ኤርምያስ 34 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 34:1-22

ለሴዴቅያስ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

1የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆርና ሰራዊቱ ሁሉ፣ በግዛቱም ሥር ያሉ መንግሥታትና ሕዝቦች ሁሉ ኢየሩሳሌምንና በአካባቢዋ የሚገኙትን ከተሞች ይወጉ በነበረ ጊዜ፣ እንዲህ የሚል ቃል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 2“የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሴዴቅያስ ሄደህ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ይህችን ከተማ ለባቢሎን ንጉሥ አሳልፌ ልሰጣት ነው፤ እርሱም በእሳት ያቃጥላታል፤ 3አንተም በርግጥ ትያዛለህ፤ ዐልፈህም ለእርሱ ትሰጣለህ እንጂ ከእጁ አታመልጥም። የባቢሎንን ንጉሥ በዐይኖችህ ታየዋለህ፤ ፊት ለፊትም ያነጋግርሃል፤ ወደ ባቢሎንም ትሄዳለህ።

4“ ‘ነገር ግን፣ የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ እግዚአብሔር ስለ አንተ እንዲህ ይላል፤ በሰይፍ አትሞትም፤ 5በሰላም ትሞታለህ። ሕዝቡ ከአንተ በፊት ለነበሩት ነገሥታት አባቶችህ ክብር በቀብራቸው ጊዜ እሳት እንዳነደዱ፣ በቀብርህም ጊዜ ስለ ክብርህ እሳት ያነድዳሉ፤ “ዋይ ዋይ ጌታችን!” እያሉም ያለቅሱልሃል፤ እኔ ራሴ ይህን ቃል ተናግሬአለሁና፤ ይላል እግዚአብሔር።’ ”

6ነቢዩ ኤርምያስ ይህን ሁሉ ለይሁዳ ንጉሥ ለሴዴቅያስ በኢየሩሳሌም ነገረው፤ 7በዚህም ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ ሰራዊት ኢየሩሳሌምንና የቀሩትን የይሁዳ ከተሞች ለኪሶንና ዓዜቃን እየወጋ ነበር፤ ከተመሸጉት የይሁዳ ከተሞችም የቀሩት እነዚሁ ብቻ ነበሩና።

የባሪያዎች ነጻ አለመውጣት

8ንጉሡ ሴዴቅያስ ባሪያዎችን ነጻ ለማውጣት ከኢየሩሳሌም ሕዝብ ሁሉ ጋር ቃል ኪዳን ካደረገ በኋላ፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ። 9እያንዳንዱ ሰው፣ ዕብራዊ የሆነውን ወንድ ባሪያውንና ዕብራዊት የሆነችውን ሴት ባሪያውን ነጻ ማውጣት ነበረበት፤ ማንም ሰው አይሁዳዊ ወንድሙን በባርነት መግዛት አልነበረበትም። 10በዚህ ቃል ኪዳን የተስማሙት ባለሥልጣኖችና ሕዝቡ ሁሉ ወንድ ወይም ሴት ባሪያዎቻቸውን ነጻ ለመልቀቅና ከእንግዲህ ባሪያ አድርገው ላይገዟቸው ተስማሙ። 11በኋላ ግን ሐሳባቸውን ቀይረው ነጻ የለቀቋቸው ባሪያዎቻቸውን እንዲመለሱ አደረጓቸው፤ እንደ ገናም ባሪያ አድርገው ገዟቸው።

12ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 13“የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በባርነት ከተገዙበት ከግብፅ ምድር ባወጣኋቸው ጊዜ፣ ከአባቶቻችሁ ጋር እንዲህ ብዬ ቃል ኪዳን አደረግሁ፤ 14“ራሱን በባርነት ለእናንተ የሸጠውን ዕብራዊ ወንድማችሁን እያንዳንዳችሁ በየሰባት ዓመቱ ነጻ ትለቅቃላችሁ፤ ስድስት ዓመት ከተገዛላችሁ በኋላ ነጻ ታወጡታላችሁ።”34፥14 ዘዳ 15፥12 አባቶቻችሁ ግን አልሰሙኝም ጆሯቸውንም ወደ እኔ አላዘነበሉም። 15እናንተም አሁን ንስሓ በመግባት በፊቴ ትክክለኛ ነገር አደረጋችሁ፤ እያንዳንዳችሁም ለወገኖቻችሁ ነጻነት ዐወጃችሁ፤ ስሜ በሚጠራበት ቤትም በፊቴ ቃል ኪዳን ገባችሁ። 16ነገር ግን ተመልሳችሁ ስሜን አረከሳችሁ፤ ወደ ፈለጉበት እንዲሄዱ ነጻ የለቀቃችኋቸውንም ወንዶችና ሴቶች ባሪያዎቻችሁን መለሳችሁ፤ እንደ ገናም ባሪያዎቻችሁ አደረጋችኋቸው።’

17“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ለወንድሞቻችሁና ለወገኖቻችሁ ነጻነት አላወጃችሁምና አልታዘዛችሁኝም። እንግዲህ እኔ ነጻነት ዐውጅላችኋለሁ፤’ ይላል እግዚአብሔር። ‘ይኸውም በሰይፍ፣ በቸነፈርና በራብ የምትወድቁበት ነጻነት ነው። ለምድር መንግሥታት ሁሉ መሠቀቂያ አደርጋችኋለሁ። 18ኪዳኔን ያፈረሱትንና በፊቴ የገቡትን የኪዳኑን ቃል ያልፈጸሙትን ሰዎች ሥጋውን ሁለት ቦታ ከፍለው በመካከሉ እንዳለፉት፣ እንደ እንቦሳው አደርጋቸዋለሁ። 19የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን መሪዎች፣ የቤተ መንግሥቱን ባለሟሎች፣ ካህናቱንና በእንቦሳው ሥጋ መካከል ያለፉትን ሕዝብ ሁሉ፣ 20ነፍሳቸውን ለሚሹ ጠላቶቻቸው አሳልፌ እሰጣለሁ፤ ሬሳቸውም ለሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት መብል ይሆናል።

21“ ‘የይሁዳን ንጉሥ ሴዴቅያስንና መኳንንቱን፣ ነፍሳቸውን ለሚሹ ጠላቶቻቸው ይኸውም ለጊዜው እናንተን ከመውጋት ለተመለሱ ለባቢሎን ንጉሥ ሰራዊት አሳልፌ እሰጣለሁ። 22እነሆ፤ አዝዛቸዋለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር፤ ወደዚህችም ከተማ እንደ ገና እመልሳቸዋለሁ። እነርሱም ይወጓታል፤ ይይዟታል፤ በእሳትም ያቃጥሏታል። የይሁዳንም ከተሞች ሰው የማይኖርባቸው፣ ባድማ አደርጋቸዋለሁ።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 34:1-22

พระดำรัสเตือนเศเดคียาห์

1ขณะที่กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนและกองทัพของพระองค์กับมวลอาณาจักรและประชาชนในจักรวรรดิที่ทรงปกครองกำลังสู้รบกับเยรูซาเล็มและหัวเมืองต่างๆ โดยรอบ ก็มีพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ความว่า 2“พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสดังนี้ว่า จงไปบอกกษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์ว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ เรากำลังจะยกเมืองนี้ให้กษัตริย์บาบิโลน และเขาจะเผามันเสีย 3เจ้าจะหนีไม่พ้นมือเขา แต่จะถูกจับกุมตัวไปให้เขาอย่างแน่นอน เจ้าจะเห็นกษัตริย์บาบิโลนกับตา และเขาจะพูดกับเจ้าซึ่งๆ หน้าและเจ้าจะไปยังบาบิโลน

4“ ‘แต่จงฟังพระสัญญาขององค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด กษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์เอ๋ย องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสเกี่ยวกับเจ้าดังนี้ว่า เจ้าจะไม่ตายเพราะสงคราม 5เจ้าจะตายอย่างสงบสุข และประชาชนจะเผาเครื่องหอมเป็นเกียรติแก่เจ้าเหมือนที่ได้ทำแก่บรรพบุรุษของเจ้าซึ่งเป็นกษัตริย์ที่ครองราชย์ก่อนเจ้า เขาจะร่ำไห้อาลัยเจ้าว่า “โอ้ อนิจจา กษัตริย์ของเรา!” เราเองได้สัญญาไว้ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น’ ”

6แล้วผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์จึงทูลทุกอย่างต่อกษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์ในเยรูซาเล็ม 7ขณะที่กองทัพบาบิโลนกำลังสู้รบกับเยรูซาเล็มและสู้รบกับลาคิชและอาเซคาห์ซึ่งเป็นหัวเมืองป้อมปราการที่ยังคงต่อสู้อยู่ในยูดาห์

เสรีภาพสำหรับทาส

8พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์หลังจากที่กษัตริย์เศเดคียาห์ทรงทำสัญญากับประชาชนในเยรูซาเล็มว่าจะประกาศให้เสรีภาพแก่ทาสทั้งปวง 9ให้ทุกคนปล่อยทาสฮีบรู ไม่ว่าชายหรือหญิง อย่าให้ผู้ใดทำให้ชาวยิวซึ่งเป็นพี่น้องร่วมชาติตกเป็นทาส 10ดังนั้นบรรดาข้าราชบริพารและประชาชนทั้งปวงที่เข้าร่วมในพันธสัญญานี้จึงเห็นพ้องต้องกันที่จะปลดปล่อยทาสชายหญิงของตนให้พ้นจากข้อผูกมัดทุกประการ 11แต่หลังจากนั้นพวกเขาก็เปลี่ยนใจ และจับทาสที่ปล่อยเป็นไทแล้วกลับมาเป็นทาสอีก

12ฉะนั้นจึงมีพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ว่า 13“พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสดังนี้ว่า เราได้ทำพันธสัญญากับบรรพบุรุษของพวกเจ้าเมื่อเรานำคนเหล่านั้นออกมาจากอียิปต์ซึ่งเป็นดินแดนทาส เราสั่งไว้ว่า 14‘ทุกปีที่เจ็ดพวกเจ้าทุกคนต้องปลดปล่อยพี่น้องชาวฮีบรูซึ่งขายตัวเองเป็นทาสของเจ้า หลังจากที่เขารับใช้เจ้ามาตลอดหกปีแล้ว พวกเจ้าต้องปล่อยเขาเป็นไท’34:14 ฉธบ.15:12 แต่บรรพบุรุษของเจ้าทั้งหลายไม่ยอมใส่ใจ ไม่ยอมฟังคำของเรา 15เมื่อเร็วๆ นี้ เจ้าสำนึกผิดและทำสิ่งที่ถูกต้องในสายตาของเรา เจ้าแต่ละคนประกาศให้เสรีภาพแก่พี่น้องร่วมชาติของตน เจ้าถึงกับทำสัญญาต่อหน้าเราในวิหารซึ่งใช้นามของเรา 16แต่บัดนี้เจ้ากลับคำและลบหลู่นามของเรา พวกเจ้าแต่ละคนบังคับทาสชายหญิงซึ่งเจ้าได้ปลดปล่อยให้เป็นอิสระและให้ไปไหนมาไหนได้ตามใจชอบนั้น กลับมาเป็นทาสของเจ้าอีก

17“ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า เจ้าไม่ได้เชื่อฟังเรา ไม่ได้ประกาศให้อิสรภาพแก่พี่น้องร่วมชาติของเจ้า ดังนั้นเราขอประกาศให้ ‘เสรีภาพ’ แก่เจ้า องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ ‘เสรีภาพ’ที่จะล้มตายด้วยสงคราม โรคระบาด และการกันดารอาหาร เราจะทำให้เจ้าเป็นที่รังเกียจเดียดฉันท์แก่มวลอาณาจักรในโลกนี้ 18ผู้ที่ละเมิดพันธสัญญาของเรา และไม่ทำตามข้อกำหนดของพันธสัญญาซึ่งให้ไว้ต่อหน้าเรา เราจะปฏิบัติต่อพวกเขาเหมือนวัวที่ถูกผ่าออกเป็นสองท่อนและเดินผ่ากลาง 19บรรดาผู้นำของยูดาห์และเยรูซาเล็ม ข้าราชสำนัก ปุโรหิต และประชากรทั้งปวง ที่เดินผ่ากลางสองท่อนของวัวนั้น 20เราจะมอบพวกเขาให้แก่ศัตรูผู้หมายเอาชีวิตของพวกเขา ซากศพของพวกเขาจะตกเป็นเหยื่อของสัตว์ป่าและนกในอากาศ

21“เราจะมอบกษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์และข้าราชบริพารของเขาแก่ศัตรูผู้ที่มุ่งเอาชีวิตเขาแก่กองทัพกษัตริย์บาบิโลน ซึ่งได้ถอนทัพไปจากพวกเจ้า 22องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่าเราจะออกคำสั่งและเราจะนำพวกเขากลับมากรุงนี้อีก พวกเขาจะมาต่อสู้ เอาชนะและเผาเมืองเสีย เราจะทำให้หัวเมืองต่างๆ ของยูดาห์ถูกทิ้งร้าง ไม่มีใครอาศัยอยู่”