ዕዝራ 8 – NASV & OL

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 8:1-36

ከዕዝራ ጋር የተመለሱት የየቤተ ሰቡ አለቆች ስም ዝርዝር

1በንጉሡ በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት ከባቢሎን አብረውኝ የወጡት የየቤተ ሰቡ አለቆችና አብረዋቸው የተመዘገቡት እነዚህ ናቸው፤

2ከፊንሐስ ዘሮች ጌርሶን፤

ከኢታምር ዘሮች ዳንኤል፤

ከዳዊት ዘሮች ሐጡስ፤ 3እርሱም ከሴኬንያ ዘሮች ነው፤

ከፋሮስ ዘሮች ዘካርያስና ከእርሱም ጋር 150 ወንዶች ተመዝግበው ነበር፤

4ከፋሐት ሞዓብ ዘሮች የዘራእያ ልጅ ኤሊሆ ዔናይና ከእርሱም ጋር 200 ወንዶች፤

5ከዛቱ8፥5 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 8፥22) ይህን ስም ይጨምራሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ዛቱ የሚለውን አይጨምርም። ዘሮች የየሕዚኤል ልጅ ሴኬንያና ከእርሱም ጋር 300 ወንዶች፤

6ከዓዲን ዘሮች የዮናታን ልጅ ዔቤድና ከእርሱም ጋር 50 ወንዶች፤

7ከኤላም ዘሮች የጎቶልያ ልጅ የሻያና ከእርሱም ጋር 70 ወንዶች፤

8ከሰፋጥያስ ዘሮች፣ የሚካኤል ልጅ ዝባድያ፣ ከ80 ወንዶች ጋር፤

9ከኢዮአብ ዘሮች የይሒኤል ልጅ አብድዩና ከእርሱ ጋር 218 ወንዶች፤

10ከባኒ8፥10 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 8፥36) ይህን ስም ይጨምራሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ባኒ የሚለውን አይጨምርም። ዘሮች የዮሲፍያ ልጅ ሰሎሚትና ከእርሱም ጋር 160 ወንዶች፤

11ከቤባይ ዘሮች የቤባይ ልጅ ዘካርያስ ከእርሱም ጋር 28 ወንዶች፤

12ከዓዝጋድ ዘሮች የሃቃጣን ልጅ ዮሐናንና ከእርሱም ጋር 110 ወንዶች፤

13ከአዶኒቃም ዘሮች፣ የመጨረሻዎቹ ስማቸው ይህ ነው፤ ኤሊፋላት፣ ይዑኤልና ሸማያ፣ ከእነርሱም ጋር 60 ወንዶች፤

14ከበጉዋይ ዘሮች ዑታይና ዘቡድ፣ ከእነርሱም ጋር 70 ወንዶች።

ወደ ኢየሩሳሌም መመለስ

15እኔም ወደ አኅዋ በሚፈሰው ወንዝ አጠገብ ሰዎቹን ሰበሰብኋቸው፤ በዚያም ሦስት ቀን ቈየን። ሕዝቡንና ካህናቱን ስመለከት፣ ከሌዊ ወገን የሆነ አንድም ሰው በዚያ አላገኘሁም። 16ስለዚህ መራሕያኑን አልዓዛርን፣ አርኤልን፣ ሸማያን፣ ኤልናታንን፣ ያሪብን፣ ኤልናታን፣ ናታንን፣ ዘካርያስንና ሜሱላምን እንዲሁም መምህራኑን ዮያሪብንና ኤልናታንን አስጠራኋቸው፤ 17እነርሱንም ካሲፍያ በሚባል ስፍራ አለቃ ወደ ሆነው ወደ አዶ ላክኋቸው፤ በአምላካችን ቤት የሚያገለግሉ ሰዎችን ያመጡልን ዘንድ በካሲፍያ የቤተ መቅደስ አገልጋዮች ለሆኑት ለአዶና ለሥጋ ዘመዶቹ የሚናገሩትን አስታወቅኋቸው። 18መልካሚቱ የአምላካችን እጅ በእኛ ላይ ስለ ነበረች፣ ከሞሖሊ ዘሮች የእስራኤል ልጅ የሌዊ ልጅ የሆነውን ሰራብያ ተብሎ የሚጠራውን አስተዋይ ሰው፣ ከእርሱም ጋር ዐሥራ ስምንት የሚሆኑ ወንዶች ልጆቹንና ወንድሞቹን አመጡልን፤ 19እንዲሁም ሐሸብያንና ከሜራሪ ዘሮች የሻያን፣ ከወንድሞቹና ከአጎቶቹ ወንዶች ልጆች ጋር 20 ወንዶችን አመጡልን። 20በተጨማሪም ዳዊትና ሹማምቱ ሌዋውያኑን እንዲረዳ ካቋቋሙት ከቤተ መቅደሱ አገልጋዮች ቡድን 220 አመጡ፤ እነዚህም ሁሉ በየስማቸው ተመዘገቡ።

21ራሳችንን በአምላካችን ፊት ዝቅ እንድናደርግ፣ ጕዞውም ለእኛና ለልጆቻችን፣ ለንብረታችንም ሁሉ የተቃና እንዲሆንልን፣ እዚያው በአኅዋ ወንዝ አጠገብ ጾም ዐወጅሁ። 22“መልካሚቱ የአምላካችን እጅ በሚፈልጉት ሁሉ ላይ ናት፤ እርሱን በሚተዉ ሁሉ ላይ ግን ቍጣው ትወርድባቸዋለች” ብለን ለንጉሡ ነግረነው ስለ ነበር፣ በመንገድ ላይ ከጠላት የሚጠብቁን ወታደሮችንና ፈረሰኞችን እንዲሰጠን ንጉሡን ለመጠየቅ ዐፍሬ ነበር። 23ስለዚህ ጾምን፤ ወደ አምላካችንም ስለዚህ ነገር ልመና አቀረብን፤ እርሱም ጸሎታችንን ሰማ።

24እኔም ከዋና ዋናዎቹ ካህናትም ዐሥራ ሁለት ሰዎችን፣ ከእነርሱም ጋር ሰራብያን፣ ሐሸቢያንና ከወንድሞቻቸውም መካከል ዐሥር ሰዎችን ለየሁ፤ 25ንጉሡ፣ አማካሪዎቹ፣ ሹሞቹና በዚያ የነበሩ እስራኤል ሁሉ ለአምላካችን ቤት የሰጡትን ብር፣ ወርቅና ዕቃ ሁሉ መዝኜ ሰጠኋቸው። 26ስድስት መቶ አምሳ መክሊት8፥26 22 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብር፣ አንድ መቶ መክሊት የብር ዕቃዎች፣ አንድ መቶ መክሊት ወርቅ፣8፥26 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። 27አንድ ሺሕ ዳሪክ8፥27 8.5 ኪሎ ግራም ያህል ነው። የሚያወጡ ሃያ የወርቅ ወጭቶችና እንደ ወርቅ ነጥረው ከሚያብረቀርቅ ናስ የተሠሩ ሁለት ዕቃዎችን መዝኜ በእጃቸው አስረከብኋቸው።

28እንዲህም አልኋቸው፤ “እናንተና እነዚህ ዕቃዎች ለእግዚአብሔር ተቀድሳችኋል፤ ብሩና ወርቁ ለአባቶቻችሁ አምላክ ለእግዚአብሔር በበጎ ፈቃድ የቀረበ መባ ነው። 29ኢየሩሳሌም በሚገኘው በእግዚአብሔር ቤት ክፍሎች ውስጥ በዋና ዋናዎቹ ካህናት፣ በሌዋውያኑና በየቤተ ሰቡ የእስራኤል አለቆች ፊት እስክትመዝኗቸው ድረስ በጥንቃቄ ጠብቋቸው።” 30ከዚያም ካህናቱና ሌዋውያኑ ኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ አምላካችን ቤት እንዲሄድ የተመዘነውን ብር፣ ወርቅና ንዋያተ ቅድሳት ተረከቡ።

31እኛም በመጀመሪያው ወር ዐሥራ ሁለተኛው ቀን ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከአኅዋ ወንዝ ተነሣን። የአምላካችን እጅ በላያችን ነበረች፤ እርሱም ከጠላቶቻችንና በመንገድ ላይ ከሚሸምቁ አዳነን። 32ኢየሩሳሌምም ደረስን፤ በዚያም ሦስት ቀን ዐረፍን።

33በአራተኛው ቀን ብሩን፣ ወርቁንና ንዋያተ ቅድሳቱን በአምላካችን ቤት መዝነን ለኦሪዮ ልጅ ለካህኑ ለሜሪሞት በእጁ አስረከብነው፤ ከእርሱም ጋር የፊንሐስ ልጅ አልዓዛር፣ ሌዋውያኑ የኢያሱ ልጅ ዮዛባትና የቢንዊ ልጅ ኖዓድያ ነበሩ። 34ሁሉም ነገር ተቈጠረ፤ ተመዘነም፤ የተመዘነውም ሁሉ በዚያኑ ጊዜ ተመዘገበ።

35ከዚያም ከምርኮ የተመለሱት፣ ለእስራኤል ሁሉ ዐሥራ ሁለት ወይፈኖችን፣ ዘጠና ስድስት አውራ በጎችን፣ ሰባ ሰባት ተባዕት ጠቦቶችን፣ ለእስራኤል አምላክ የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረቡ፤ ለኀጢአት መሥዋዕት ደግሞ ዐሥራ ሁለት ተባዕት ፍየሎችን አቀረቡ። ይህም ሁሉ ለእግዚአብሔር የቀረበ የሚቃጠል መሥዋዕት ነበር። 36የንጉሡንም ትእዛዝ ለንጉሡ እንደራሴዎችና በኤፍራጥስ ማዶ ለሚገኙት አገረ ገዦች ሰጡ፤ እነርሱም ሕዝቡንና የእግዚአብሔርን ቤት ረዱ።

O Livro

Esdras 8:1-36

Os chefes de família que voltaram com Esdras

1São estes os nomes e as genealogias dos chefes que me acompanharam, desde Babilónia, durante o reinado do rei Artaxerxes:

2descendentes de Fineias:

Gerson;

descendentes de Itamar:

Daniel;

do subclã de David, pertencente ao clã de Secanias:

Hatus;

3descendentes de Parós:

Zacarias e 150 outros homens;

4descendentes de Paate-Moabe:

Elioenai, filho de Zeraías, e mais 200 homens;

5descendentes de Zatu:

Secanias, filho de Jaaziel, e com ele 300 homens;

6descendentes de Adim:

Ebede, filho de Jónatas, e 50 homens;

7descendentes de Elão:

Jesaías, filho de Atalia, e mais 70 homens;

8descendentes de Sefatias:

Zebadias, filho de Micael, com ele 80 homens;

9descendentes de Joabe:

Obadias, filho de Jeiel, e 218 homens;

10descendentes de Bani:

Selomite, filho de Josifias, e mais 160 homens;

11descendentes de Bebai:

Zacarias, filho de Bebai, e 28 homens;

12descendentes de Azgade:

Joanã, filho de Hacatã, e mais 110 homens;

13descendentes de Adonicão:

Elifelete, Jeiel e Semaías, mais 60 homens, que chegaram mais tarde;

14descendentes de Bigvai:

Utai, Zacur e 70 outros homens.

O retorno a Jerusalém

15Juntámo-nos na margem do rio Aava e ficámos ali acampados três dias, enquanto eu verificava as listas do povo e dos sacerdotes que iam chegando. Verifiquei que não havia nem um só levita que se tivesse apresentado voluntariamente. 16Então, mandei chamar Eliezer, Ariel, Semaías, Elnatã, Jaribe, Elnatã, Natã, Zacarias e Mesulão, líderes levitas; também mandei buscar Joiaribe e Elnatã, que eram sábios. 17Enviei-os depois a Ido, líder dos judeus em Casifia, para lhe pedir, a ele, aos seus irmãos e aos funcionários do templo, que nos mandassem sacerdotes para o templo de Deus em Jerusalém. 18E Deus foi bom para connosco! Mandou-nos um homem notável chamado Serebias e os seus 18 filhos e irmãos; uma pessoa muito inteligente, descendente de Mali, filho de Levi e neto de Israel. 19Deus também fez com que se apresentassem Hasabias e Jesaías, filho de Merari, com 20 dos seus familiares, filhos e irmãos. 20Vieram também 220 funcionários do templo. Estes funcionários eram assistentes dos levitas, uma categoria instituída pelo rei David. Todos estes 220 homens foram devidamente registados pelos seus nomes.

21Enquanto ali estávamos, à beira do rio Aava, proclamei um jejum, para nos humilharmos perante Deus; orámos para que nos desse uma boa viagem e nos protegesse, a nós, assim como aos nossos filhos e bagagens, durante a viagem. 22Porque me envergonhei de pedir ao rei soldados, a pé e a cavalo, para nos acompanharem e nos protegerem dos inimigos durante o caminho; pois tínhamos dito que o nosso Deus protege todos quantos o adoram e a desgraça só vem aos que o abandonam. 23Por isso, jejuámos e implorámos a Deus que cuidasse de nós, e ele assim fez.

24Designei 12 chefes de entre os sacerdotes, Serebias, Hasabias e 10 outros sacerdotes; 25deveriam responsabilizar-se pelo transporte da prata e do ouro, dos recipientes em ouro e dos outros objetos que o rei e o seu conselho, e os líderes do povo de Israel, tinham oferecido para o templo de Deus. 26Pesei o dinheiro, quando lho entreguei, e contei no total 22 quilos de prata; avaliei também em 3,4 toneladas os vasos de prata e em outro tanto os de ouro. 27Havia também 20 taças de ouro que pesavam 8 quilos; entreguei-lhes, igualmente, 2 belas taças de bronze que eram tão preciosas com as de ouro.

28Depois disse-lhes: “Vocês estão consagrados ao Senhor; tal como vocês, também consagrei os tesouros: o equipamento, o dinheiro e as taças que foram oferecidas voluntariamente ao Senhor, o Deus dos vossos pais. 29Assim, vigiem bem estes tesouros! Terão de os apresentar, sem a mínima perda, aos sacerdotes e aos chefes dos levitas, assim como aos anciãos de Israel em Jerusalém, onde deverão ser colocados nas salas do tesouro do templo do Senhor.” 30Os sacerdotes e os levitas aceitaram a responsabilidade daquele transporte até ao templo de Deus em Jerusalém.

31Levantámos o acampamento junto ao rio Aava no dia 12 do primeiro mês e partimos para Jerusalém. Deus protegeu-nos e livrou-nos dos inimigos e dos bandidos durante todo o caminho. 32Assim, chegamos sãos e salvos a Jerusalém e permanecemos ali três dias.

33No quarto dia, após a chegada, todo o ouro e prata e os outros valores foram pesados no templo, por Meremote, filho de Urias o sacerdote, por Eleazar, filho de Fineias, por Jozabade, filho de Jesua, e por Noadias, filho de Binuí, todos eles levitas. 34Foi tudo contado e anotado o peso do ouro e da prata.

35Depois disso, os que tinham regressado do cativeiro, ofereceram holocaustos ao Deus de Israel: 12 novilhos por toda a nação de Israel, 96 carneiros, 77 cordeiros e 12 bodes como oferta pelo pecado. Todos estes animais foram queimados em holocausto ao Senhor. 36Os decretos reais foram entregues aos seus representantes e aos governadores de todas as províncias a ocidente do rio Eufrates, os quais colaboraram, eles próprios, nos trabalhos de reconstrução do templo de Deus.