ዕንባቆም 3 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ዕንባቆም 3:1-19

የዕንባቆም ጸሎት

1በዝማሬ የቀረበ የነቢዩ የዕንባቆም ጸሎት፤ በሺግዮኖት።3፥1 የሥነ ጽሑፍ ወይም የሙዚቃ ቋንቋ ሳይሆን አይቀርም።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ዝናህን ሰምቻለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህም አስፈራኝ፤

በእኛ ዘመን አድሳቸው፤

በእኛም ጊዜ እንዲታወቁ አድርግ፤

በመዓት ጊዜ ምሕረትን ዐስብ።

3እግዚአብሔር ከቴማን፣

ቅዱሱም ከፋራን ተራራ መጣ። ሴላ3፥3 ትርጕሙ በትክክል የማይታወቅ ቢሆንም የዜማ ቃል ሳይሆን አይቀርም።

ክብሩ ሰማያትን ሸፈነ፤

ውዳሴውም ምድርን ሞላ።

4ጸዳሉ እንደ ፀሓይ ብርሃን ነው፤

ጨረር ከእጁ ወጣ፤

ኀይሉም በዚያ ተሰውሯል።

5መቅሠፍት በፊቱ ሄደ፤

ቸነፈርም እግር በእግር ተከተለው።

6ቆመ፤ ምድርን አንቀጠቀጠ፤

ተመለከተ፤ ሕዝቦችን አብረከረከ፤

የዘላለም ተራሮች ተፈረካከሱ፤

የጥንት ኰረብቶችም ፈራረሱ፤

መንገዱ ዘላለማዊ ነው።

7የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ፣

የምድያምም መኖሪያዎች ሲታወኩ አየሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ በወንዞች ላይ ተቈጣህን?

መዓትህስ በምንጮች ላይ ነበርን?

በፈረሶችህና በድል አድራጊ ሠረገሎችህ

በጋለብህ ጊዜ፣

በባሕር ላይ ተቈጥተህ ነበርን?

9ቀስትህን አዘጋጀህ፤

ፍላጻም እንዲመጣልህ አዘዝህ፤ ሴላ

ምድርን በወንዞች ከፈልህ፤

10ተራሮች አዩህ፤ ተጨነቁም፤

የውሃ ሞገድ ዐልፎ ሄደ፤

ቀላዩ ደነፋ፤

ማዕበሉንም ወደ ላይ አነሣ።

11ከሚወረወሩ ፍላጾችህ፣

ከሚያብረቀርቅ የጦርህ ነጸብራቅ የተነሣም፣

ፀሓይና ጨረቃ በቦታቸው ቆሙ።

12በምድር ላይ በመዓት ተመላለስህ፤

ሕዝቦችንም በቍጣ ረገጥሃቸው።

13ሕዝብህን ለመታደግ፣

የቀባኸውንም ለማዳን ወጣህ፤

የክፋትን ምድር መሪ ቀጠቀጥህ፤

ከራስ ጠጕሩ እስከ እግር ጥፍሩም ዕርቃኑን አስቀረኸው። ሴላ

14እንደ ዐውሎ ነፋስ ሊበታትነን የመጣውን፣

ምስኪኑን በስውር በመዋጥ የሚደሰተውን፣

የሰራዊት አለቃ ራስ፣

በገዛ ጦሩ ወጋህ።

15ታላላቅ ውሆችን በመናጥ፣

ባሕሩን በፈረሶችህ ረገጥህ።

16እኔ ሰማሁ፤ ልቤም ደነገጠብኝ፤

ከንፈሬ ከድምፁ የተነሣ ተንቀጠቀጠ፤

ፍርሀት እስከ ዐጥንቴ ዘልቆ ገባ፤

እግሬም ተብረከረከ፤

ሆኖም በሚወርረን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ፣

የጥፋትን ቀን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ።

17ምንም እንኳ የበለስ ዛፍ ባያፈራ፣

ከወይን ተክልም ፍሬ ባይገኝ፣

የወይራም ዛፍ ፍሬ ባይሰጥ፣

ዕርሻዎችም ሰብል ባይሰጡ፣

የበጎች ጕረኖ እንኳ ባዶውን ቢቀር፣

ላሞችም በበረት ውስጥ ባይገኙ፣

18እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤

በድነቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።

19ጌታ እግዚአብሔር ኀይሌ ነው፤

እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤

በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።

ለመዘምራን አለቃ፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቼ የተዘመረ መዝሙር።

Japanese Contemporary Bible

ハバクク書 3:1-19

3

ハバククの祈り

1これは、ハバククが主の前で歌った勝利の祈りです。

2主よ。

今、私は、あなたのうわさを聞きました。

あなたがしようとしておられるみわざを知り、

恐れをもって礼拝しています。

この非常時に直面している私たちを、

再び、昔のあなたのようにお助けください。

あなたの力を示してください。

御怒りの中にも、あわれみを忘れないでください。

3神がシナイ山から砂漠を越えて来られるのが

見えます。

その輝きが天地に満ちています。

その栄光は天に満ち、地は神への賛美でいっぱいです。

神は、なんとすばらしい方でしょう。

4両手からは、まばゆいばかりの光が放たれます。

神は恐るべき力を秘め、

5疫病を従えて進みます。

6神はしばらくの間じっと立ち止まり、

地上を見渡します。

それから国々を揺り動かし、

今までびくともしなかった山々を打ち砕き、

丘を平らにするのです。

あなたの力は変わることがありません。

7クシャンとミデヤンの人々が

恐れおののいているのが見えます。

8-9主よ、川を打ち、海の水を左右に分けたのは、

怒ってそうしたのですか。

川や海に不満を抱いたからですか。

いいえ、

あなたの救いの戦車を遣わそうとされたのです。

すべての人がその力を見ました。

それから、あなたが命じると、

泉が地の上にわき出ました。

10山々はそれを見て、震えました。

激流が走り、

深い淵が叫んで、主への降伏を告げました。

11見上げる太陽と月は光を失い始め、

あなたの矢から発する輝きと槍のひらめきとで、

ぼやけています。

12あなたは憤りに燃えて地を行き巡り、

御怒りで国々を踏みつけました。

13ご自分が選んだ民を救うために出て行き、

悪者たちの頭を砕き、

頭のてっぺんから足のつま先まで、

その骨をさらしものにしました。

14イスラエルなど物の数ではないと、

つむじ風のようにやって来た者たちを、

彼らの武器で滅ぼしました。

15あなたの騎手たちは海を渡って前進し、

大水は高くもり上がりました。

16このすべてを聞いて、私は震え、

歯ががくがくしています。

足もとがふらつき、ぶるぶる震えています。

私は、侵略した民に苦しみが襲いかかる日を、

静かに待ち望みましょう。

17いちじくの木が全滅して花も実もつけず、

オリーブの木も実りがなく、

畑が荒れたままであっても、

羊の群れが野で死に、牛小屋がからっぽでも、

18私は主を喜びます。

私を救ってくださる神のおかげで幸せです。

19神、主は私の力です。

私を鹿のように速く走れるようにし、

山の向こうに安全に連れて行ってくださるのです。

(聖歌隊の指揮者のために。

この頌歌を歌うときは弦楽器の伴奏で歌うこと。)