ዘዳግም 21 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዘዳግም 21:1-23

ገዳዩ ላልታወቀ ሰው ስለሚቀርብ ማስተስረያ

1አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እንድትወርሳት በሚሰጥህ ምድር አንድ ሰው ተገድሎ ሜዳ ላይ ቢገኝና ገዳዩም ማን እንደ ሆነ ባይታወቅ፣ 2ሽማግሌዎችህና ዳኞችህ ወጥተው ሬሳው ወድቆ ከተገኘበት ስፍራ አንሥቶ በአቅራቢያው እስካሉት ከተሞች ድረስ ያለውን ርቀት ይለኩ። 3ከዚያም ሬሳው ወድቆ ከተገኘበት ስፍራ በጣም ቅርብ የሆነችው ከተማ ሽማግሌዎች ለሥራ ያልደረሰችና ቀንበር ያልተጫነባትን ጊደር ይዘው፣ 4ከዚያ በፊት ታርሶ ወይም ተዘርቶበት ወደማይታወቅ ወራጅ ውሃ ወዳለበት ሸለቆ ያምጡት። በዚያ ሸለቆም የጊደሪቱን ዐንገት ይስበሩ፤ 5እንዲያገለግሉና በእግዚአብሔር (ያህዌ) ስም እንዲባርኩ፣ በማንኛውም የክርክርና የጥቃት ጕዳዮች ሁሉ ላይ ውሳኔ እንዲሰጡ፣ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) መርጧቸዋልና የሌዊ ልጆች ካህናቱ ወደ ፊት ይቅረቡ። 6ከዚያም ሬሳው በተገኘበት አቅራቢያ ባለችው ከተማ የሚኖሩ ሽማግሌዎች ሁሉ፣ በሸለቆው ውስጥ፣ ዐንገቷ በተሰበረው ጊደር ላይ እጃቸውን ይታጠቡ። 7እንዲህም ብለው ይናገሩ፤ “እጆቻችን ደም አላፈሰሱም፤ ድርጊቱ ሲፈጸምም ዐይኖቻችን አላዩም። 8እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ ስለ ተቤዠኸው ሕዝብህ ስለ እስራኤል ብለህ ይህን ስርየት ተቀበል፤ ሕዝብህንም በፈሰሰው ንጹሕ ደም በደለኛ አታድርግ።” ስለ ፈሰሰውም ደም ስርየት ይደረግላቸዋል። 9አንተም በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ቀና የሆነውን ስታደርግ፣ የንጹሑን ደም የማፍሰስ በደልን ከመካከልህ ታስወግዳለህ።

የተማረከች ሴት ስለ ማግባት

10ከጠላቶችህ ጋር ጦርነት ልትገጥም ወጥተህ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) እነርሱን በእጅህ አሳልፎ ሰጥቶህ በማረክህ ጊዜ፣ 11ከምርኮኞቹ መካከል መልከ መልካም ሴት አይተህ ብትማርክህ፣ ሚስትህ ልታደርጋት ትችላለህ። 12ወደ ቤትህ ውሰዳት፤ ጠጕሯን ትላጭ፤ ጥፍሯንም ትቍረጥ። 13ስትማረክ የለበሰችውንም ልብስ ታውልቅ፤ እቤትህ ተቀምጣ ለአባትና ለእናቷ ወር ሙሉ ካለቀሰችላቸው በኋላ፣ ልትደርስባትና ባል ልትሆናት፣ እርሷም ሚስት ልትሆንህ ትችላለች። 14በእርሷ ደስተኛ ባትሆን፣ ወደምትፈልገው እንድትሄድ ነጻነት ስጣት፤ ውርደት ላይ ጥለሃታልና ልትሸጣት ወይም እንደ ባሪያ ልትቈጥራት አይገባህም።

የበኵር ልጅ መብት

15አንድ ሰው ሁለት ሚስቶች ቢኖሩት፣ አንደኛዋን የሚወድዳት፣ ሌላዋን ግን የሚጠላት ቢሆን፣ ሁለቱም ወንዶች ልጆችን ወልደውለት በኵር ልጁ ግን የተወለደው ከማይወድዳት ሚስቱ ቢሆን፣ 16ንብረቱን ለልጆቹ በሚያወርስበት ጊዜ፣ የብኵርናን መብት ከማይወድዳት ሚስቱ ከወለደው በኵር ልጅ ገፎ፣ ከሚወድዳት ሚስቱ ለተወለደው ልጁ በአድልዎ መስጠት አይገባውም፤ 17ይልቁንም ከተጠላችው ሚስቱ ለተወለደው ልጅ ካለው ሀብት ሁሉ ሁለት እጅ ድርሻውን በመስጠት ብኵርናውን ያስታውቅ፤ ያ ልጅ የአባቱ ኀይል መጀመሪያ ነውና፣ የብኵርና መብት የራሱ ነው።

የማይታዘዝ ልጅ

18አንድ ሰው፣ የአባቱን ወይም የእናቱን ትእዛዝ የማይሰማ፣ ቢቀጡትም የማይታረም እልከኛና ዐመፀኛ ልጅ ቢኖረው፣ 19አባትና እናቱ ይዘው በሚኖሩበት ከተማ በር ወዳሉት አለቆች ያምጡት፤ 20“ይህ ልጃችን እልከኛና ዐመፀኛ ነው፤ አይታዘዘንም፤ አባካኝና ሰካራም ነው” ብለው ለአለቆች ይንገሯቸው። 21ከዚያም በኋላ የከተማዪቱ ሰዎች ሁሉ እስኪሞት ድረስ በድንጋይ ይውገሩት፤ ክፉውንም ከመካከልህ አስወግድ፤ እስራኤልም ሁሉ ይህን ሰምቶ ይፈራል።

ልዩ ልዩ ሕጎች

22አንድ ሰው ለሞት የሚያበቃ በደል ፈጽሞ ቢገደልና በድኑ በዕንጨት ላይ ቢሰቀል፣ 23በድኑን በዕንጨት ላይ እንደ ተሰቀለ አታሳድረው፤ ምክንያቱም በዕንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ዘንድ የተረገመ ነውና፤ አምላክህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም ያህዌ) ርስት አድርጎ የሚሰጥህን ምድር እንዳታረክስ፣ በዚያኑ ዕለት ቅበረው።

Thai New Contemporary Bible

เฉลยธรรมบัญญัติ 21:1-23

การลบบาปสำหรับการฆาตกรรมที่ไม่รู้ตัวผู้กระทำผิด

1เมื่อท่านเข้าสู่ดินแดนซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานเป็นกรรมสิทธิ์ หากพบศพกลางทุ่งและไม่ทราบว่าใครเป็นคนฆ่า 2ผู้อาวุโสและตุลาการของท่านจะวัดระยะจากศพไปยังเมืองที่ใกล้ที่สุด 3แล้วผู้อาวุโสของเมืองนั้นจะนำวัวสาวซึ่งไม่เคยเทียมแอก ไม่เคยถูกใช้งานมาก่อน 4ไปยังหุบเขาซึ่งไม่เคยมีการไถหว่านและมีธารน้ำไหล แล้วหักคอวัวที่นั่น 5ปุโรหิตชนเลวีจะก้าวไปข้างหน้า เพราะพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงเลือกปุโรหิตให้ปฏิบัติหน้าที่ ให้อวยพรในพระนามพระยาห์เวห์ และให้ตัดสินกรณีพิพาทและการทำร้ายร่างกาย 6บรรดาผู้อาวุโสของเมืองที่ใกล้ที่สุดนั้นจะล้างมือเหนือวัวซึ่งถูกหักคอในหุบเขา 7และประกาศว่า “มือของเราไม่ได้ทำให้หลั่งเลือด และตาของเราไม่ได้เห็นว่าใครทำ 8ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้าโปรดรับการลบมลทินบาปสำหรับอิสราเอลประชากรของพระองค์ซึ่งทรงไถ่ไว้แล้ว อย่าให้ประชากรของพระองค์ต้องรับโทษที่คนบริสุทธิ์ผู้นี้ถูกฆ่าตายเลย” แล้วความตายนี้จะได้รับการอภัยโทษบาป 9ท่านก็จะได้ช่วยให้ตัวเองพ้นโทษจากการที่คนบริสุทธิ์ต้องตาย เนื่องจากท่านได้ทำสิ่งที่ถูกต้องในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้า

การแต่งงานกับหญิงเชลย

10เมื่อท่านออกรบและพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านทรงมอบข้าศึกไว้ในมือของท่าน และท่านจับเขาเป็นเชลย 11หากท่านเห็นหญิงงามในหมู่เชลยซึ่งท่านชอบและอยากได้ไว้เป็นภรรยา 12จงพานางมาที่บ้านของท่าน ให้นางโกนผมและตัดเล็บ 13และเปลี่ยนเสื้อผ้าซึ่งสวมอยู่เมื่อถูกจับมาเป็นเชลย ให้นางอยู่ในบ้านของท่าน ไว้ทุกข์แก่บิดามารดาของนางหนึ่งเดือนเต็มๆ หลังจากนั้นท่านจึงรับนางมาเป็นภรรยา 14หากนางไม่ถูกใจท่าน จงปล่อยนางไปตามทางที่นางต้องการ อย่าขายหรือปฏิบัติกับนางเยี่ยงทาส เพราะท่านได้ทำให้นางอับอายแล้ว

สิทธิบุตรหัวปี

15หากชายใดมีภรรยาสองคน เขารักคนหนึ่งและไม่รักอีกคนหนึ่ง และทั้งสองให้กำเนิดบุตรชายแก่เขา แต่บุตรหัวปีเป็นบุตรของภรรยาที่เขาไม่รัก 16เมื่อเขาแบ่งทรัพย์สินให้บุตรชายของเขา เขาจะต้องไม่ให้สิทธิบุตรหัวปีแก่บุตรชายที่เกิดจากภรรยาที่เขารักแทนบุตรชายหัวปีจริงๆ ที่เกิดจากภรรยาที่เขาไม่รัก 17เขาต้องยอมรับบุตรของภรรยาที่เขาไม่รักเป็นบุตรหัวปีโดยยกทรัพย์สินให้แก่บุตรหัวปีเป็นสองเท่า บุตรนี้เป็นเครื่องหมายแรกแห่งกำลังของบิดาของเขา สิทธิบุตรหัวปีเป็นของเขา

บุตรดื้อดึง

18หากคนใดมีบุตรชายที่ดื้อดึงหัวแข็ง ไม่อยู่ในโอวาทไม่ยอมเชื่อฟังบิดามารดา แม้ถูกตีสั่งสอนก็แล้ว 19ให้บิดามารดานำตัวบุตรนั้นมาพบผู้อาวุโสของเมืองนั้นที่ประตูเมือง 20เขาจะแจ้งผู้อาวุโสว่า “ลูกคนนี้ดื้อรั้นหัวแข็ง ไม่เชื่อฟัง ชอบสำมะเลเทเมา” 21แล้วชาวเมืองนั้นจะเอาหินขว้างเขาให้ตาย ท่านต้องขจัดความชั่วร้ายออกไปจากหมู่พวกท่าน ชนอิสราเอลทั้งปวงจะได้ยินเหตุการณ์ที่เกิดขึ้นแล้วเกรงกลัว

กฎอื่นๆ

22ผู้ใดทำความผิดที่มีโทษถึงตาย เมื่อถูกประหารแขวนศพไว้บนต้นไม้ 23อย่าปล่อยให้ศพค้างอยู่บนต้นไม้ข้ามคืน จงฝังในวันนั้น เพราะคนที่ถูกแขวนไว้ที่ต้นไม้นั้นถูกพระเจ้าสาปแช่ง อย่าทำให้แผ่นดินที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานแก่ท่านเป็นกรรมสิทธิ์นั้นเป็นมลทิน