชเขลของสถานนมัสการ

25เงินที่เก็บมาจากชุมชนหนักประมาณ 3.4 ตัน38:25 ภาษาฮีบรูว่า 100 ตะลันต์ 1,775 เชเขลตามเชเขลของสถานนมัสการ 26โดยเก็บจากผู้ชายอายุยี่สิบปีขึ้นไป ตามรายชื่อในทะเบียนสำมะโนประชากรรวม 603,550 คน คนละประมาณ 5.5 กรัม38:26 ภาษาฮีบรูว่า 1 เบคา นั่นคือครึ่งเชเขลตามเชเขลของสถานนมัสการ 27เงินหนักประมาณ 3.4 ตัน38:27 ภาษาฮีบรูว่า 100 ตะลันต์ใช้ทำฐานรองรับสถานนมัสการและเสาค้ำม่าน 100 ฐาน แต่ละฐานใช้เงินหนักประมาณ 34 กิโลกรัม38:27 ภาษาฮีบรูว่า 1 ตะลันต์ 28เงินอีกประมาณ 20 กิโลกรัม38:28 ภาษาฮีบรูว่า 1,775 เชเขลใช้ทำตะขอบนเสา หุ้มหัวเสา และทำราวยึดม่าน

29ทองสัมฤทธิ์ซึ่งนำมาจากเครื่องบูชายื่นถวายหนักประมาณ 2.4 ตัน38:29 ภาษาฮีบรูว่า 70 ตะลันต์ 2,400 เชเขล 30ใช้ในการหล่อฐานรองรับเสาตรงทางเข้าเต็นท์นัดพบ แท่นบูชาทองสัมฤทธิ์พร้อมกับตะแกรงทองสัมฤทธิ์ และภาชนะใช้สอยทั้งหมดสำหรับแท่น 31ฐานรองรับเสาลานพลับพลาโดยรอบ ทางเข้าและหลักหมุดที่ใช้ในการสร้างพลับพลาและลานพลับพลาโดยรอบ