ዘዳግም 6 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 6:1-25

አምላክህን እግዚአብሔርን ውደድ

1ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ በምትወርሷት ምድር እንድትጠብቁት አስተምራችሁ ዘንድ አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሰጠኝ ትእዛዝ፣ ሥርዐትና ሕግ ይህ ነው፤ 2ይኸውም፣ የምሰጣችሁን ሥርዐቱንና ትእዛዙን ሁሉ በመጠበቅ፣ ዕድሜያችሁ እንዲረዝም፣ አንተ፣ ልጆችህና ከእነርሱ በኋላ የሚመጡት ልጆቻቸው በሕይወት ዘመናችሁ ሁሉ አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ትፈሩት ዘንድ ነው። 3እንግዲህ እስራኤል ሆይ ስማ፤ የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) በሰጠህ ተስፋ መሠረት፣ ማርና ወተት በምታፈስሰው ምድር መልካም እንዲሆንልህና እጅግ እንድትበዛ፣ ትእዛዙንም ትጠብቅ ዘንድ ጥንቃቄ አድርግ።

4እስራኤል ሆይ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) አንድ እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው6፥4 ወይም፣ እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤ እግዚአብሔር አንድ ነው ወይም እግዚአብሔር አምላካችን ነው፤ እግዚአብሔር ብቻውን5አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኀይልህ ውደድ። 6ዛሬ የምሰጥህን እነዚህን ትእዛዞች በልብህ ያዝ። 7ለልጆችህም አስጠናቸው፤ በቤትህ ስትቀመጥ፣ በመንገድም ስትሄድ፣ ስትተኛና ስትነሣም ስለ እነርሱ ተናገር። 8በእጅህ ላይ ምልክት አድርገህ እሰራቸው፤ በግንባርህም ላይ ይሁኑ። 9በቤትህ መቃኖች በግቢህም በሮች ላይ ጻፋቸው።

10አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ለአንተ ለመስጠት ለአባቶችህ ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ወደ ማለላቸው ምድር ሲያስገባህ፣ በዚያም ያልሠራሃቸውን ታላላቅና ያማሩ ከተሞችን፣ 11የራስህ ባልነበሩ መልካም ነገሮች ሁሉ የተሞሉ ቤቶችን፣ ያልቈፈርሃቸውን የውሃ ጕድጓዶች፣ ያልተከልሃቸውን የወይን ተክሎችና የወይራ ዛፎች ሲሰጥህና በልተህም ስትጠግብ፣ 12ከባርነት ምድር ከግብፅ ያወጣህን እግዚአብሔርን (ያህዌ) እንዳትረሳ ተጠንቀቅ!

13አምላክህን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) ፍራ፤ እርሱን ብቻ አገልግል፤ በስሙም ማል። 14በዙሪያህ ያሉ ሕዝቦች የሚያመልኳቸውን ሌሎች አማልክት አትከተል፤ 15ምክንያቱም በመካከልህ ያለው አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ቀናተኛ አምላክ (ኤሎሂም) ስለሆነ፣ በአንተም ላይ ቍጣው ስለሚነድድ፣ ከምድር ገጽ ያጠፋሃል። 16በማሳህ እንዳደረጋችሁት አምላካችሁን እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) አትፈታተኑት። 17አምላካችሁ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) የሰጣችሁን ትእዛዞች፣ መመሪያዎችና ሥርዐቶች በጥንቃቄ ጠብቁ። 18መልካም እንዲሆንልህና እግዚአብሔር (ያህዌ) ለአባቶችህ በመሐላ እንድትወርሳት፣ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ተስፋ የሰጣቸውን መልካሚቱን ምድር ገብተህ ቀናና መልካም የሆነውን አድርግ፤ 19እግዚአብሔር (ያህዌ) በተናገረው መሠረትም ጠላቶችህን ሁሉ ከፊትህ ታስወጣለህ። 20በሚመጡት ዘመናት ልጅህ፣ “አምላካችን እግዚአብሔር (ያህዌ ኤሎሂም) ያዘዛችሁ የመመሪያዎቹ፣ የሥርዐቶቹና የሕጎቹ ትርጕም ምንድን ነው?” ብሎ በሚጠይቅህ ጊዜ፣ 21እንዲህ በለው፤ “እኛ በግብፅ የፈርዖን ባሮች ነበርን፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን በብርቱ እጅ ከግብፅ አወጣን። 22እኛ በዐይናችን እያየን እግዚአብሔር (ያህዌ) ታላላቅና አስፈሪ የሆኑ ታምራዊ ምልክቶችና ድንቆችን በግብፅ፣ በፈርዖንና በመላው ቤተ ሰዎቹ ላይ አደረገ። 23እኛን ግን ለአባቶቻችን በመሐላ ተስፋ ወደ ሰጣቸው ምድር ሊያስገባንና ሊሰጠን ከዚያ አወጣን። 24ዛሬ እንደ ሆነው ሁሉ ምንጊዜም መልካም እንዲሆንልንና በሕይወት እንድንኖር ይህን ሥርዐት ሁሉ እንድንፈጽም፣ አምላካችንንም እግዚአብሔርን (ኤሎሂም ያህዌ) እንድንፈራ እግዚአብሔር (ያህዌ) አዘዘን። 25እንግዲህ ይህን ሁሉ ሕግ እርሱ ባዘዘን መሠረት፣ በአምላካችን በእግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ፊት ተጠንቅቀን ከጠበቅን፣ ያ ለእኛ ጽድቃችን ይሆናል።”

New International Reader’s Version

Deuteronomy 6:1-25

Love the Lord Your God

1The Lord your God has directed me to teach you his commands, rules and laws. Obey them in the land you will take over when you go across the Jordan River. 2Then you, your children and their children after them will honor the Lord your God as long as you live. Obey all his rules and commands I’m giving you. If you do, you will enjoy long life. 3Israel, listen to me. Make sure you obey me. Then things will go well with you. The number of your people will increase greatly in a land that has plenty of milk and honey. That’s what the Lord, the God of your parents, promised you.

4Israel, listen to me. The Lord is our God. The Lord is the one and only God. 5Love the Lord your God with all your heart and with all your soul. Love him with all your strength. 6The commandments I give you today must be in your hearts. 7Make sure your children learn them. Talk about them when you are at home. Talk about them when you walk along the road. Speak about them when you go to bed. And speak about them when you get up. 8Write them down and tie them on your hands as a reminder. Also tie them on your foreheads. 9Write them on the doorframes of your houses. Also write them on your gates.

10The Lord your God will bring you into the land of Canaan. He gave his word. He promised he would give the land to your fathers, to Abraham, Isaac and Jacob. The land has large, wealthy cities you didn’t build. 11It has houses filled with all kinds of good things you didn’t provide. The land has wells you didn’t dig. And it has vineyards and groves of olive trees you didn’t plant. You will have plenty to eat. 12But be careful that you don’t forget the Lord. Remember that he brought you out of Egypt. That’s the land where you were slaves.

13Worship the Lord your God. He is the only one you should serve. When you make promises, do so in his name. 14Don’t serve the gods of the nations around you. 15The Lord your God is among you. He wants you to worship only him. If you worship other gods, God will be very angry with you. And he will destroy you from the face of the land. 16Don’t test the Lord your God as you did at Massah. 17Be sure to obey the Lord’s commands. Obey the terms and rules he has given you. 18Do what is right and good in the Lord’s eyes. Then things will go well with you. You will go in and take over the land. It’s the good land the Lord promised to your people of long ago. 19You will drive out all your enemies to make room for you. That’s what the Lord said would happen.

20Later on, your child might ask you, “What is the meaning of the terms, rules and laws the Lord our God has commanded you to obey?” 21If they do ask you, tell them, “We were Pharaoh’s slaves in Egypt. But the Lord used his mighty hand to bring us out of Egypt. 22With our own eyes we saw the Lord send amazing signs. They were great and terrible. He sent them on Egypt and Pharaoh and everyone in his house. 23But the Lord brought us out of Egypt. He planned to bring us into the land of Canaan and give it to us. It’s the land he promised to our people of long ago. 24The Lord our God commanded us to obey all his rules. He commanded us to honor him. If we do, we will always succeed and be kept alive. That’s what is happening today. 25We must make sure we obey the whole law in the sight of the Lord our God. That’s what he has commanded us to do. If we obey his law, we’ll be doing what he requires of us.”