ዘፀአት 16 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዘፀአት 16:1-36

መናና ድርጭት

1መላው የእስራኤል ማኅበር ከግብፅ በወጡ በሁለተኛው ወር በዐሥራ አምስተኛው ቀን ከኤሊም ተነሥተው በኤሊምና በሲና መካከል ወደምትገኘው ወደ ሲን ምድረ በዳ መጡ። 2በምድረ በዳውም መላው ማኅበር በሙሴና በአሮን ላይ አጕረመረሙ። 3እስራኤላውያንም እነርሱን እንዲህ አሏቸው፣ “በሥጋ መቀቀያው ምንቸት ዙሪያ ተቀምጠን የፈለግነውን ያህል ምግብ መመገብ በምንችልበት በግብፅ ሳለን፣ ምነው በእግዚአብሔር (ያህዌ) እጅ ሞተን ባረፍነው ኖሮ! እናንተ ግን ይህ ሁሉ ጉባኤ በራብ እንዲያልቅ ወደዚህ ምድረ በዳ አመጣችሁን” አሏቸው።

4ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “ከሰማይ እንጀራ አዘንብላችኋለሁ። ሕዝቡም በየቀኑ እየወጡ ለዕለት የሚበቃቸውን ይሰበስቡ፤ በዚህም ትእዛዞቼን ይጠብቁ እንደ ሆነ እፈትናቸዋለሁ። 5በስድስተኛው ቀን በሌሎቹ ዕለታት ከሚሰበስቡት ዕጥፍ ሰብስበው ያዘጋጁ።”

6ስለዚህ ሙሴና አሮን ለእስራኤላውያን ሁሉ፣ እንዲህ አሉ፤ “ከግብፅ ምድር ያወጣችሁ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኑን በዛሬዪቱ ምሽት ታውቃላችሁ። 7በእርሱ ላይ ያሰማችሁትን ማጕረምረም ሰምቷልና በማለዳ እግዚአብሔርን (ያህዌ) ክብር ታያላችሁ፤ ለመሆኑ በእኛስ ላይ የምታጕረመርሙት እኛ ምንድን ነንና ነው?” አሏቸው። 8ሙሴም ንግግሩን በመቀጠል፣ “በእርሱ ላይ ማጕረምረማችሁን ሰምቷልና በምሽት የምትበሉትን ሥጋ፣ በማለዳም የምትፈልጉትን ያህል እንጀራ በሚሰጣችሁ ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኑን ታውቃላችሁ፤ እኛ ማን ነን? በእኛ ላይ አይደለም ያጕረመረማችሁት፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ላይ ነው እንጂ” አላቸው።

9ከዚያም ሙሴ አሮንን፣ “ ‘ማጕረምረማችሁን እርሱ ሰምቷልና ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ቅረቡ’ ብለህ ለመላው የእስራኤል ማኅበር ተናገር” አለው።

10አሮንም ለመላው የእስራኤል ማኅበር ሲናገር ሳለ ወደ ምድረ በዳው ተመለከቱ፤ በዚያም የእግዚአብሔር (ያህዌ) ክብር በደመናው ላይ ተገልጦ ይታይ ነበር።

11እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 12“የእስራኤላውያንን ማጕረምረም ሰምቻለሁ፤ ይህን ንገራቸው፤ ‘ፀሓይ ከመጥለቋ በፊት ሥጋ ትበላላችሁ፤ ሲነጋም እንጀራ ትበላላችሁ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ (ያህዌ ኤሎሂም) መሆኔን ታውቃላችሁ።’ ”

13በዚያች ምሽት ድርጭቶች መጥተው ሰፈሩን አለበሱት፤ በነጋውም በሰፈሩ ዙሪያ ጤዛ ተኝቶበት ነበር። 14ጤዛው ከረገፈ በኋላ በሜዳው ላይ ስስ የሆነ ዐመዳይ የሚመስል የተጋገረ ነገር በምድረ በዳው ላይ ታየ። 15እስራኤላውያንም ይህን ባዩ ጊዜ ምን እንደ ሆነ ባለማወቃቸው እርስ በርሳቸው፣ “ይህ ነገር ምንድን ነው?” ተባባሉ።

ሙሴም፣ “ይህ ትበሉት ዘንድ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሰጣችሁ እንጀራ ነው አላቸው። 16እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ይህ ነው፤ ‘እያንዳንዱ የሚያስፈልገውን ያህል ይሰብስብ፤ በድንኳናችሁ ባለው ሰው ልክ ለእያንዳንዱ አንድ ጎሞር16፥16 ይህ በቍጥር 18፡32፡33 እንዲሁም 36 ላይ ተጠቅሷል፤ ወደ ሁለት ሊትር ያህል ይሆናል። ውሰዱ’ ” ብሎ እግዚአብሔር (ያህዌ) አዝዟል።

17እስራኤላውያንም እንደ ተነገራቸው አደረጉ፤ አንዳንዶች አብዝተው፣ አንዳንዶች ደግሞ አሳንሰው ሰበሰቡ። 18የሰበሰቡትን በጎሞር በሰፈሩ ጊዜ ብዙ የሰበሰበው አልተረፈውም፤ ጥቂት የሰበሰበውም አልጐደለበትም፤ እያንዳንዱ የሰበሰበው የሚያስፈልገውን ያህል ሆነ።

19ሙሴም፣ “ማንም ከዚህ ለነገ ምንም ማስተረፍ የለበትም” አላቸው።

20ሆኖም ግን አንዳንዶቹ ሙሴ የተናገረውን ቸል በማለት ከሰበሰቡት ውስጥ ከፊሉን አስተርፈው አሳደሩ፤ በማግስቱም ጧት ተልቶ መሽተት ጀመረ፤ ስለዚህ ሙሴ ተቈጣቸው።

21በየማለዳው እያንዳንዱ የሚያስፈልገውን ያህል ሰበሰበ፤ ፀሓዩ እየበረታ በሄደም ጊዜ ቀለጠ። 22በስድስተኛው ቀን ለእያንዳንዱ ሰው ሁለት ሁለት ጎሞር16፥22 ምናልባት ወደ 4.5 ሊትር ሊደርስ ይችላል። አድርገው ዕጥፍ ሰበሰቡ፤ የማኅበሩም አለቆች ወደ ሙሴ መጥተው ይህንኑ ነገሩት። 23እርሱም አላቸው፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ይህ ነው፤ ‘ነገ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ ሰንበት በመሆን፣ የዕረፍት ቀን ይሆናል።’ ስለዚህ መጋገር የምትፈልጉትን ጋግሩ፤ መቀቀል የምትፈልጉትን ቀቅሉ። የተረፈውን አስቀምጡ፤ እስከ ጧትም ድረስ አቈዩት።”

24ስለዚህ ሙሴ እንዳዘዘው እስከ ጧት ድረስ አቈዩት፤ አልሸተተም፤ ወይም አልተላም። 25ሙሴም እንዲህ አለ፤ “ዛሬውኑ ብሉት፤ ዛሬ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰንበት ነውና። ዛሬ በመሬት ላይ ምንም አታገኙም። 26ስድስት ቀን ትሰበስቡታላችሁ፤ በሰባተኛው ቀን በሰንበት ዕለት ግን ምንም ነገር አይኖርም።”

27ሆኖም አንዳንዶቹ በሰባተኛው ቀን ለመሰብሰብ ወጡ፤ ነገር ግን ምንም አላገኙም። 28ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “ትእዛዞቼንና መመሪያዎቼን ለመፈጸም እስከ መቼ እንቢ ትላላችሁ?16፥28 ዕብራይስጡ የብዙ ቍጥር ያሳያል። 29እግዚአብሔር (ያህዌ) ሰንበትን የሰጣችሁ መሆኑን ልብ በሉ፤ በስድስተኛው ቀን ለሁለት ቀን የሚሆን እንጀራ የሰጣችሁ ለዚህ ነው። በሰባተኛው ቀን እያንዳንዱ ሰው ባለበት ይቈይ፤ ማንም አይወጣም።” 30ስለዚህ ሕዝቡም በሰባተኛው ቀን ዐረፉ።

31የእስራኤልም ሕዝብ ምግቡን መና አሉት16፥31 መና ማለት፣ ምንድን ነው? ማለት ነው (15 ይመ)፤ እርሱም እንደ ድንብላል ዘር ነጭ፣ ጣሙም ከማር እንደ ተጋገረ ቂጣ ነበር። 32ሙሴም አለ፤ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘን ይህ ነው፤ ‘ከግብፅ ባወጣኋችሁ ጊዜ በምድረ በዳ እንድትበሉ የሰጠኋችሁን እንጀራ ያዩ ዘንድ አንድ ጎሞር መና ወስደህ ለሚመጡት ትውልዶች አቈየው።’ ”

33ስለዚህ ሙሴ አሮንን፣ “አንድ ማሰሮ ወስደህ አንድ ጎሞር መና አስቀምጥበት፤ ለሚመጡት ትውልዶች እንዲቈይም እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት አስቀምጠው” አለው።

34እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዳዘዘው አሮን፣ መናው ይጠበቅ ዘንድ በምስክሩ ፊት አስቀመጠው። 35እስራኤላውያን ወደ መኖሪያቸው ምድር እስኪመጡ ድረስ ለአርባ ዓመት መና በሉ፤ ወደ ከነዓን ድንበር እስከሚደርሱ ድረስ መና በሉ።

36አንድ ጎሞር የኢፍ መስፈሪያ አንድ ዐሥረኛ ነው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

出埃及記 16:1-36

天糧

1以色列全體會眾從以琳出發,來到以琳西奈中間的曠野,時值他們離開埃及後的第二個月的十五日。 2以色列全體會眾在曠野向摩西亞倫發怨言說: 3「我們還不如當初在埃及就死在耶和華手中。在那裡,我們至少可以圍在肉鍋旁吃個飽。現在,你把我們帶到曠野來,是要叫全體會眾餓死在這裡嗎?」

4耶和華對摩西說:「我要從天上降下食物給你們。百姓可以每天出去拾取他們當天所需的分量,這樣我就可以試驗他們是否遵行我的訓誨。 5到第六天,他們要比平時多拾取一倍,好夠兩天的分量。」 6摩西亞倫以色列百姓說:「今天晚上你們就知道把你們從埃及領出來的是耶和華。 7明天早上,你們會看見祂的榮耀,因為祂聽見了你們向祂所發的怨言。我們算什麼,你們何必埋怨我們? 8耶和華聽見你們發的怨言了,晚上祂必給你們肉吃,早晨再給你們餅吃。我們算什麼?你們埋怨的其實不是我們,而是耶和華。」 9摩西亞倫說:「你去叫以色列全體會眾到耶和華面前來,因為祂已聽見他們的怨言。」 10亞倫以色列全體會眾說話的時候,他們向曠野遠望,果然看見耶和華的榮光在雲彩中顯現。 11耶和華對摩西說: 12「我已經聽見以色列人的怨言。你告訴他們,『到了黃昏,你們就會有肉吃,早晨就會有餅可以吃飽,這樣你們就知道我是你們的上帝耶和華。』」

13到了黃昏,果然有許多鵪鶉飛來,把營地都遮蓋了。到了早晨,營區四周的地上佈滿露水, 14露水蒸發以後,曠野便出現一層薄薄的、像白霜的東西。 15以色列人見了,不知道是何物,便彼此議論說:「這是什麼?」摩西對他們說:「這就是耶和華給你們的食物。 16耶和華吩咐你們要按自己和家人的食量來拾取,每人約拾取兩升。」

17於是,以色列人遵命而行,有些拾的多,有些拾的少。 18後來,他們用俄梅珥16·18 俄梅珥」,量器,約「兩升」。量的時候,就發現多拾的沒有剩餘,少拾的也沒有缺乏,剛好是每人所需要的量。 19摩西又吩咐他們說:「你們所拾取的,不可留到早晨!」 20可是,有的人不聽,留了一些。到第二天早上,食物已腐爛生蟲,發出惡臭,摩西就向他們發怒。 21於是,百姓每天早晨出營拾取食物,各人按著所需分量拾取,到太陽升起後,食物就融化了。 22到第六天,他們就拾取雙倍的分量,也就是每人四升。會眾的首領來稟告摩西23摩西對他們說:「耶和華說,『明天是安息日,是向耶和華守的聖安息日。你們要把一切食物預備好,或烤或煮,吃剩的可以留到明天。』」 24百姓就照摩西的吩咐,把吃剩的食物留到第二天早晨,食物沒有發臭生蟲。 25摩西對他們說:「你們今天就吃這些吧,因為今天是耶和華的安息日,地上不會有食物讓你們拾取。 26你們有六天可以拾取食物,但第七天是安息日,沒有食物可以拾取。」 27到了第七天早晨,有些人仍然出去要拾取食物,結果什麼也找不到。 28耶和華對摩西說:「你們到什麼時候才肯遵行我的誡命和吩咐呢? 29要知道,耶和華已將安息日賜給你們,所以第六天我會賜你們雙倍的食物。第七天,人人都要留在營中,不許外出。」 30於是,百姓在第七天休息。

31以色列人稱這種食物為嗎哪,它形狀像芫荽的種子,白色,味道像用蜜糖製成的薄餅。 32摩西說:「以下是耶和華的吩咐,『把兩升的嗎哪存留起來,直到世世代代,以便你們的子子孫孫可以看見上帝帶你們離開埃及時在曠野賜給你們的食物。』」 33於是,摩西吩咐亞倫:「拿個罐子盛滿兩升的嗎哪,放在耶和華面前,留到世世代代。」 34亞倫便照耶和華給摩西的吩咐,把嗎哪放在約櫃前保存起來。 35以色列百姓就在曠野吃了四十年的嗎哪,直到他們到達有人煙的迦南為止。 36一俄梅珥等於十分之一伊法。