ዘፀአት 30 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 30:1-38

የዕጣን መሠዊያ

30፥1-5 ተጓ ምብ – ዘፀ 37፥25-28

1“ዕጣን የሚጤስበት መሠዊያ ከግራር ዕንጨት ሥራ። 2ርዝመቱና ጐኑ ባለ አንድ አንድ ክንድ30፥2 ርዝመቱና ጐኑ 0.5 ሜትር፣ ከፍታው 0.9 ሜትር ያህል ነው። የሆነ ከፍታውም ሁለት ክንድ የሆነ አራት ማእዘን ይሁን፤ ከመሠዊያው ጋር አንድ ወጥ የሆኑ ቀንዶች ይኑሩት። 3ላዩን፣ ጐኖቹን ሁሉና ቀንዶቹን በንጹሕ ወርቅ ለብጣቸው፤ ዙሪያውን የወርቅ ክፈፍ አብጅለት። 4መሠዊያውን ለመሸከም የሚያገለግሉትን መሎጊያዎች የሚይዙ፣ ከክፈፉ በታች ትይዩ የሆኑ ሁለት የወርቅ ቀለበቶችን ለመሠዊያው አብጅ። 5መሎጊያዎቹንም ከግራር ዕንጨት ሠርተህ በወርቅ ለብጣቸው። 6መሠዊያውን ከመጋረጃው ፊት ለፊት፣ ይኸውም ከምስክሩ ታቦት ፊት፣ ከምስክሩ በላይ ካለው እኔ አንተን ከምገናኝበት ከስርየት መክደኛው ፊት አስቀምጠው።

7“አሮን መብራቶቹን በሚያዘጋጅበት ጊዜ፣ በየማለዳው ደስ የሚያሰኝ ሽታ ዕጣን በመሠዊያው ላይ ያጢስ። 8ምሽት ላይ መብራቶቹን በሚያበራበትም ጊዜ ዕጣኑን ማጠን አለበት፤ ይኸውም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ዕጣኑ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ዘወትር እንዲጤስ ነው። 9በዚህም መሠዊያ ላይ ሌላ ዕጣን ወይም ሌላ የሚቃጠል መሥዋዕት ወይም የእህል መሥዋዕት አታቅርብ፤ የመጠጥ መሥዋዕትም አታፍስስበት። 10አሮን በዓመት አንድ ጊዜ በቀንዶቹ ላይ ማስተስረያ ያደርግበታል፤ ይህ ዓመታዊ ማስተስረያ በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ለማስተስረያ ከሚሆን የኀጢአት መሥዋዕት ደም ጋር መደረግ አለበት፤ ይህም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) እጅግ ቅዱስ ነው።”

የማስተስረያ ገንዘብ

11ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ 12“የእስራኤላውያንን ጠቅላላ ቈጠራ በምታደርግበት ጊዜ እያንዳንዱ ሰው በሚቈጠርበት ወቅት ለሕይወቱ ቤዛ የሚሆን ወጆ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መክፈል አለበት፤ በዚህም ዐይነት ስትቈጥራቸው በእነርሱ ላይ መቅሠፍት አይመጣም። 13ማንም ወደ ተቈጠሩት ዘንድ የሚያልፍ ሃያ አቦሊ በሚመዝን በመቅደሱ ሰቅል ሚዛን ግማሽ ሰቅል30፥13 በዚህና በቍጥር 15 ላይ 6 ግራም ያህል ነው። መስጠት አለበት፤ ይህ ግማሽ ሰቅል ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የሚቀርብ መሥዋዕት ነው። 14ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከሃያ በላይ ሆኖ ወደ ተቈጠሩት ያለፉት ሁሉ፣ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት ማቅረብ አለባቸው። 15ለሕይወታችሁ ማስተስረያ እንዲሆን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት በምታቀርቡበት ጊዜ ባለጠጋው ከግማሽ ሰቅል በላይ፣ ድኻውም አጕድሎ አይስጥ። 16የማስተስረያውን ገንዘብ ከእስራኤላውያን ተቀብለህ ለመገናኛው ድንኳን አገልግሎት አውለው፤ ለሕይወታችሁ ማስተስረያ በማድረግ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት የእስራኤላውያን ማስተስረያ ይሆናል።”

የመታጠቢያ ሰን

17ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ 18“ለመታጠቢያ ከናስ ማስቀመጫው ጋር የናስ ሰን አብጅ፤ በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል አስቀምጠህ ውሃ አድርግበት። 19አሮንና ወንዶች ልጆቹ በውስጡ ባለው ውሃ እጃቸውንና እግራቸውን ይታጠቡበታል። 20ወደ መገናኛው ድንኳን በሚገቡበት ጊዜ ሁሉ እንዳይሞቱ በውሃ ይታጠቡ፤ እንዲሁም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የእሳት መሥዋዕት ለማቅረብ ወደ መሠዊያው ለማገልገል በሚቀርቡበት ጊዜ፣ 21እንዳይሞቱ እጃቸውንና እግራቸውን ይታጠባሉ፤ ይህም በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ለአሮንና ለትውልዶቹ የዘላለም ሥርዐት ይሆናል።”

ቅብዐ ዘይት

22ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፣ 23“ምርጥ ቅመሞችን፣ አምስት መቶ ሰቅል30፥23 ወደ 6 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ፈሳሽ ከርቤ፣ ግማሽ ይኸውም ሁለት መቶ አምሳ ሰቅል ጣፋጭ ቀረፋ፣ ሁለት መቶ አምሳ ሰቅል ጠጅ ሣር፣ 24አምስት መቶ ሰቅል ብርጕድ ውሰድ፤ ሁሉም እንደ መቅደሱ ሰቅልና አንድ የኢን መስፈሪያ30፥24 ወደ 4 ሊትር ያህል ነው። የወይራ ዘይት ይሁን፤ 25እነዚህን በቀማሚ እንደ ተሠራ እንደሚሸት ቅመም የተቀደሰ ቅብዐ ዘይት አድርግ፤ የተቀደሰ ቅብዐ ዘይት ይሆናል። 26ከዚያም የመገናኛውን ድንኳን፣ የምስክሩን ታቦት፣ 27ጠረጴዛውንና ዕቃዎቹን ሁሉ፣ መቅረዙንና ዕቃዎቹን፣ የዕጣን መሠዊያውን፣ 28የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያውንና ዕቃዎቹን ሁሉ እንዲሁም የመታጠቢያ ሰኑን ከነመቆሚያው እንድትቀባበት ይሁን። 29እጅግ የተቀደሱ ይሆኑም ዘንድ ቀድሳቸው፤ የሚነካቸውም ሁሉ የተቀደሰ ይሆናል።

30“ካህናት ሆነው ያገለግሉኝ ዘንድ አሮንንና ወንዶች ልጆቹን ቅባቸው፤ ቀድሳቸውም። 31ለእስራኤላውያን ንገራቸው፤ ‘በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ይህ የእኔ የተቀደሰ የቅብዐት ዘይት ይሆናል። 32በማንም ሰው ሰውነት ላይ አታፍስሱት፤ በተመሳሳይ መንገድ ምንም ዘይት አትሥሩ፤ የተቀደሰ ነው፤ ቅዱስ መሆኑን ልብ በሉ። 33ተመሳሳይ ዐይነት የሠራና ከካህናት ሌላ በማንም ሰው ላይ ያፈሰሰ ሁሉ ከወገኑ ይወገድ።’ ”

ዕጣን

34ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “ተመጣጣኝ በማድረግ የጣፋጭ ሽቱ ቅመሞች፣ የሚንጠባጠብ ሙጫ፣ በዛጐል ውስጥ የሚገኝ ሽቱ፣ የሚሸት ሙጫ እና ንጹሕ ዕጣን ወስደህ፣ 35በቀማሚ እንደ ተሠራ ጣፋጭ መዐዛ ያለው የተቀመመ ዕጣን አብጅ፤ በጨው የተቀመመ፣ ንጹሕና የተቀደሰ ይሁን። 36ከእርሱም ጥቂቱን ወቅጠህ ዱቄት በማድረግ አልመህ በመገናኛው ድንኳን ከምስክሩ ፊት ለፊት ከአንተ ጋር በምገናኝበት ስፍራ አስቀምጠው፤ ለአንተ እጅግ የተቀደሰ ይሆናል። 37ለራስህ በዚያ ዐይነት መንገድ ምንም ዐይነት ዕጣን አታብጅ። ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ መሆኑን ልብ በል። 38በመልካም ሽታው ይደሰት ዘንድ እርሱን አስመስሎ የሚሠራ ሁሉ ከወገኑ የተወገደ ይሁን።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

出埃及记 30:1-38

造香坛的条例

1“你要用皂荚木造一座烧香用的坛。 2坛是四方形的,长宽各四十五厘米,高九十厘米,上面有突出的角状物,与坛连成一体。 3坛顶、坛的四面和坛上的角状物要包上纯金,四周镶上金边。 4要在坛两侧的金边下面安两个金环,使横杠穿过金环,以便抬香坛。 5要用皂荚木造横杠,包上金。 6要把香坛放在约柜前幔子的外面,对着约柜上的施恩座——就是我要跟你会面的地方。

7亚伦每天早上料理灯台的时候,要在这坛上烧芬芳的香。 8黄昏点灯的时候,他也要在耶和华面前烧香,世世代代都要如此。 9不可在这香坛上烧别的香料,不可用这坛来献燔祭或素祭,也不可在上面浇奠祭。 10亚伦每年要在坛的角上行一次赎罪礼,用赎罪祭牲的血涂在坛角上,世代如此。这是耶和华至圣的坛。”

人丁的赎价

11耶和华对摩西说: 12“你统计以色列人口的时候,每一个被统计的男子都要缴付赎价给耶和华,赎回自己的性命,免得在统计人口期间发生灾祸。 13凡被统计的人都要付六克银子,即十季拉,以圣所的秤为准,作为献给耶和华的礼物。 14凡被统计的,年龄在二十岁以上的男子都要献此礼物给耶和华。 15富有的不用多缴,贫穷的也不可少付,每个人都要付六克银子,作为献给耶和华的礼物,用来赎他们自己的性命。 16要向以色列人收赎命的款项,供会幕使用,可以使以色列人在耶和华面前蒙眷顾,赎性命。”

洗濯盆

17耶和华对摩西说: 18“你用铜造一个洗濯盆和盆座,放在会幕和祭坛之间,盆里盛着水, 19亚伦父子们洗手洗脚, 20他们进会幕或在坛上献火祭之前,一定要自洁才可以供职,免得死亡。 21他们要洗手洗脚,免得死亡,这是亚伦和他的子孙世世代代都要守的条例。”

22耶和华对摩西说: 23“要以圣所的秤为准,用上等的香料,就是没药液六公斤、香肉桂和菖蒲各三公斤、 24肉桂皮六公斤,再加上橄榄油四升, 25按着调制香料的方法制作圣膏油。 26要用这些膏油来抹会幕、约柜、 27桌子和桌上所有的器具、灯台和灯台上的器具、香坛、 28燔祭坛和坛上所有的器具、洗濯盆和盆座。 29你要使这一切圣洁,成为至圣之物。凡碰到它们的都会圣洁。

30“你也要用这种油来膏亚伦父子们,使他们分别出来,做圣洁的祭司事奉我。 31你要把我的话告诉以色列百姓,‘我要世世代代以这油为圣膏油。 32不要把这膏油用在普通人身上,也不可仿制,因为这是圣膏油,你们也要视之为圣物。 33任何人若仿制或用这油抹祭司以外的人,要将他从民中铲除。’”

34耶和华对摩西说:“要取各种芬芳的香料,就是苏合香、香螺、白松香和纯乳香,分量相同, 35用调制香料的方法调制,加上盐,做成纯净圣洁的香。 36你们要把一些香捣成极细的粉末,放在会幕内的约柜前面,就是我与你会面的地方,你们要视这香为至圣之物。 37你们不可用同样的配方为自己做香,要视它为耶和华的圣物。 38任何人若仿制这香,自己拿来私用30:38 私用”希伯来文是“闻这香味”。,必从民中被铲除。”