ዕዝራ 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ዕዝራ 7:1-28

ዕዝራ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ

1ከእነዚህም ነገሮች በኋላ በፋርስ ንጉሥ በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት፣ ዕዝራ የሠራያ ልጅ፣ የዓዛርያስ ልጅ፣ የኬልቅያስ ልጅ 2የሰሎም ልጅ፣ የሳዶቅ ልጅ፣ የአኪጦብ ልጅ፣ 3የአማርያ ልጅ፣ የዓዛርያስ ልጅ፣ የመራዮት ልጅ፣ 4የዘራእያ ልጅ፣ የኦዚ ልጅ፣ የቡቂ ልጅ፣ 5የአቢሱ ልጅ፣ የፊንሐስ ልጅ፣ የአልዓዛር ልጅ፣ የታላቁ ካህን የአሮን ልጅ፤ 6ይህ ዕዝራ ከባቢሎን መጣ፤ እርሱም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ሕግ በሚገባ የሚያውቅ የሕግ መምህር ነበር። የአምላኩ የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ስለ ነበረች፣ የጠየቀውን ሁሉ ንጉሡ ፈቀደለት። 7እንደዚሁም አንዳንድ እስራኤላውያን፣ ከካህናት፣ ከሌዋውያን፣ ከመዘምራን፣ ከበር ጠባቂዎችና ከቤተ መቅደሱ አገልጋዮች ጋር በመሆን በንጉሡ በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት በሰባተኛው ዓመት ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።

8ዕዝራ በንጉሡ ሰባተኛ ዓመት በአምስተኛው ወር ኢየሩሳሌም ደረሰ። 9መልካሚቱ የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ስለ ነበረች፣ ከባቢሎን በመጀመሪያው ወር በመጀመሪያው ቀን ተነሥቶ በአምስተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ኢየሩሳሌም ደረሰ። 10ዕዝራ የእግዚአብሔርን ሕግ በማጥናትና በማድረግ፣ ለእስራኤልም ሥርዐቱንና ሕጉን በማስተማር ራሱን ፈጽሞ ሰጥቶ ነበር።

ንጉሥ አርጤክስስ ለዕዝራ የሰጠው ደብዳቤ

11እግዚአብሔር ለእስራኤል የሰጠውን ሕግና ትእዛዝ ዐዋቂ ለነበረው ለካህኑና ለመምህሩ ዕዝራ ንጉሥ አርጤክስስ የሰጠው የደብዳቤ ቅጅ ይህ ነው፤

127፥12 ዕዝ 7፥12-26 ላይ የሚገኘው ክፍል የተጻፈው በአረማይክ ቋንቋ ነው። ከንጉሠ ነገሥት አርጤክስስ፤ ለሰማይ አምላክ ሕግ መምህር ለሆነው ለካህኑ ለዕዝራ፤

ሰላም ለአንተ ይሁን፤

13ካህናቱንና ሌዋውያኑን ጨምሮ በመንግሥቴ ውስጥ የሚኖርና ከአንተ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ የሚፈልግ ማንኛውም እስራኤላዊ መሄድ እንዲችል ይህን ትእዛዝ ሰጥቻለሁ። 14በእጅህ በሚገኘው በአምላክህ ሕግ መሠረት፣ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም እንድትመረምር በንጉሡና በሰባት አማካሪዎቹ ተልከሃል። 15ከዚህም በላይ፣ ንጉሡና አማካሪዎቹ መኖሪያው በኢየሩሳሌም ለሆነው ለእስራኤል አምላክ በፈቃዳቸው የሰጡትን ብርና ወርቅ ይዘህ ሂድ፤ 16እንዲሁም ከመላው ባቢሎን አውራጃ የምታገኘውን ብርና ወርቅ በሙሉ፣ ሕዝቡና ካህናቱም በኢየሩሳሌም ላለው ለአምላካቸው ቤተ መቅደስ በፈቃዳቸው የሚሰጡትን መባ ሁሉ ይዘህ ሂድ። 17በዚህም ገንዘብ ወይፈኖችን፣ አውራ በጎችንና ጠቦቶችን፣ ከእህል ቍርባኖቻቸውና ከመጠጥ ቍርባኖቻቸው ጋር መግዛት እንዳለብህ አትርሳ፤ እነዚህንም በኢየሩሳሌም በሚገኘው በአምላካችሁ ቤተ መቅደስ መሠዊያ ላይ አቅርብ። 18ከዚህ የሚቀረውንም ብርና ወርቅ አንተና ወንድሞችህ አይሁድ እንደ አምላካችሁ ፈቃድ ደስ ለሚላችሁ ነገር ሁሉ አውሉት። 19ለአምላክህ ቤተ መቅደስ በዐደራ የተሰጠህንም ዕቃ ሁሉ በኢየሩሳሌም አምላክ ፊት አቅርብ። 20ከዚህም በላይ ለአምላክህ ቤተ መቅደስ ለመስጠት የምትፈልገውን ነገር ሁሉ ከንጉሡ ግምጃ ቤት መውሰድ ትችላለህ።

21በኤፍራጥስ ማዶ የምትገኙ በጅሮንዶች ሁሉ፣ የሰማይ አምላክ ሕግ መምህር የሆነው ካህኑ ዕዝራ የሚጠይቃችሁን ሁሉ በትጋት እንድትሰጡት እኔ ንጉሥ አርጤክስስ እነሆ አዝዣለሁ፤ 22እስከ አንድ መቶ መክሊት7፥22 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብር፣ እስከ አንድ መቶ ቆሮስ7፥22 22 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። ስንዴ፣ እስከ አንድ መቶ ባዶስ7፥22 2.2 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። መስፈሪያ ወይን ጠጅ፣ እስከ አንድ መቶ ባዶስ የወይራ ዘይትና የሚፈለገውን ያህል ጨው ስጡት። 23የሰማይ አምላክ የሚያዘው ሁሉ፣ ለሰማይ አምላክ ቤተ መቅደስ በፍጹም ትጋት ይደረግ፤ በንጉሡና በልጆቹ መንግሥት ላይ ለምን ቍጣ ይውረድ? 24ደግሞም በካህናቱ፣ በሌዋውያኑ፣ በመዘምራኑ፣ በበር ጠባቂዎቹ፣ በቤተ መቅደሱ አገልጋዮች ወይም በሌሎቹ በዚህ በእግዚአብሔር ቤት ሠራተኞች ላይ ቀረጥ፣ ግብርና እጅ መንሻ ለመጣል ሥልጣን እንደሌላችሁ ይህን ዕወቁ።

25አንተም ዕዝራ ከአምላክህ እንደ ተሰጠህ ጥበብ መጠን፣ ከኤፍራጥስ ማዶ ለሚገኙት ሕዝቦች ሁሉ የአምላክህን ሕግ የሚያውቁ ዳኞችንና ፈራጆችን ሹምላቸው፤ ሕጉን የማያውቅ ሰው ቢኖር፣ አንተ ራስህ አስተምረው። 26ለአምላክህ ሕግና ለንጉሡ ሕግ የማይታዘዝ ማንኛውም ሰው፣ የሞት ወይም የስደት ወይም የንብረት መወረስ ወይም የእስራት ቅጣት ይፈጸምበት።

27በኢየሩሳሌም የሚገኘው የእግዚአብሔር ቤት በዚህ ሁኔታ እንዲከበር ይህን በንጉሡ ልብ ያኖረ የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ቡሩክ ይሁን፤ 28እንዲሁም በንጉሡ፣ በአማካሪዎቹና በኀያላን ሹሞቹ ፊት ሁሉ ሞገስን የሰጠኝ አምላክ የተመሰገነ ይሁን። የአምላኬ የእግዚአብሔር እጅ በእኔ ላይ ስለ ነበረች፣ አብረውኝ እንዲሄዱ ከእስራኤል መካከል የታወቁ ሰዎችን ለመሰብሰብ ብርታት አገኘሁ።

Thai New Contemporary Bible

เอสรา 7:1-28

เอสรามายังเยรูซาเล็ม

1หลังจากเหตุการณ์เหล่านี้ ระหว่างรัชกาลกษัตริย์อารทาเซอร์ซีสแห่งเปอร์เซีย เอสราผู้เป็นบุตรของเสไรอาห์ ผู้เป็นบุตรของอาซาริยาห์ ผู้เป็นบุตรของฮิลคียาห์ 2ผู้เป็นบุตรของชัลลูม ผู้เป็นบุตรของศาโดก ผู้เป็นบุตรของอาหิทูบ 3ผู้เป็นบุตรของอามาริยาห์ ผู้เป็นบุตรของอาซาริยาห์ ผู้เป็นบุตรของเมราโยท 4ผู้เป็นบุตรของเศราหิยาห์ ผู้เป็นบุตรของอุสซี ผู้เป็นบุตรของบุคคี 5ผู้เป็นบุตรของอาบีชูวา ผู้เป็นบุตรของฟีเนหัส ผู้เป็นบุตรของเอเลอาซาร์ ผู้เป็นบุตรของอาโรนหัวหน้าปุโรหิต 6เอสราผู้นี้เดินทางมาจากบาบิโลน เอสราเป็นครูผู้เชี่ยวชาญในบทบัญญัติของโมเสสซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลประทาน กษัตริย์ประทานทุกอย่างตามที่เขาทูลขอ เพราะพระหัตถ์ของพระยาห์เวห์พระเจ้าของเขาอยู่เหนือเขา 7ชาวอิสราเอลบางคนรวมทั้งปุโรหิต คนเลวี นักร้อง ยามเฝ้าประตู และผู้ช่วยงานในพระวิหารร่วมเดินทางมายังเยรูซาเล็มในปีที่เจ็ดแห่งรัชกาลกษัตริย์อารทาเซอร์ซีสด้วย

8เอสรามาถึงเยรูซาเล็มในเดือนที่ห้าปีที่เจ็ดแห่งรัชกาลของกษัตริย์องค์นั้น 9เอสราออกเดินทางจากบาบิโลนวันที่หนึ่งเดือนที่หนึ่ง และมาถึงเยรูซาเล็มในวันที่หนึ่งเดือนที่ห้า เพราะพระหัตถ์อันทรงพระคุณของพระเจ้าอยู่เหนือเอสรา 10เพราะเอสราได้อุทิศตนในการศึกษาและปฏิบัติตามบทบัญญัติขององค์พระผู้เป็นเจ้า และเพื่อสอนกฎหมายและบทบัญญัตินั้นในอิสราเอล

สาส์นของกษัตริย์อารทาเซอร์ซีสถึงเอสรา

11นี่เป็นสำเนาพระราชสาส์นของกษัตริย์อารทาเซอร์ซีสถึงเอสราผู้เป็นปุโรหิตและเป็นครูซึ่งรอบรู้เกี่ยวกับพระบัญชาและกฎหมายขององค์พระผู้เป็นเจ้าสำหรับอิสราเอล ความว่า

127:12 อสร.7:12-26 เขียนเป็นภาษาอารเมค จากจอมกษัตริย์อารทาเซอร์ซีส

ถึงปุโรหิตเอสราผู้สอนบทบัญญัติของพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์

สวัสดี

13บัดนี้ เราออกกฤษฎีกาว่า ชาวอิสราเอลคนใดในราชอาณาจักรของเรา รวมทั้งปุโรหิตและคนเลวีที่ประสงค์จะกลับไปยังเยรูซาเล็มกับท่านก็ไปได้ 14กษัตริย์และที่ปรึกษาทั้งเจ็ดของพระองค์ส่งท่านไปเพื่อสอบถามถึงเรื่องยูดาห์และเยรูซาเล็มเกี่ยวกับบทบัญญัติของพระเจ้าซึ่งอยู่ในมือของท่าน 15ยิ่งกว่านั้นจงนำทองคำและเงินซึ่งกษัตริย์กับที่ปรึกษาของพระองค์มอบถวายด้วยความสมัครใจแด่พระเจ้าแห่งอิสราเอลผู้ประทับในเยรูซาเล็มไปด้วย 16พร้อมทั้งเงินและทองทั้งหมดที่รวบรวมได้จากแคว้นบาบิโลนกับของถวายตามความสมัครใจจากประชาชนและบรรดาปุโรหิต สำหรับพระวิหารของพระเจ้าในเยรูซาเล็ม 17จงใช้เงินเหล่านี้ซื้อวัวผู้ แกะผู้ ลูกแกะตัวผู้ เครื่องธัญบูชา และเครื่องดื่มบูชา แล้วถวายบนแท่นบูชาของพระวิหารของพระเจ้าของท่านในเยรูซาเล็ม

18เงินและทองที่เหลืออาจจะใช้ทำอะไรก็ได้ตามแต่ท่านและพี่น้องชาวยิวของท่านเห็นสมควรตามพระประสงค์ของพระเจ้าของท่าน 19จงนำเครื่องใช้ทั้งหมดซึ่งเรามอบให้ท่านดูแลไปถวายพระเจ้าแห่งเยรูซาเล็มเพื่อใช้สำหรับการนมัสการในพระวิหารของพระเจ้าของท่าน 20อนุญาตให้เบิกปัจจัยอื่นที่จำเป็นสำหรับพระวิหารของพระเจ้าของท่านจากคลังหลวงได้

21บัดนี้เรา กษัตริย์อารทาเซอร์ซีส ขอบัญชามายังนายคลังทุกแห่งในมณฑลที่อยู่อีกฟากหนึ่งของแม่น้ำยูเฟรติสว่า จงจัดหาสิ่งต่างๆ แก่ปุโรหิตเอสราผู้สอนบทบัญญัติของพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์อย่างสุดความสามารถตามที่เขายื่นคำขอ 22จนถึงจำนวนเงินหนักประมาณ 3.4 ตัน7:22 ภาษาฮีบรูว่า 100 ตะลันต์ ข้าวสาลีประมาณ 22 กิโลลิตร7:22 ภาษาฮีบรูว่า 100 โคร์ เหล้าองุ่นประมาณ 2.2 กิโลลิตร7:22 ภาษาฮีบรูว่า 100 บัท ทั้งสองแห่งในข้อนี้ น้ำมันมะกอกประมาณ 2.2 กิโลลิตร และเกลือไม่จำกัดจำนวน 23จงจัดหาทุกสิ่งที่พระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ทรงระบุไว้อย่างแข็งขันเพื่อพระวิหารของพระเจ้าแห่งฟ้าสวรรค์ เหตุใดจึงต้องให้พระเจ้าทรงพระพิโรธต่อราชอาณาจักรของกษัตริย์และโอรสของพระองค์เล่า? 24พึงรู้อีกด้วยว่าพวกท่านไม่มีสิทธิอำนาจที่จะเรียกเก็บภาษีอากร บรรณาการ หรือค่าธรรมเนียมใดๆ จากปุโรหิต คนเลวี นักร้อง ยามเฝ้าประตู ผู้ช่วยงานพระวิหาร หรือคนงานอื่นๆ ในพระนิเวศของพระเจ้า

25สำหรับท่าน เอสรา จงใช้สติปัญญาซึ่งพระเจ้าประทานให้แต่งตั้งตุลาการกับเจ้าหน้าที่เพื่อให้ความยุติธรรมแก่ประชากรทุกคนที่อีกฟากหนึ่งของแม่น้ำยูเฟรติสซึ่งรู้บทบัญญัติของพระเจ้า ส่วนผู้ที่ไม่รู้จักบทบัญญัติ ท่านก็จงสอนเขา 26ผู้ใดไม่ยอมปฏิบัติตามบทบัญญัติของพระเจ้าของท่านและกฎหมายของกษัตริย์ ต้องถูกลงอาญาถึงตาย ถูกเนรเทศ ริบทรัพย์ หรือจำคุก

27ขอถวายสรรเสริญแด่พระยาห์เวห์พระเจ้าของบรรพบุรุษของเรา ผู้ทรงบันดาลให้กษัตริย์มีพระทัยที่จะนำเกียรติยศมาสู่พระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าในเยรูซาเล็มเช่นนี้ 28ผู้ทรงโปรดปรานและเชิดชูข้าพเจ้าต่อหน้ากษัตริย์ ต่อหน้าเหล่าที่ปรึกษาและข้าราชสำนักผู้ทรงอำนาจทั้งปวง เพราะว่าพระหัตถ์ของพระยาห์เวห์พระเจ้าของข้าพเจ้าอยู่เหนือข้าพเจ้า ข้าพเจ้าจึงมีใจกล้า รวบรวมผู้นำจากอิสราเอลขึ้นไปกับข้าพเจ้า