ዕንባቆም 2 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዕንባቆም 2:1-20

1በመጠበቂያዬ ላይ እቆማለሁ፤

በምሽጉ ቅጥር ላይ ወጥቼ እቈያለሁ፤

ምን እንደሚለኝ፣

ለክርክሩም2፥1 ወይም በተገሠጽሁ ጊዜ የምሰጠውን ምላሽ የምሰጠውን መልስ ለማወቅ እጠባበቃለሁ።

የእግዚአብሔር መልስ

2እግዚአብሔርም እንዲህ ሲል መለሰ፤

“በቀላሉ እንዲነበብ፣

ራእዩን ጻፈው፤

በሰሌዳም ላይ ቅረጸው።

3ራእዩ የተወሰነለትን ጊዜ ይጠብቃልና፤

ስለ መጨረሻውም ይናገራል፤

እርሱም አይዋሽም፤

የሚዘገይ ቢመስልም ጠብቀው፤

በርግጥ ይመጣል2፥3 የሚመጣ ሰው እንዳለ የሚያመለክቱ አሉ።፤ ከቶም አይዘገይም።

4“እነሆ፤ እርሱ ታብዮአል፤

ምኞቱ ቀና አይደለም፤

ጻድቅ ግን በእምነት2፥4 በታማኝነቱ የሚሉ አሉ። ይኖራል።

5በርግጥ የወይን ጠጅ አታልሎታል፤

ትዕቢተኛ ነው፤ ከቶ አያርፍም፤

እንደ ሲኦል2፥5 መቃብር የሚሉ አሉ። ስስታም ነው፣

እንደ ሞት ከቶ አይጠግብም፤

ሕዝቦችን ለራሱ ይሰበስባል፤

ሰዎችንም ሁሉ ማርኮ ይወስዳል።

6“ታዲያ በእንደዚህ ዐይነቱ ሰው ላይ በማፌዝና በመዘበት እንዲህ እያሉ ሁሉም አይሣለቁበትምን?

“ ‘የተሰረቀውን ሸቀጥ ለራሱ ለሚያከማች፣

ራሱን በዐመፅ ባለጠጋ ለሚያደርግ ወዮለት!

ይህ የሚቀጥለውስ እስከ መቼ ነው?’

7ባለ ዕዳ ያደረግሃቸው ድንገት አይነሡብህምን?

ነቅተውስ አያስደነግጡህምን?

በእጃቸውም ትወድቃለህ።

8አንተ ብዙ ሕዝብ ስለ ዘረፍህ፣

የተረፉት ሕዝቦች ይዘርፉሃል፤

የሰው ደም አፍስሰሃልና፤

አገሮችንና ከተሞችን፣ በውስጣቸው የሚኖሩትን ሁሉ አጥፍተሃል።

9“በተጭበረበረ ትርፍ መኖሪያውን ለሚገነባ፣

ከጠላት እጅ ለማምለጥ፣

ቤቱን በከፍታ ላይ ለሚሠራ ወዮለት!

10የብዙ ሰዎች ነፍስ እንዲጠፋ አሢረሃል፤

በገዛ ቤትህ ላይ ውርደትን፣ በራስህም ላይ ጥፋትን አምጥተሃል።

11ድንጋይ ከቅጥሩ ውስጥ ይጮኻል፤

ከዕንጨት የተሠሩ ተሸካሚዎችም ይመልሱለታል።

12“ከተማን ደም በማፍሰስ ለሚሠራ፣

በወንጀልም ለሚመሠርታት ወዮለት።

13ሰዎች፣ ለእሳት ማገዶ እንዲሆን እንዲለፉ፣

ሕዝቦችም በከንቱ እንዲደክሙ፣

እግዚአብሔር ጸባኦት ወስኖ የለምን?

14ውሃ ባሕርን እንደሚሸፍን ሁሉ፣

ምድርም የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።

15“ኀፍረተ ሥጋቸውን ለማየት፣

ባልንጀሮቹን ለሚያጠጣ፣

እስኪሰክሩም ድረስ ወይን ለሚቀዳላቸው ወዮለት!

16በክብር ፈንታ ዕፍረት ትሞላለህ፤

አሁን ደግሞ ተራው የአንተ ነውና፤ ጠጣ፤ ኀፍረተ ሥጋህም ይገለጥ፤

በእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ያለው ጽዋ ይመለስብሃል፤

ክብርህንም ውርደት ይሸፍነዋል።

17በሊባኖስ ላይ የሠራኸው ግፍ ያጥለቀልቅሃል፤

እንስሳቱን ማጥፋትህም ያስደነግጥሃል፤

የሰው ደም አፍስሰሃልና፤

አገሮችንና ከተሞችን በውስጣቸው የሚኖሩትንም ሁሉ አጥፍተሃልና።

18“የሰው እጅ የቀረጸው ጣዖት፣

ሐሰትንም የሚናገር ምስል ምን ፋይዳ አለው?

ሠሪው በገዛ እጁ ሥራ ይታመናልና፣

መናገር የማይችሉ ጣዖታትን ይሠራልና።

19ዕንጨቱን፣ ‘ንቃ!’

ሕይወት የሌለውንም ድንጋይ፣ ‘ተነሣ!’ ለሚል ወዮለት፤

በውኑ ማስተማር ይችላልን?

እነሆ፤ በወርቅና በብር ተለብጧል፤

እስትንፋስም የለውም።”

20እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፣

ምድር ሁሉ በፊቱ ጸጥ ትበል።

Japanese Contemporary Bible

ハバクク書 2:1-20

2

1今、私は見張り台に立ち、

神が私の訴えにどう答えるか待っていましょう。

主の答え

2すると主はこう言いました。

「板に、わたしの答えを書き記せ。

だれでもひと目で読んで

ほかの者にすぐ伝えることができるように、

大きな字で、はっきり書きなさい。

3だが、わたしが計画しているこのことは、

今すぐには起こらない。

ゆっくりと、着実に、確かに、

幻が実現する時が近づいている。

遅いように思えても、失望してはならない。

これらのことは必ず起こる。

忍耐していなさい。

ただの一日も遅れることはない。

4今から言うことをよく聞いておけ。

このカルデヤ人たちがそうするように、

悪者は自分だけを信頼して失敗する。

だが正しい人は、わたしを信頼して生きる。

5そのうえ、このおごり高ぶったカルデヤ人は、

自分たちのぶどう酒によって裏切られる。

ぶどう酒は人を欺くものだからだ。

彼らは貪欲で、多くの国をかき集めてきたが、

まるで死や地獄のように、決して満足しない。

6捕らえられた者たちが彼らをあざける時が

こようとしている。

『強盗ども。とうとう年貢の納め時だ。

人を虐げ、ゆすり取った当然の報いを受けろ』と。」

7「突然、おまえに借りのある者たちが怒って刃向かい、

おまえの持ち物を奪い取る。

その時、おまえはなすすべもなく立ち尽くし、

震える。

8おまえは多くの国を破滅させた。

今度はおまえが破滅する番だ。

人殺しめ。

おまえは田舎とすべての町を無法状態にした。

9邪悪な手段で富を得ながら、

危険を逃れて生きようとしているおまえは災いだ。

10殺人を犯すことで自分の名を辱め、

いのちさえ失っている。

11まさに、自分の家の壁の石がおまえを訴え、

天井の梁がそれに同調している。

12殺人と強奪で得た金で町を築くおまえは災いだ。

13主に逆らう国々の利益は

彼らの手の中で灰になると、主は定めていなかったか。

彼らがどんなに精を出しても、すべてが水の泡だ。

14(海が水で満たされているように、

全地が主の栄光を知ることで満たされる時がくる。)

15酔っぱらいをこづくように、

近隣の国々をよろめかせ、

その裸と恥を眺めて楽しんでいるおまえは災いだ。

16やがておまえの全盛期は終わり、辱められる。

神のさばきの杯を飲み干すがいい。

よろめいて倒れよ。

17おまえはレバノンの森を切り倒した。

今度はおまえが切り倒される。

おまえは罠で捕らえた野獣を恐ろしい目に会わせた。

今度はおまえが恐ろしい目に会う。

至るところの町々で、殺人と暴虐を行ったからだ。

18人間が造った偶像を拝んで、何の得があったのか。

そんな物が助けになるなど、全く愚かなうそだ。

自分で造った物を信頼していたとは、

なんと愚かな者か。

19いのちのない木の偶像に、

起きて自分たちを救えと命じる者、物言わぬ石に、

何をすべきか教えてほしいと呼びかける者は災いだ。

偶像は、神の代わりに語ることができるのか。

金銀で覆われているが、その中にいのちは全くない。

20しかし主は、ご自分の聖なる神殿にいる。

全地はその御前に静まれ。」