ዘሌዋውያን 27 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 27:1-34

ስለ ስጦታ የወጣ ሕግ

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ማንኛውም ሰው ተመጣጣኙን ዋጋ በመክፈል ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ሰውን ለመስጠት የተለየ ስእለት ቢሳል፣ 3ዕድሜው ከሃያ እስከ ስድሳ ዓመት ለሆነ ወንድ፣ በቤተ መቅደሱ ሰቅል27፥3 0.6 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 16 ይመ ሚዛን መሠረት፣ ግምቱ አምሳ ጥሬ ሰቅል27፥3 11.5 ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 25 ይመ ብር ይሁን። 4ለሴት ከሆነ ግምቱ ሠላሳ ሰቅል27፥4 0.3 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል ይሁን። 5ዕድሜው ከአምስት እስከ ሃያ ዓመት ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ ሃያ ሰቅል፣27፥5 0.2 ኪሎ ግራም ገደማ ይሆናል ሴት ከሆነች ግምቷ ዐሥር ሰቅል27፥5 110 ግራም ገደማ ይሆናል፤ እንዲሁም 7 ይመ ይሁን። 6ዕድሜው ከአንድ ወር እስከ አምስት ዓመት ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ አምስት ሰቅል27፥6 55 ግራም ገደማ ይሆናል ጥሬ ብር፣ ለሴት ከሆነ ሦስት ሰቅል27፥6 35 ግራም ገደማ ይሆናል ጥሬ ብር ይሁን። 7ስድሳ ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ለሆነ ሰው፣ ወንድ ከሆነ ግምቱ ዐሥራ አምስት ሰቅል፣ ሴት ከሆነች ዐሥር ሰቅል ይሁን። 8ስእለት የተሳለው ድኻ ከሆነና ግምቱን መክፈል ካልቻለ ግን፣ ለስጦታ ያሰበውን ሰው ወደ ካህኑ ያምጣ፤ ካህኑም የተሳለው ሰው ባለው ዐቅም መሠረት መክፈል የሚገባውን ይተምንለታል።

9“ ‘ሰውየው የተሳለው ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት ሆኖ መቅረብ የሚችል እንስሳ ከሆነ፣ እንዲህ ያለው ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተሰጠ እንስሳ የተቀደሰ ይሆናል። 10ሰውየው መልካም የሆነውን እንስሳ መልካም ባልሆነው፣ መልካም ያልሆነውንም መልካም በሆነው አይለውጥ ወይም አይተካ፤ አንዱን እንስሳ በሌላው ከተካም ሁለቱ የተቀደሱ ይሆናሉ። 11እንስሳው በሥርዐቱ መሠረት የረከሰ፣ ለእግዚአብሔርም (ያህዌ) መሥዋዕት ሆኖ መቅረብ የማይገባው ከሆነ፣ ሰውየው እንስሳውን ወደ ካህኑ ያቅርብ፤ 12መልካም ቢሆን ወይም ባይሆን፣ ካህኑ ዋጋውን ይወስን፤ የካህኑም ውሳኔ የጸና ይሆናል። 13ባለቤቱ እንስሳውን መዋጀት ከፈለገ ግን፣ በተተመነው ዋጋ ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት።

14“ ‘አንድ ሰው ቤቱን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ይሆን ዘንድ ቢቀድስ፣ መልካም ቢሆን ወይም ባይሆን ካህኑ ዋጋውን ይተምን፤ ካህኑም የተመነው ዋጋ የጸና ይሆናል። 15ቤቱን የቀደሰው ሰው መልሶ ሊዋጀው ከፈለገ ግን፣ የዋጋውን አንድ አምስተኛ በዋጋው ላይ መጨመር አለበት፤ ቤቱም ዳግመኛ የራሱ ይሆናል።

16“ ‘አንድ ሰው ከወረሰው ርስት ላይ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የዕርሻ መሬት ቢቀድስ፣ ዋጋው የሚተመነው ለመሬቱ በሚያስፈልገው ዘር መጠን ይሆናል፤ ይኸውም ለአንድ ሆሜር27፥16 220 ሊትር ገደማ ይሆናል መስፈሪያ የገብስ ዘር አምሳ ሰቅል ጥሬ ብር ነው። 17ሰውየው ዕርሻውን የቀደሰው በኢዮቤልዩ ዓመት ከሆነ፣ የተወሰነው ዋጋ አይለወጥም። 18ዕርሻውን የሚቀድሰው ከኢዮቤልዩ በኋላ ከሆነ ግን፣ ካህኑ ዋጋውን የሚተምነው እስከሚመጣው የኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ባሉት ዓመታት ቍጥር ልክ ነው፤ የተተመነውም ዋጋ ይቀነሳል። 19ዕርሻውን የቀደሰው ሰው መልሶ መዋጀት ከፈለገ፣ በዋጋው ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት፤ ከዚያ በኋላ ዕርሻው እንደ ገና የራሱ ይሆናል። 20ዕርሻውን ባይዋጅ ወይም ለሌላ ሰው አሳልፎ ቢሸጥ፣ ከዚያ በኋላ ሊዋጀው አይችልም። 21ዕርሻው በኢዮቤልዩ በሚለቀቅበት ጊዜ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) እንደ ተሰጠ ዕርሻ ተቈጥሮ ቅዱስና የካህናቱ27፥21 ወይም የካህኑ ንብረት ይሆናል።

22“ ‘አንድ ሰው የወረሰው ርስት ያልሆነውን፣ በገንዘቡ የገዛውን የዕርሻ መሬት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ቢቀድስ፣ 23ካህኑ የዕርሻውን መሬት ዋጋ እስከ ኢዮቤልዩ ዓመት ድረስ ባለው ጊዜ መጠን ይተምናል፤ ሰውየው የተተመነውን ዋጋ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ አድርጎ በዚያኑ ዕለት ይክፈል። 24በኢዮቤልዩ ዓመትም የዕርሻው መሬት የቀድሞው ባለ ርስት ለነበረው፣ ለሸጠውም ሰው ይመለሳል። 25እያንዳንዱ ዋጋ የሚተመነው በቤተ መቅደሱ ሰቅል ልክ ሆኖ አንዱ ሰቅል ሃያ ጌራ ነው።

26“ ‘የእንስሳት በኵር ቀድሞውኑ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ስለሆነ፣ ማንም ሰው የእንስሳትን በኵር ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መቀደስ አይችልም፤ በሬም27፥26 የዕብራይስጡ ቃል ተባዕትና እንስትን ሊያጠቃልል ይችላል ሆነ በግ የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነውና። 27እንስሳው ርኩስ ከሆነ ግን፣ ባለቤቱ በተተመነው ዋጋ ላይ አንድ አምስተኛ ጨምሮ ሊዋጀው ይችላል፤ የማይዋጀው ከሆነ ግን በተተመነው ዋጋ ይሸጥ።

28“ ‘ነገር ግን ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ተለይቶ የተሰጠ27፥28 የዕብራይስጡ አገላለጽ አንድን ነገር ወይም ሰውን እንደማይመለስ ሆኖ ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል። ማንኛውም ነገር፦ ሰውም ሆነ እንስሳ ወይም በውርስ የተገኘ መሬት አይሸጥም፤ አይዋጅምም። ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተሰጠ ማንኛውም ነገር እጅግ የተቀደሰ ነውና።

29“ ‘እንዲጠፋ የተወሰነ ማንኛውም ሰው አይዋጅም፤27፥29 የዕብራይስጡ አገላለጽ አንድን ነገር ወይም ሰውን ሙሉ በሙሉ በማስወገድ እንደማይመለስ ሆኖ ለእግዚአብሔር መስጠትን ያመለክታል መገደል አለበት።

30“ ‘ከዕርሻ ምርትም ሆነ ከዛፍ ፍሬ፣ ማንኛውም ከምድሪቱ የሚገኝ ዐሥራት የእግዚአብሔር (ያህዌ) ነው፤ ለእግዚአብሔርም (ያህዌ) የተቀደሰ ነው። 31አንድ ሰው ከዐሥራቱ የትኛውንም መዋጀት ቢፈልግ፣ በዋጋው ላይ አንድ አምስተኛ መጨመር አለበት። 32ከቀንድ ከብቶች፣ ከበጎችና ከፍየሎች መንጋ የሚወጣው ዐሥራት ከእረኛ በትር በታች ከሚያልፉት ዐሥረኛው እንስሳ ይሆናል፤ ይህም ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የተቀደሰ ነው። 33ሰውየው መልካም የሆነውን መልካም ካልሆነው አይለይ ወይም አይተካ፤ አንዱን በሌላው ቢተካ ግን ሁለቱም እንስሳት የተቀደሱ ይሆናሉ፤ ሊዋጁም አይችሉም።’ ”

34እግዚአብሔር (ያህዌ) በሲና ተራራ ላይ በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል ሕዝብ የሰጣቸው ትእዛዞች እነዚህ ናቸው።

Swedish Contemporary Bible

3 Moseboken 27:1-34

Ersättning till Herren

1Herren talade till Mose: 2”Säg till israeliterna att när någon genom ett särskilt löfte bestämts för tjänst inför Herren27:2 En person kunde skänkas till livslång tjänst inför Herren i helgedomen (se 1 Sam 1:11,28); dock fick endast leviterna tjänstgöra där. Här tycks det således vara frågan om lösesumman för en icke-levit som inte kunde tjänstgöra i helgedomen., kan detta värderas enligt följande: 3För en man i åldern 20 till 60 år gäller 50 siklar27:3 1 sikel=12 gram. silver enligt tempelsikeln. 4För en kvinna gäller 30 siklar. 5För en pojke mellan 5 och 20 år gäller 20 siklar och för en flicka 10. 6För en pojke i åldern från en månad upp till 5 år gäller 5 siklar och för en flicka 3 siklar. 7För en man över 60 år gäller 15 och för en kvinna 10 siklar. 8Men om någon är alltför fattig att betala den fastställda summan ska han föras till prästen och prästen ska bestämma värdet efter hans betalningsförmåga, vad han ska betala som har avlagt löftet.

9Om det är ett djur som blivit lovat till Herren och som är acceptabelt som ett offer, är det heligt. 10Man får inte byta ut det eller ersätta gott med dåligt eller dåligt med gott. Om han gör det, är både det första och det andra djuret heligt. 11Men om djuret är orent och inte tillåtet för offer åt Herren, ska det föras till prästen 12och prästen ska värdera det, hur bra eller dåligt det är och det värdet ska sedan gälla. 13Om mannen vill lösa in det, ska han öka dess värde med tjugo procent.

14Om någon vill helga sitt hus åt Herren, ska prästen fastställa dess värde utifrån hur bra eller dåligt det är och det värdet ska sedan gälla. 15Vill den som helgat sitt hus sedan köpa det tillbaka, ska värdet ökas med tjugo procent för att det åter ska bli hans.

16Om en man helgar ett stycke av familjens åkermark till Herren, ska det värderas i förhållande till den mängd utsäde som krävs för att beså det. En åker som kräver 220 liter korn för att besås värderas till 50 siklar silver. 17För den som överlämnar sin åker under friåret ska det värdet bestå. 18Men om det sker efter friåret, ska prästen bestämma värdet i förhållande till det antal år som är kvar till nästa friår och minska värdet utifrån det. 19Om han som helgat åkern vill köpa tillbaka den, ska värdet ökas med tjugo procent och så ska åkern bli hans igen.

20Men om han inte löser in åkern eller om han har sålt åkern till någon annan, får den inte mer återköpas. 21När den blir fri på friåret, blir den helig som en åker vigd åt Herren och den ska ges till prästen.

22Om en man vill helga åt Herren en köpt åker som inte är en del av hans familjeegendom, 23ska prästen uppskatta värdet på den fram till friåret. Mannen ska samma dag ge det fastställda värdet som är helgat åt Herren 24och vid friåret ska åkern lämnas tillbaka till den ursprunglige ägaren vars egendom den var. 25Alla värden ska fastställas efter tempelsikel. En sikel är 20 gera.

26Ingen får helga det förstfödda från boskapen åt Herren, vare sig det är en oxe, ett får eller en get, för det är redan hans. 27Men om det är ett orent djur, ska det friköpas efter det fastställda värdet plus tjugo procent. Om det inte löses tillbaka ska det säljas efter det fastställda värdet. 28Men allt sådant som är vigt åt Herren, något som en man har vigt åt honom av sin egendom – människor, djur eller ärvd mark, ska inte säljas eller återlösas, för det är högheligt inför Herren.

29En människa som vigts åt förintelse får aldrig friköpas. Han måste dö.

30En tiondel av landets alla produkter, vare sig det gäller säd eller frukt, är avskilda och helgade åt Herren. 31Om någon skulle vilja lösa in sitt tionde, måste han lägga tjugo procent till dess värde. 32Vart tionde djur tillhör också Herren både bland nötkreatur och all den småboskap som era herdar räknar in; vart tionde av dem är helgat åt Herren. 33Det ska inte väljas efter vad som är gott eller dåligt och får inte ersättas med något. Om man byter ut ett djur, ska både det ursprungliga djuret och det som valts i dess ställe tillhöra Herren och inte kunna köpas tillbaka.”

34Det här är de bud för Israels folk som Herren gav Mose på Sinai berg.