ዕዝራ 9 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 9:1-15

ከባዕዳን ጋር ስለ ተደረገው ጋብቻ የዕዝራ ጸሎት

1እነዚህ ነገሮች ከተፈጸሙ በኋላ መሪዎቹ ወደ እኔ መጥተው እንዲህ አሉኝ፤ “ካህናቱንና ሌዋውያኑን ጨምሮ የእስራኤል ሕዝብ ከጎረቤቶቻቸው ከከነዓናውያን፣ ከኬጢያውያን፣ ከፌርዛውያን፣ ከኢያቡሳውያን፣ ከአሞናውያን ርኩሰት ራሳቸውን አልለዩም። 2ሴቶቻቸውን ለራሳቸውና ለልጆቻቸው ሚስት አድርገው ወስደዋል፤ የተቀደሰውንም ዘር ከምድር ሕዝቦች ጋር ደባልቀዋል፤ በዚህ በደል ዋነኛ የሆኑትም መሪዎቹና ሹማምቱ ናቸው።”

3እኔም ይህን በሰማሁ ጊዜ፣ መጐናጸፊያዬንና ካባዬን ቀደድሁ፤ የራሴን ጠጕርና ጢሜን ነጨሁ፤ እጅግ ደንግጬም ተቀመጥሁ። 4በደል ከፈጸሙት ምርኮኞች የተነሣም በእስራኤል አምላክ ቃል የተንቀጠቀጡት ሁሉ በዙሪያዬ ተሰበሰቡ፤ እኔም እስከ ሠርክ መሥዋዕት ድረስ እጅግ እንደ ደነገጥሁ በዚያው ተቀመጥሁ።

5ከዚያም፣ የሠርክ መሥዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ፣ የተቀደደውን መጐናጸፊያዬንና ካባዬን እንደ ለበስሁ በሐዘን ከተቀመጥሁበት ተነሣሁ፤ በጕልበቴም ተንበርክኬ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር እጆቼን በመዘርጋት፣ 6እንዲህ ስል ጸለይሁ፤

“አምላኬ ሆይ፤ ኀጢአታችን ከራሳችን በላይ ሆኗል፤ በደላችንም እስከ ሰማያት ደርሷል፤ አምላኬ ሆይ፤ ፊቴን ወደ አንተ ቀና ለማድረግ ፈራሁ፤ እጅግም ፈራሁ። 7ከአባቶቻችን ዘመን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በደላችን ታላቅ ነው። ከኀጢአታችንም የተነሣ፣ ዛሬ እንደ ሆነው ሁሉ እኛም ሆንን፣ ነገሥታቶቻችንና ካህናቶቻችን በባዕዳን ነገሥታት እጅ ወድቀን ለሰይፍ፣ ለምርኮ፣ ለብዝበዛና ለውርደት ተዳርገናል።

8“አሁን ግን እግዚአብሔር አምላካችን ቅሬታ ይተውልን ዘንድ፣ በመቅደሱም ውስጥ ጽኑ ስፍራ ይሰጠን ዘንድ፣ ለጥቂት ጊዜ ቸርነቱን አሳይቶናል፤ ስለዚህ አምላካችን ለዐይናችን ብርሃን ሰጠን፤ በባርነትም ሳለን ለጥቂት ጊዜ ዕረፍት ሰጠን። 9ባሮች ብንሆንም፣ አምላካችን ግን ባሮች ሆነን እንድንቀር አልተወንም፤ ነገር ግን በፋርስ ነገሥታት ፊት ቸርነቱን አሳየን፤ የአምላካችንን ቤት እንደ ገና እንድንሠራና ፍርስራሾቿን እንድንጠግን አዲስ ሕይወት ሰጠን፤ በይሁዳና በኢየሩሳሌምም የመከላከያ ቅጥር ሰጠን።

10“አሁን ግን አምላካችን ሆይ፤ ከዚህ በኋላ ምን እንላለን? ትእዛዞችህን አቃልለናልና፤ 11ያቃለልነውም በባሮችህ በነቢያት አማካይነት፣ ‘ለመውረስ የምትገቡባት ምድር በሕዝቦቿ ርኩሰት ተበክላለች፤ ከዳር እስከ ዳርም በአጸያፊ ድርጊታቸውና በርኩሰታቸው ተሞልታለች፤ 12ስለዚህ ሴቶች ልጆቻችሁን ለወንዶች ልጆቻቸው አትስጡ፤ ሴቶች ልጆቻቸውንም ለወንዶች ልጆቻችሁ አትውሰዱ። ብርቱዎች እንድትሆኑ፣ የምድሪቱን መልካም ነገር እንድትበሉና ለልጆቻችሁም የዘላለም ርስት እንድታወርሱ ከእነርሱ ጋር ምንም ዐይነት ውል አታድርጉ’ ብለህ የሰጠኸውን ትእዛዝ ነው።

13“ይህ ሁሉ የደረሰብን በክፉ ሥራችንና በብዙ በደላችን ምክንያት ነው፤ አምላካችን ሆይ፤ አንተ ግን እንደ በደላችን ብዛት አልቀጣኸንም፤ ይልቁንም ቅሬታን ተውህልን። 14ታዲያ ትእዛዞችህን እንደ ገና ተላልፈን እንዲህ ያለውን አስጸያፊ ድርጊት ከሚፈጽሙ ሕዝቦች ጋር መጋባት ተገቢ ነውን? አንተስ ቅሬታ እስከማይኖር ወይም አንድም ሰው እስከማይድን ድረስ ተቈጥተህ አታጠፋንምን? 15የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ እኛም በዚህ ዕለት ተርፈን በሕይወት አለን። እነሆ፣ በፊትህ ከነበደላችን ቀርበናል፤ ከበደላችን የተነሣ ግን በፊትህ ሊቆም የሚችል ማንም የለም።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以斯拉记 9:1-15

以斯拉的祷告

1这些事以后,众首领来告诉我说:“以色列民众、祭司和利未人还没有与当地各族分开,他们仍随从迦南人、人、比利洗人、耶布斯人、亚扪人、摩押人、埃及人和亚摩利人的可憎行为。 2他们为自己和自己的儿子娶这些人的女儿为妻,使圣洁的民族与当地的人混杂。首领和官员是这种不忠之事的罪魁。” 3一听到这些,我便撕裂衣服和外袍,拔掉头发和胡须,惊惧地坐下。 4听了以色列上帝的话而战抖的人都聚集在我周围,因为流亡归来的人不忠。我惊惧地坐在那里,直到献晚祭的时候。

5献晚祭的时候,我满怀忧伤地起来,穿着那撕裂的衣服和外袍,双膝跪下,向我的上帝耶和华伸出双手, 6说:“我的上帝啊,我羞愧难当,不敢抬头看你,因为我们的恶行灭顶,我们的罪恶滔天。 7从我们的祖先开始到现在,我们罪恶深重。由于我们的罪恶,我们、我们的君王和祭司都落在外邦君王的手中,被他们杀害、俘虏、抢掠和羞辱,如同今天的光景。 8但如今我们的上帝耶和华暂且施恩于我们,为我们存留一些余民,使我们安然住在这圣洁之地。你使我们眼睛明亮,在我们受奴役时赐给我们一点生机。 9虽然我们是奴隶,我们的上帝却没有离弃受奴役的我们,祂在波斯众王面前施恩于我们,使我们复兴、得以重建毁坏的上帝的殿,让我们在犹大耶路撒冷有护墙。

10“如今,我们的上帝啊,事已至此,我们还能说什么呢?因为我们背弃了你的诫命, 11就是你借着你的仆人——众先知给我们的吩咐,‘你们将要占领的那片土地被当地人的污秽玷污,他们的可憎行径使那里充满污秽。 12所以不要让你们的女儿嫁给他们的儿子,也不要让你们的儿子娶他们的女儿。永不可为他们谋求平安和好处。这样,你们就可强盛,吃那里的美好出产,也可将那地方留给你们的子孙作为永久的产业。’

13“虽然因为我们的恶行和大罪,这一切事情临到我们,但我们的上帝啊,你给我们的惩罚比我们该受的轻多了,你还施恩给我们留下这些余民。 14我们岂能再违背你的诫命,与这些行为可憎的人通婚?若我们这样行,你岂不发怒毁灭我们,使我们无一幸免吗? 15以色列的上帝耶和华啊,你是公义的,所以我们这些余民今天才得以幸存。看啊,我们在你面前身负罪恶,因而无人能在你面前站立得住。”