ዘኍል 1 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘኍል 1:1-54

የሕዝብ ቈጠራ

1እስራኤላውያን ከግብፅ በወጡ በሁለተኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር፣ በመጀመሪያው ቀን በሲና ምድረ በዳ ሳሉ እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ተናገረው፤ እንዲህም አለው፤ 2“የወንዶቹን ስም አንድ በአንድ በመዘርዘር መላውን የእስራኤል ማኅበረ ሰብ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው ቍጠሯቸው። 3በመላው እስራኤል ያሉትን ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያም በላይ ሆኖ ለውጊያ ብቁ የሆኑትን ወንዶች ሁሉ አንተና አሮን በየምድባቸው ቍጠሯቸው። 4ከየነገዱ የአባቶች ቤት ተጠሪ የሆነ አንድ ሰው ከእናንተ ጋር ይሁን።

5“የሚረዷችሁም ሰዎች ስም የሚከተለው ነው፤

“ከሮቤል የሰዲዮር ልጅ ኤሊሱር፤

6ከስምዖን የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል፤

7ከይሁዳ የአሚናዳብ ልጅ ነአሶን፤

8ከይሳኮር የሶገር ልጅ ናትናኤል፤

9ከዛብሎን የኬሎን ልጅ ኤልያብ፤

10ከዮሴፍ ልጆች ከኤፍሬም የዓሚሁድ ልጅ ኤሊሳማ፤

ከምናሴ የፍዳሱር ልጅ ገማልኤል፤

11ከብንያም የጋዴዮን ልጅ አቢዳን፤

12ከዳን የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር፤

13ከአሴር የኤክራን ልጅ ፋግኤል፤

14ከጋድ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ፤

15ከንፍታሌም የዔናን ልጅ አኪሬ።”

16እነዚህ ከማኅበረ ሰቡ የተመረጡ የየነገዱ አለቆች ሲሆኑ እነርሱም የእስራኤል ጐሣዎች መሪዎች ነበሩ።

17ሙሴና አሮን ስማቸው የተጠቀሰውን እነዚህን ሰዎች ወሰዱ፤ 18ከዚያም በሁለተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ማኅበረ ሰቡን በሙሉ በአንድነት ሰበሰቧቸው። የተሰበሰቡትም በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው የትውልድ ሐረጋቸውን ተናገሩ፤ 19እግዚአብሔር ሙሴን ባዘዘው መሠረት ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ የሆነ ወንዶች ስማቸው አንድ በአንድ ተመዘገበ። እንዲህ አድርጎም በሲና ምድረ በዳ ቈጠራቸው።

20ከእስራኤል የበኵር ልጅ ከሮቤል ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያ በላይ ሆኖ በሰራዊቱ ውስጥ ለማገልገል ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 21ከሮቤል ነገድ የተቈጠሩት አርባ ስድስት ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

22ከስምዖን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 23ከስምዖን ነገድ የተቈጠሩት አምሳ ዘጠኝ ሺሕ ሦስት መቶ ነበሩ።

24ከጋድ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 25ከጋድ ነገድ የተቈጠሩትም አርባ አምስት ሺሕ ስድስት መቶ አምሳ ነበሩ።

26ከይሁዳ ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 27ከይሁዳ ነገድ የተቈጠሩትም ሰባ አራት ሺሕ ስድስት መቶ ነበሩ።

28ከይሳኮር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 29ከይሳኮር ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ አራት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

30ከዛብሎን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 31ከዛብሎን ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሰባት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

32ከዮሴፍ ልጆች፦

ከኤፍሬም ዝርያ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 33ከኤፍሬም ነገድ የተቈጠሩትም አርባ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

34ከምናሴ ዝርያዎች፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 35ከምናሴ ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ ሁለት ሺሕ ሁለት መቶ ነበሩ።

36ከብንያም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ፤ 37ከብንያም ነገድ የተቈጠሩትም ሠላሳ አምስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

38ከዳን ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 39ከዳን ነገድ የተቈጠሩትም ስድሳ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ነበሩ።

40ከአሴር ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 41ከአሴር ነገድ የተቈጠሩት አርባ አንድ ሺሕ አምስት መቶ ነበሩ።

42ከንፍታሌም ዝርያ፦

ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ። 43ከንፍታሌም ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሦስት ሺሕ አራት መቶ ነበሩ።

44በሙሴና በአሮን፣ እያንዳንዳቸውም ቤተ ሰባቸውን በወከሉት በዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል አለቆች የተቈጠሩት ወንዶች እነዚህ ናቸው። 45ስለዚህ እስራኤላውያን ሁሉ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ በእስራኤል ሰራዊት ውስጥ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት በየቤተ ሰባቸው ተቈጠሩ፤ 46ጠቅላላ ቍጥራቸውም ስድስት መቶ ሦስት ሺሕ አምስት መቶ አምሳ ነበር።

47የሌዊ ነገድ ቤተ ሰቦች ግን ከሌሎች ጋር አብረው አልተቈጠሩም፤ 48እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ ብሎት ነበርና፤ 49“የሌዊን ነገድ አትቍጠር፤ በእስራኤላውያንም ቈጠራ ውስጥ አታስገባው፤ 50በዚህ ፈንታ ሌዋውያንን በምስክሩ ማደሪያ፣ በውስጡ ባሉት በመገልገያ ዕቃዎች ሁሉ እንዲሁም ከዚሁ ጋር በተያያዙ በማናቸውም ነገሮች ላይ ኀላፊዎች ይሁኑ፤ ማደሪያውንና በውስጡ ያሉትን የመገልገያ ዕቃዎች ይሸከሙ፤ በውስጡ ያገልግሉ፤ ድንኳናቸውንም በዙሪያው ይትከሉ። 51ማደሪያው በሚነሣበት ጊዜ ሌዋውያን ይንቀሉት፤ ማደሪያው በሚተከልበትም ጊዜ ሌዋውያን ያቁሙት፤ ሌላ ሰው ቢቀርብ ግን ይገደል። 52እስራኤላውያን በየምድባቸው ድንኳናቸውን ይትከሉ፤ እያንዳንዱም ሰው በየሰፈሩና በየዐርማው ሥር ይስፈር። 53ሌዋውያን ግን በእስራኤላውያን ማኅበረ ሰብ ላይ ቍጣ እንዳይወርድ ድንኳኖቻቸውን በምስክሩ ማደሪያ ዙሪያ ይትከሉ፤ የምስክሩ ማደሪያ ድንኳን ኀላፊዎች ሌዋውያን ናቸው።”

54እስራኤላውያንም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ይህን ሁሉ አደረጉ።

Swedish Contemporary Bible

4 Moseboken 1:1-54

Förberedelser för vandringen

(1:1—10:10)

Den första folkräkningen

(26:1-51)

Gud ger order om en folkräkning

1Den första dagen i andra månaden året efter det att israeliterna lämnat Egypten och kommit till Sinais öken, talade Herren till Mose i uppenbarelsetältet:

2”Räkna hela Israels menighet, alla män i varje stam och familj, varje namn för sig. 3Du och Aron ska mönstra alla vapenföra Israels män från tjugo år och uppåt, häravdelning för häravdelning. 4En man från varje stam, ett familjeöverhuvud, ska hjälpa er. 5Här är namnen på männen som ska hjälpa er:

från Rubens stam Elisur, Shedeurs son,

6från Simons Shelumiel, Surishaddajs son,

7från Judas Nachshon, Amminadavs son,

8från Isaskars Netanel, Suars son,

9från Sebulons Eliav, Helons son,

10från Efraims (Josefs son) Elishama, Ammihuds son,

från Manasse (Josefs son) Gamliel, Pedasurs son,

11från Benjamins Avidan, Gidonis son,

12från Dans Achieser, Ammishaddajs son,

13från Ashers Pagiel, Okrans son,

14från Gads Eljasaf, Deguels son,

15från Naftalis stam Achira, Enans son.”

16Dessa män var utsedda av menigheten och var ledare för sina fäders stammar, de var Israels stamhövdingar.

17Mose och Aron tog dessa namngivna män 18och sammankallade hela menigheten på första dagen i andra månaden. Folket infördes i förteckningen efter sina släkter och familjer, varje namn för sig, alla män från tjugo år och uppåt 19som Herren hade befallt Mose. Så mönstrade han dem i Sinaiöknen.

20Av Rubens, Israels förstföddes, stam upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 21Av Rubens stam mönstrades 46 500 man.

22Av Simons ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 23Av Simons stam mönstrades 59 300 man.

24Av Gads ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 25Av Gads stam mönstrades 45 650 man.

26Av Judas ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 27Av Judas stam mönstrades 74 600 man.

28Av Isaskars ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 29Av Isaskars stam mönstrades 54 400 man.

30Av Sebulons ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 31Av Sebulons stam mönstrades 57 400 man.

32Av Efraims, Josefs sons, ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 33Av Efraims stam mönstrades 40 500 man.

34Av Manasses, Josefs sons, ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 35Av Manasses stam mönstrades 32 200 man.

36Av Benjamins ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 37Av Benjamins stam inmönstrades 35 400 man.

38Av Dans ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 39Av Dans stam mönstrades 62 700 man.

40Av Ashers ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 41Av Ashers stam mönstrades 41 500 man.

42Av Naftalis ättlingar upptecknades släkt för släkt, familj för familj, namn för namn alla vapenföra män från tjugo år och uppåt. 43Av Naftalis stam mönstrades 53 400 man.

44Dessa mönstrades av Mose och Aron och Israels hövdingar, tolv män som representerade var sin stamfamilj. 45Alla vapenföra israeliter från tjugo år och uppåt mönstrades alltså familjevis. 46Sammanlagt räknades 603 550 stridsdugliga män vid mönstringen.

47Leviternas fädernestam räknades dock inte i mönstringen tillsammans med de andra. 48Herren talade nämligen till Mose: 49”Du ska inte räkna Levis stam i mönstringen av israeliterna. 50Du ska ge dem i uppdrag att bära förbundstecknets boning och utföra allt som hör samman med den och alla dess redskap och sköta om dem. De måste bo nära tältet 51och när det ska flyttas är det leviternas sak att ta ner det och att sätta upp det igen vid nästa lägerplats. Om någon annan kommer nära det ska han dödas. 52Varje israelit ska slå läger tillsammans och under eget banér, efter sina häravdelningar. 53Leviternas tält ska slås upp runt förbundstecknets boning för att Guds vrede inte ska komma över Israels meninghet. Leviterna är ansvariga för den och dess skötsel.”

54Alla dessa befallningar som Herren hade gett Mose efterföljdes av israeliterna.