ዕብራውያን 3 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ዕብራውያን 3:1-19

ኢየሱስ ከሙሴ በላይ ነው

1እንግዲህ የሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፤ የእምነታችን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት የሆነውን ኢየሱስን አስቡ። 2ሙሴ በእግዚአብሔር ቤት ሁሉ ላይ ታማኝ እንደ ነበር፣ እርሱም ለሾመው ታማኝ ነበር። 3ቤትን የሚሠራ ከቤቱ ይልቅ የሚበልጥ ክብር እንዳለው፣ ኢየሱስም ከሙሴ የሚበልጥ ክብር የተገባው ሆኖ ተገኝቷል፤ 4እያንዳንዱ ቤት የራሱ ሠሪ አለው፤ ነገር ግን ሁሉን የሠራ እግዚአብሔር ነው። 5ሙሴ ወደ ፊት ስለሚነገረው ነገር እየመሰከረ፣ በእግዚአብሔር ቤት ሁሉ ላይ እንደ አንድ ታማኝ አገልጋይ ነበር፤ 6ክርስቶስ ግን በእግዚአብሔር ቤት ላይ እንደ ታማኝ ልጅ ነው። እኛም የምንተማመንበትንና የምንመካበትን ተስፋ አጥብቀን ብንይዝ ቤቱ ነን።

ስለ አለማመን የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

7ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል፣

“ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣

8በምድረ በዳ በፈተና ቀን፣

በዐመፅ እንዳደረጋችሁት፣

ልባችሁን አታደንድኑ።

9አባቶቻችሁ በዚያ ተፈታተኑኝ፤

መረመሩኝ፤ ያደረግሁትንም ሁሉ ለአርባ ዓመት አዩ።

10በዚያም ትውልድ ላይ የተቈጣሁት ለዚህ ነበር፤

እንዲህም አልሁ፤ ‘ልባቸው ሁልጊዜ ይስታል፤

መንገዴንም አላወቁም፤’

11ስለዚህ በቍጣዬ እንዲህ ብዬ ማልሁ፤

‘ወደ ዕረፍቴ ከቶ አይገቡም።’ ”

12ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ ማንም ከሕያው እግዚአብሔር የሚያስኰበልል፣ ኀጢአተኛና የማያምን ልብ እንዳይኖረው ተጠንቀቁ። 13ነገር ግን ከመካከላችሁ ማንም በኀጢአት ተታልሎ ልቡ እንዳይደነድን፣ “ዛሬ” እየተባለ ሳለ በየቀኑ እርስ በርሳችሁ ተጽናኑ። 14በመጀመሪያ የነበረንን እምነት እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንይዝ ከክርስቶስ ጋር ተካፋዮች እንሆናለን፤ 15ይኸውም፣

“ዛሬ ድምፁን ብትሰሙ፣

በዐመፅ እንዳደረጋችሁት፣

አሁንም ልባችሁን አታደንድኑ”

እንደ ተባለው ነው።

16ሰምተው ያመፁት እነማን ነበሩ? ሙሴ ከግብፅ መርቶ ያወጣቸው ሁሉ አይደሉምን? 17አርባ ዓመት የተቈጣውስ እነማንን ነበር? ኀጢአት ሠርተው ሬሳቸው በምድረ በዳ ወድቆ የቀረውን አይደለምን? 18ያልታዘዙትን3፥18 ወይም ያላመኑትን ካልሆነ በቀር ወደ ዕረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ? 19እንግዲህ ሊገቡ ያልቻሉት ካለማመናቸው የተነሣ እንደ ሆነ እንረዳለን።

King James Version

Hebrews 3:1-19

1Wherefore, holy brethren, partakers of the heavenly calling, consider the Apostle and High Priest of our profession, Christ Jesus; 2Who was faithful to him that appointed him, as also Moses was faithful in all his house. 3For this man was counted worthy of more glory than Moses, inasmuch as he who hath builded the house hath more honour than the house. 4For every house is builded by some man; but he that built all things is God. 5And Moses verily was faithful in all his house, as a servant, for a testimony of those things which were to be spoken after; 6But Christ as a son over his own house; whose house are we, if we hold fast the confidence and the rejoicing of the hope firm unto the end. 7Wherefore (as the Holy Ghost saith, To day if ye will hear his voice, 8Harden not your hearts, as in the provocation, in the day of temptation in the wilderness: 9When your fathers tempted me, proved me, and saw my works forty years. 10Wherefore I was grieved with that generation, and said, They do alway err in their heart; and they have not known my ways. 11So I sware in my wrath, They shall not enter into my rest.) 12Take heed, brethren, lest there be in any of you an evil heart of unbelief, in departing from the living God. 13But exhort one another daily, while it is called To day; lest any of you be hardened through the deceitfulness of sin. 14For we are made partakers of Christ, if we hold the beginning of our confidence stedfast unto the end; 15While it is said, To day if ye will hear his voice, harden not your hearts, as in the provocation. 16For some, when they had heard, did provoke: howbeit not all that came out of Egypt by Moses. 17But with whom was he grieved forty years? was it not with them that had sinned, whose carcases fell in the wilderness? 18And to whom sware he that they should not enter into his rest, but to them that believed not? 19So we see that they could not enter in because of unbelief.