ዕዝራ 8 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 8:1-36

ከዕዝራ ጋር የተመለሱት የየቤተ ሰቡ አለቆች ስም ዝርዝር

1በንጉሡ በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት ከባቢሎን አብረውኝ የወጡት የየቤተ ሰቡ አለቆችና አብረዋቸው የተመዘገቡት እነዚህ ናቸው፤

2ከፊንሐስ ዘሮች ጌርሶን፤

ከኢታምር ዘሮች ዳንኤል፤

ከዳዊት ዘሮች ሐጡስ፤ 3እርሱም ከሴኬንያ ዘሮች ነው፤

ከፋሮስ ዘሮች ዘካርያስና ከእርሱም ጋር 150 ወንዶች ተመዝግበው ነበር፤

4ከፋሐት ሞዓብ ዘሮች የዘራእያ ልጅ ኤሊሆ ዔናይና ከእርሱም ጋር 200 ወንዶች፤

5ከዛቱ8፥5 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 8፥22) ይህን ስም ይጨምራሉ፤ ዕብራይስጡ ግን ዛቱ የሚለውን አይጨምርም። ዘሮች የየሕዚኤል ልጅ ሴኬንያና ከእርሱም ጋር 300 ወንዶች፤

6ከዓዲን ዘሮች የዮናታን ልጅ ዔቤድና ከእርሱም ጋር 50 ወንዶች፤

7ከኤላም ዘሮች የጎቶልያ ልጅ የሻያና ከእርሱም ጋር 70 ወንዶች፤

8ከሰፋጥያስ ዘሮች፣ የሚካኤል ልጅ ዝባድያ፣ ከ80 ወንዶች ጋር፤

9ከኢዮአብ ዘሮች የይሒኤል ልጅ አብድዩና ከእርሱ ጋር 218 ወንዶች፤

10ከባኒ8፥10 አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች (እንዲሁም መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 8፥36) ይህን ስም ይጨምራሉ፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ባኒ የሚለውን አይጨምርም። ዘሮች የዮሲፍያ ልጅ ሰሎሚትና ከእርሱም ጋር 160 ወንዶች፤

11ከቤባይ ዘሮች የቤባይ ልጅ ዘካርያስ ከእርሱም ጋር 28 ወንዶች፤

12ከዓዝጋድ ዘሮች የሃቃጣን ልጅ ዮሐናንና ከእርሱም ጋር 110 ወንዶች፤

13ከአዶኒቃም ዘሮች፣ የመጨረሻዎቹ ስማቸው ይህ ነው፤ ኤሊፋላት፣ ይዑኤልና ሸማያ፣ ከእነርሱም ጋር 60 ወንዶች፤

14ከበጉዋይ ዘሮች ዑታይና ዘቡድ፣ ከእነርሱም ጋር 70 ወንዶች።

ወደ ኢየሩሳሌም መመለስ

15እኔም ወደ አኅዋ በሚፈሰው ወንዝ አጠገብ ሰዎቹን ሰበሰብኋቸው፤ በዚያም ሦስት ቀን ቈየን። ሕዝቡንና ካህናቱን ስመለከት፣ ከሌዊ ወገን የሆነ አንድም ሰው በዚያ አላገኘሁም። 16ስለዚህ መራሕያኑን አልዓዛርን፣ አርኤልን፣ ሸማያን፣ ኤልናታንን፣ ያሪብን፣ ኤልናታን፣ ናታንን፣ ዘካርያስንና ሜሱላምን እንዲሁም መምህራኑን ዮያሪብንና ኤልናታንን አስጠራኋቸው፤ 17እነርሱንም ካሲፍያ በሚባል ስፍራ አለቃ ወደ ሆነው ወደ አዶ ላክኋቸው፤ በአምላካችን ቤት የሚያገለግሉ ሰዎችን ያመጡልን ዘንድ በካሲፍያ የቤተ መቅደስ አገልጋዮች ለሆኑት ለአዶና ለሥጋ ዘመዶቹ የሚናገሩትን አስታወቅኋቸው። 18መልካሚቱ የአምላካችን እጅ በእኛ ላይ ስለ ነበረች፣ ከሞሖሊ ዘሮች የእስራኤል ልጅ የሌዊ ልጅ የሆነውን ሰራብያ ተብሎ የሚጠራውን አስተዋይ ሰው፣ ከእርሱም ጋር ዐሥራ ስምንት የሚሆኑ ወንዶች ልጆቹንና ወንድሞቹን አመጡልን፤ 19እንዲሁም ሐሸብያንና ከሜራሪ ዘሮች የሻያን፣ ከወንድሞቹና ከአጎቶቹ ወንዶች ልጆች ጋር 20 ወንዶችን አመጡልን። 20በተጨማሪም ዳዊትና ሹማምቱ ሌዋውያኑን እንዲረዳ ካቋቋሙት ከቤተ መቅደሱ አገልጋዮች ቡድን 220 አመጡ፤ እነዚህም ሁሉ በየስማቸው ተመዘገቡ።

21ራሳችንን በአምላካችን ፊት ዝቅ እንድናደርግ፣ ጕዞውም ለእኛና ለልጆቻችን፣ ለንብረታችንም ሁሉ የተቃና እንዲሆንልን፣ እዚያው በአኅዋ ወንዝ አጠገብ ጾም ዐወጅሁ። 22“መልካሚቱ የአምላካችን እጅ በሚፈልጉት ሁሉ ላይ ናት፤ እርሱን በሚተዉ ሁሉ ላይ ግን ቍጣው ትወርድባቸዋለች” ብለን ለንጉሡ ነግረነው ስለ ነበር፣ በመንገድ ላይ ከጠላት የሚጠብቁን ወታደሮችንና ፈረሰኞችን እንዲሰጠን ንጉሡን ለመጠየቅ ዐፍሬ ነበር። 23ስለዚህ ጾምን፤ ወደ አምላካችንም ስለዚህ ነገር ልመና አቀረብን፤ እርሱም ጸሎታችንን ሰማ።

24እኔም ከዋና ዋናዎቹ ካህናትም ዐሥራ ሁለት ሰዎችን፣ ከእነርሱም ጋር ሰራብያን፣ ሐሸቢያንና ከወንድሞቻቸውም መካከል ዐሥር ሰዎችን ለየሁ፤ 25ንጉሡ፣ አማካሪዎቹ፣ ሹሞቹና በዚያ የነበሩ እስራኤል ሁሉ ለአምላካችን ቤት የሰጡትን ብር፣ ወርቅና ዕቃ ሁሉ መዝኜ ሰጠኋቸው። 26ስድስት መቶ አምሳ መክሊት8፥26 22 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብር፣ አንድ መቶ መክሊት የብር ዕቃዎች፣ አንድ መቶ መክሊት ወርቅ፣8፥26 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። 27አንድ ሺሕ ዳሪክ8፥27 8.5 ኪሎ ግራም ያህል ነው። የሚያወጡ ሃያ የወርቅ ወጭቶችና እንደ ወርቅ ነጥረው ከሚያብረቀርቅ ናስ የተሠሩ ሁለት ዕቃዎችን መዝኜ በእጃቸው አስረከብኋቸው።

28እንዲህም አልኋቸው፤ “እናንተና እነዚህ ዕቃዎች ለእግዚአብሔር ተቀድሳችኋል፤ ብሩና ወርቁ ለአባቶቻችሁ አምላክ ለእግዚአብሔር በበጎ ፈቃድ የቀረበ መባ ነው። 29ኢየሩሳሌም በሚገኘው በእግዚአብሔር ቤት ክፍሎች ውስጥ በዋና ዋናዎቹ ካህናት፣ በሌዋውያኑና በየቤተ ሰቡ የእስራኤል አለቆች ፊት እስክትመዝኗቸው ድረስ በጥንቃቄ ጠብቋቸው።” 30ከዚያም ካህናቱና ሌዋውያኑ ኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ አምላካችን ቤት እንዲሄድ የተመዘነውን ብር፣ ወርቅና ንዋያተ ቅድሳት ተረከቡ።

31እኛም በመጀመሪያው ወር ዐሥራ ሁለተኛው ቀን ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከአኅዋ ወንዝ ተነሣን። የአምላካችን እጅ በላያችን ነበረች፤ እርሱም ከጠላቶቻችንና በመንገድ ላይ ከሚሸምቁ አዳነን። 32ኢየሩሳሌምም ደረስን፤ በዚያም ሦስት ቀን ዐረፍን።

33በአራተኛው ቀን ብሩን፣ ወርቁንና ንዋያተ ቅድሳቱን በአምላካችን ቤት መዝነን ለኦሪዮ ልጅ ለካህኑ ለሜሪሞት በእጁ አስረከብነው፤ ከእርሱም ጋር የፊንሐስ ልጅ አልዓዛር፣ ሌዋውያኑ የኢያሱ ልጅ ዮዛባትና የቢንዊ ልጅ ኖዓድያ ነበሩ። 34ሁሉም ነገር ተቈጠረ፤ ተመዘነም፤ የተመዘነውም ሁሉ በዚያኑ ጊዜ ተመዘገበ።

35ከዚያም ከምርኮ የተመለሱት፣ ለእስራኤል ሁሉ ዐሥራ ሁለት ወይፈኖችን፣ ዘጠና ስድስት አውራ በጎችን፣ ሰባ ሰባት ተባዕት ጠቦቶችን፣ ለእስራኤል አምላክ የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረቡ፤ ለኀጢአት መሥዋዕት ደግሞ ዐሥራ ሁለት ተባዕት ፍየሎችን አቀረቡ። ይህም ሁሉ ለእግዚአብሔር የቀረበ የሚቃጠል መሥዋዕት ነበር። 36የንጉሡንም ትእዛዝ ለንጉሡ እንደራሴዎችና በኤፍራጥስ ማዶ ለሚገኙት አገረ ገዦች ሰጡ፤ እነርሱም ሕዝቡንና የእግዚአብሔርን ቤት ረዱ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以斯拉記 8:1-36

歸回之人

1亞達薛西王年間,與我一起從巴比倫上到耶路撒冷之人的族長和家譜如下: 2非尼哈的子孫有革順以他瑪的子孫有但以理大衛的子孫有哈突3巴錄的後裔、示迦尼的子孫有撒迦利亞及一百五十名同族譜的男子; 4巴哈·摩押的子孫有西拉希雅的兒子以利約乃及二百名男子; 5薩土8·5 薩土」七十士譯本有此名字,希伯來文則無。的子孫有雅哈悉的兒子示迦尼及三百名男子; 6亞丁的子孫有約拿單的兒子以別及五十名男子; 7以攔的子孫有亞他利雅的兒子耶篩亞及七十名男子; 8示法提雅的子孫有米迦勒的兒子西巴第雅及八十名男子; 9約押的子孫有耶歇的兒子俄巴底亞及二百一十八名男子; 10巴尼8·10 巴尼」七十士譯本有此名字,希伯來文則無。的後裔、約細斐的子孫有示羅密及一百六十名男子; 11比拜的後裔有比拜的兒子撒迦利亞及二十八名男子; 12押甲的後裔有哈加坦的兒子約哈難及一百一十名男子; 13稍後歸回的亞多尼干的子孫有以利法列耶利示瑪雅及六十名男子; 14比革瓦伊的子孫有烏太撒布及七十名男子。

以斯拉為聖殿召集利未人

15我把他們召集在流向亞哈瓦的河邊,我們在那裡紮營三天。我察看民眾和祭司,發現他們當中沒有利未人。 16於是,我派人叫來首領以利以謝亞列示瑪雅以利拿單雅立以利拿單拿單撒迦利亞米書蘭及兩位教師約雅立以利拿單17我派他們去見迦西斐雅的首領易多,請他們告訴易多及其做殿役的親族帶一些人來我們上帝的殿裡事奉。 18我們的上帝施恩幫助我們,他們給我們帶來一位能幹的人示利比及其弟兄和兒子共十八人。示利比以色列的兒子利未的後裔抹利的子孫。 19他們還帶來哈沙比雅米拉利的子孫耶篩亞,以及哈沙比雅的弟兄和兒子共二十人。 20此外還有二百二十名殿役,他們都是被點名指派的。從前大衛和眾官員曾指派殿役服侍利未人。

以斯拉帶領百姓禁食

21然後,我在亞哈瓦河邊宣佈禁食,為要在我們的上帝面前謙卑下來,祈求祂保護我們、我們的兒女及財物一路平安。 22我羞於求王派步兵和騎兵沿途幫助我們禦敵,因為我們曾經告訴王:「我們的上帝會施恩幫助尋求祂的人,但會向背棄祂的人發烈怒。」 23因此,我們為這事禁食、尋求我們的上帝,祂應允了我們。

獻給聖殿的禮物

24我選出十二位祭司長:示利比哈沙比雅和他們的十個弟兄。 25王及其謀士和將領,以及所有在場的以色列人獻給我們上帝殿的金銀和器皿,我都秤了交給他們。 26我交給他們的有二十二噸銀子、三點四噸銀器、三點四噸金子、 27共重八公斤半的二十個金碗和兩件貴重如金子的上等精銅器皿。 28我對他們說:「你們和這些器皿是獻給耶和華的,金銀是自願獻給你們祖先的上帝耶和華的禮物。 29你們要好好保管,護送到耶路撒冷耶和華殿的庫房裡,要在祭司長、利未人和以色列的各族長面前過秤。」 30於是,祭司和利未人接過這些稱過的金銀和器皿,要帶去耶路撒冷我們上帝的殿裡。

返回耶路撒冷

31一月十二日,我們從亞哈瓦河邊出發上耶路撒冷。我們的上帝施恩幫助我們,救我們脫離仇敵和路上埋伏之人的攻擊。 32耶路撒冷後,我們休息了三天。 33第四天,我們在我們上帝的殿裡把金銀和器皿過秤,交給烏利亞的兒子米利末祭司。在場的還有非尼哈的兒子以利亞撒利未耶書亞的兒子約撒拔賓內的兒子挪亞底34每樣東西都被數過、稱過,其重量都被記錄下來。

35從流亡之地歸回的人又獻燔祭給以色列的上帝,為全體以色列人獻上十二頭公牛、九十六隻公綿羊和七十七隻綿羊羔,並獻上十二隻公山羊作贖罪祭。這些都是獻給耶和華的燔祭。 36他們將王的諭旨交給王的總督和幼發拉底河西的省長,眾官員都為民眾和上帝殿的工作提供幫助。