ኤርምያስ 33 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 33:1-26

የመመለስ ተስፋ

1ኤርምያስ በዘብ ጠባቂዎች አደባባይ በግዞት ሳለ፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ዳግመኛ ወደ እርሱ መጣ፤ 2“ምድርን የፈጠራት፣ ያበጃትና የመሠረታት እግዚአብሔር፣ ስሙ እግዚአብሔር የሆነ፣ እርሱ እንዲህ ይላል፤ 3‘ወደ እኔ ጩኽ፤ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና የማይመረመር ነገር እገልጥልሃለሁ።’ 4የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ከባቢሎናውያን33፥4 ወይም ከለዳውያን ጋር ባለው ውጊያ፣ ዐፈር በመደልደልና በሰይፍ የሚደረገውን ጥቃት ለመከላከል ስለ ፈረሱት ስለዚህች ከተማ ቤቶችና ስለ ይሁዳ ነገሥታት ቤተ መንግሥት እንዲህ ይላል፤ 5‘እነዚህ በቍጣዬና በመዓቴ በምገድላቸው ሰዎች ሬሳ ይሞላሉ፤ ስለ ክፋቷ ሁሉ ከዚህች ከተማ ፊቴን እሰውራለሁ።

6“ ‘ይሁን እንጂ፣ ፈውስንና ጤንነትን እንደ ገና እሰጣታለሁ፤ ሕዝቤንም እፈውሳለሁ፤ በብዙ ሰላምና በርጋታ እንዲኖሩ አደርጋለሁ። 7የይሁዳን ምርኮና የእስራኤልን ምርኮ እመልሳለሁ፤33፥7 ወይም ይሁዳንና እስራኤልን ከምርኮ እመልሳለሁ ቀድሞ እንደ ነበሩት ሁኔታ አድርጌ አበጃቸዋለሁ፤ 8እኔን ከበደሉበት ኀጢአት ሁሉ አነጻቸዋለሁ፤ በእኔ ላይ ያመፁበትንም ኀጢአታቸውን ሁሉ ይቅር እላለሁ። 9ይህች ከተማ፣ ለእርሷ ያደረግሁትን በጎ ነገር ሁሉ በሚሰሙት የምድር ሕዝቦች ሁሉ ፊት ለዝና፣ ለደስታ፣ ለምስጋናና ለክብር ትሆናለች፤ ከምሰጣትም የተትረፈረፈ ብልጽግናና ሰላም የተነሣ ይፈራሉ፤ ይንቀጠቀጣሉም።’

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ይህችን ስፍራ፣ “ሰውና እንስሳት የማይኖሩባት ባድማ ናት” ትላላችሁ፤ ነገር ግን ሰውም ሆነ እንስሳ ባልነበሩባቸውና ባድማ በሆኑት በይሁዳ ከተሞችና በኢየሩሳሌም መንገዶች፣ እንደ ገና ድምፅ ይሰማል፤ 11የሐሤትና የደስታ ድምፅ፣ የሙሽራውና የሙሽራዪቱ ድምፅ፣ እንዲሁም፣

“ ‘ “እግዚአብሔር ቸር ነውና፤

ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን አመስግኑ፤”

የሚል የምስጋናን መሥዋዕት ይዘው ወደ እግዚአብሔር ቤት የሚመጡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል፤ የምድሪቱን ምርኮ ቀድሞ እንደ ነበረ እመልሳለሁና፤’ ይላል እግዚአብሔር

12“የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ሰውም ሆነ እንስሳት በማይኖሩበት በዚህ ባዶ ስፍራ፣ በከተማዎቹም ሁሉ እረኞች መንጎቻቸውን የሚያሳርፉበት እንደ ገና ያገኛሉ። 13በተራራማው አገር፣ በምዕራብ ተራሮች ግርጌና በኔጌብ ባሉ ከተሞች በብንያም አገር፣ በይሁዳ ከተሞች እንዲሁም በኢየሩሳሌም ዙሪያ ባሉ መንደሮች መንጎች እንደ ገና በሚቈጥራቸው ሰው እጅ ሥር ያልፋሉ’ ይላል እግዚአብሔር

14“ ‘ለእስራኤል ቤትና ለይሁዳ ቤት የገባሁትን የተስፋ ቃል የምፈጽምበት ጊዜ ይመጣል’ ይላል እግዚአብሔር

15“ ‘በዚያ ዘመንና በዚያ ጊዜ፣

ከዳዊት ቤት ጻድቅ ቅርንጫፍ አበቅላለሁ፤

በምድሪቱም ፍትሕንና ጽድቅን ያደርጋል።

16በዚያ ዘመን ይሁዳ ይድናል፤

ኢየሩሳሌም በሰላም ትኖራለች፤

የምትጠራበትም ስም፣

እግዚአብሔር ጽድቃችን”

የሚል ይሆናል።’ 17እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘ከዳዊት ዘር በእስራኤል ቤት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ሰው ፈጽሞ አይታጣም፤ 18ሌዋውያን ከሆኑት ካህናትም የሚቃጠል መሥዋዕት ለማቅረብ፣ የእህል ቍርባን ለማቃጠልና ሌላውንም መሥዋዕት ለመሠዋት ሁልጊዜ በፊቴ የሚቆም ሰው አይታጣም።’ ”

19የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 20እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለቀንና ለሌሊት የወሰንሁትን ሥርዐት በማፋለስ ቀንና ሌሊት በተወሰነላቸው ጊዜ እንዳይፈራረቁ ኪዳኔን ማፍረስ ብትችሉ፣ 21በዚያ ጊዜ ከአገልጋዬ ከዳዊት ጋር የገባሁትን ኪዳን፣ እንዲሁም በፊቴ በክህነት ከሚያገለግሉት ሌዋውያን ጋር የገባሁትን ኪዳን ማፍረስ ይቻላል፤ ዳዊትም ከእንግዲህ በዙፋኑ ላይ የሚነግሥ ዘር አይኖረውም። 22የአገልጋዬን የዳዊትን ዘር እንዲሁም በፊቴ የሚቆሙትን ሌዋውያን እንደማይቈጠሩ እንደ ሰማይ ከዋክብትና እንደማይሰፈር የባሕር አሸዋ አበዛቸዋለሁ።’ ”

23የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 24“ይህ ሕዝብ፣ ‘እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሁለቱን መንግሥታት33፥24 ወይም ወገን ጥሏል’ እንደሚሉ አላስተዋልህምን? ሕዝቤን ንቀዋል፤ እንደ ሕዝብም አልቈጠሯቸውም። 25እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የቀንና የሌሊት ኪዳኔን፣ የሰማይንና የምድርንም ሥርዐት ያጸናሁ እኔ ካልሆንሁ፣ 26የያዕቆብንና የአገልጋዬን የዳዊትን ዘር እጥላለሁ፤ ከልጆቹም በአብርሃም፣ በይስሐቅና በያዕቆብ ዘር ላይ ገዥ እንዲሆኑ አልመርጥም፤ ይህንም የምለው ምርኳቸውን ስለምመልስና33፥26 ወይም ከምርኮ እመልሳቸዋለሁ ስለምራራላቸው ነው።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 33:1-26

พระสัญญาว่าจะให้กลับสู่สภาพดี

1ขณะที่เยเรมีย์ยังถูกกักตัวอยู่ที่ลานทหารรักษาพระองค์ พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเขาเป็นครั้งที่สองว่า 2องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงสร้างโลก ผู้ทรงกำหนดรูปร่างและทรงสถาปนามันไว้ ผู้ทรงพระนามว่าพระยาห์เวห์ตรัสดังนี้ 3‘จงร้องเรียกเราและเราจะตอบเจ้า และจะบอกถึงสิ่งที่ยิ่งใหญ่ สิ่งที่เจ้าไม่รู้ และไม่อาจค้นพบได้นั้นแก่เจ้า’ 4ด้วยว่าพระยาห์เวห์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสเกี่ยวกับบ้านเรือนในกรุงนี้และพระราชวังของกษัตริย์ยูดาห์ซึ่งถูกรื้อลงเพื่อใช้ต้านเชิงเทินและดาบ 5ในการต่อสู้กับชาวบาบิโลน33:5 หรือชาวเคลเดียนั้นว่า ‘สถานที่เหล่านี้จะเต็มไปด้วยซากศพของผู้ที่เราประหารด้วยความโกรธและด้วยโทสะของเรา เราจะเบือนหน้าหนีกรุงนี้เพราะความชั่วร้ายทั้งปวงของมัน

6“ ‘อย่างไรก็ตามเราจะนำสุขภาพที่ดีและการบำบัดรักษามายังกรุงนี้ เราจะรักษาประชากรของเรา และจะให้พวกเขาชื่นชมกับสันติสุขและความมั่นคงอย่างล้นเหลือ 7เราจะนำยูดาห์และอิสราเอลกลับมาจากการเป็นเชลย33:7 หรือจะให้ยูดาห์และอิสราเอลกลับสู่สภาพดีดังเดิม และเราจะสร้างพวกเขาขึ้นใหม่ให้เหมือนแต่ก่อน 8เราจะชำระล้างพวกเขาจากบาปทั้งหมดที่พวกเขาได้ทำต่อเรา และให้อภัยบาปทั้งหมดที่พวกเขาได้กบฏต่อเรา 9แล้วกรุงนี้จะนำเกียรติ ความชื่นชมยินดี และคำสรรเสริญมาให้เราต่อหน้ามวลประชาชาติในโลกที่ได้ยินสิ่งดีงามทั้งปวงที่เราทำเพื่อกรุงนี้ พวกเขาจะยำเกรงจนตัวสั่นเมื่อได้เห็นความเจริญรุ่งเรืองและความสงบสุขอันไพบูลย์ซึ่งเราให้แก่กรุงนี้’

10องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘เจ้ากล่าวถึงสถานที่แห่งนี้ว่า “เป็นแดนร้าง ไม่มีคนหรือสัตว์อาศัยอยู่” แต่ในหัวเมืองต่างๆ ของยูดาห์และตามถนนหนทางของเยรูซาเล็มซึ่งถูกทิ้งร้างและไม่มีทั้งคนหรือสัตว์อาศัยอยู่จะมีเสียงให้ได้ยินอีกครั้ง 11คือเสียงรื่นเริงยินดี เสียงเจ้าบ่าวเจ้าสาว เสียงบรรดาผู้นำเครื่องบูชาขอบพระคุณมายังพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้ากล่าวว่า

“ ‘ “ขอบพระคุณพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงประเสริฐ

ความรักของพระองค์ดำรงนิรันดร์”

เพราะเราจะคืนความเจริญรุ่งเรืองแก่กรุงนี้เหมือนแต่ก่อน’ องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนั้น

12“พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสว่า ‘แผ่นดินนี้ซึ่งถูกทิ้งร้างและปราศจากคนและสัตว์ จะมีทุ่งหญ้าในทุกหัวเมืองอีกครั้ง ให้คนเลี้ยงแกะพาฝูงแพะแกะมานอนพักอยู่ 13ในเมืองต่างๆ ของแถบเทือกเขา เชิงเขาด้านตะวันตก เนเกบ ในเขตแดนของเบนยามิน เขตชานกรุงเยรูซาเล็ม และในหัวเมืองต่างๆ ของยูดาห์ จะมีฝูงแพะแกะผ่านไปใต้มือของคนเลี้ยงเพื่อจะนับพวกมันอีกครั้งหนึ่ง’ องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนั้น

14องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘วันนั้นจะมาถึง เมื่อเราจะทำตามพันธสัญญาที่เต็มไปด้วยพระคุณซึ่งเราได้ให้ไว้แก่พงศ์พันธุ์อิสราเอลและพงศ์พันธุ์ยูดาห์

15“ ‘เมื่อถึงเวลานั้น เราจะให้กิ่งอันชอบธรรม

ออกมาจากเชื้อสายของดาวิด

เขาจะผดุงความถูกต้องและเที่ยงธรรมในดินแดน

16เมื่อถึงเวลานั้น ยูดาห์จะได้รับความรอด

และเยรูซาเล็มจะอาศัยอยู่อย่างปลอดภัย

ผู้นั้นจะได้รับการขนานนามว่า

พระยาห์เวห์ผู้ทรงเป็นความชอบธรรมของเรา’

17เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘ดาวิดจะไม่ขาดคนครองบัลลังก์ของพงศ์พันธุ์อิสราเอล 18ทั้งปุโรหิตซึ่งอยู่ในเผ่าเลวีก็จะไม่ขาดคนที่ยืนอยู่ตรงหน้าเรา เพื่อถวายเครื่องเผาบูชา ธัญบูชา และเครื่องถวายอื่นๆ’ ”

19พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ว่า 20องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘หากเจ้าเลิกล้มพันธสัญญาที่เรามีต่อกลางวันและกลางคืน จนทำให้วันและคืนไม่ได้มาถึงตามกำหนดเวลาปกติได้ 21เมื่อนั้นคำมั่นสัญญาของเราที่ให้แก่ดาวิดผู้รับใช้ของเราและแก่ชนเลวีซึ่งเป็นปุโรหิตปฏิบัติหน้าที่ต่อหน้าเรา ก็จะเลิกล้มได้เช่นกัน และดาวิดก็จะไม่มีเชื้อสายที่จะครองบัลลังก์ของเขาอีก 22เราจะทำให้วงศ์วานของดาวิดผู้รับใช้ของเราและชนเลวีซึ่งปฏิบัติหน้าที่ต่อหน้าเรานั้นมีจำนวนเกินกว่าจะนับได้ ดั่งดวงดาวในท้องฟ้าและเม็ดทรายที่ชายฝั่งทะเล’ ”

23พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ว่า 24“เจ้าไม่ได้สังเกตหรือว่าคนเหล่านี้พูดกันว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทอดทิ้งสองอาณาจักร33:24 หรือครอบครัวที่พระองค์ทรงเลือกสรรไว้แล้ว’? เขาจึงดูหมิ่นประชากรของเรา ไม่ยอมรับเป็นชาติหนึ่งอีกต่อไป 25องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘หากเราไม่ได้สถาปนาพันธสัญญาที่เรามีต่อกลางวันและกลางคืน และไม่ได้กำหนดกฎเกณฑ์ของฟ้าสวรรค์และโลกไว้ 26เมื่อนั้นเราจึงจะทอดทิ้งวงศ์วานของยาโคบและดาวิดผู้รับใช้ของเรา และจะไม่เลือกบุตรคนหนึ่งของเขาขึ้นปกครองวงศ์วานของอับราฮัม อิสอัค และยาโคบ เพราะเราจะให้พวกเขากลับสู่สภาพดีดังเดิม33:26 หรือจะนำพวกเขากลับมาจากการเป็นเชลย และจะเมตตาสงสารเขา’ ”