ኤርምያስ 28 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 28:1-17

ሐሰተኛው ነቢይ ሐናንያ

1በዚያው ዓመት የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ እንደ ነገሠ በአራተኛው ዓመት፣ አምስተኛ ወር፣ የገባዖኑ ሰው የዓዙር ልጅ ነቢዩ ሐናንያ በእግዚአብሔር ቤት፣ በካህናቱና በሕዝቡ ሁሉ ፊት እንዲህ አለኝ፤ 2“የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የባቢሎን ንጉሥ የጫነባችሁን ቀንበር እሰብራለሁ፤ 3የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ከእግዚአብሔር ቤት ወደ ባቢሎን የወሰዳቸውን ዕቃዎች ሁሉ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ መልሼ አመጣለሁ። 4የይሁዳንም ንጉሥ የኢዮአቄምን ልጅ ኢኮንያንን፣28፥4 ወይም ኢዮአኪን ይላል። ሌሎች ከይሁዳ ወደ ባቢሎን ተማርከው የተወሰዱትንም ሁሉ ወደዚህ ስፍራ እመልሳለሁ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘የባቢሎን ንጉሥ የጫነባቸውን ቀንበር እሰብራለሁና።’ ”

5ነቢዩ ኤርምያስም በካህናቱና በእግዚአብሔር ቤት ቆመው በነበሩት ሕዝብ ሁሉ ፊት፣ ለነቢዩ ለሐናንያ እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ 6“አሜን፤ እግዚአብሔር ያድርገው፤ የእግዚአብሔርን ቤት ዕቃ ሁሉ፣ ተማርከው የተወሰዱትንም ምርኮኞች ሁሉ ከባቢሎን በመመለስ፣ እግዚአብሔር የተናገርኸውን ቃል ይፈጽም። 7ነገር ግን ለአንተም ለዚህም ሕዝብ የምናገረውን ቃል ስማ፤ 8ከአንተና ከእኔ በፊት ጥንት የተነሡ ነቢያት፣ በብዙ አገሮችና በታላላቅ መንግሥታት ላይ ስለ ጦርነት፣ ስለ ጥፋትና ስለ መቅሠፍት ትንቢት ተናግረዋል። 9ነገር ግን ስለ ሰላም ትንቢት የተናገረ ነቢይ እግዚአብሔር በእውነት እንደ ላከው የሚታወቀው የተናገረው ትንቢት ሲፈጸም ነው።”

10ነቢዩም ሐናንያ ቀንበሩን ከነቢዩ ኤርምያስ ዐንገት ወስዶ ሰበረው፤ 11በሕዝቡም ፊት፣ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የባቢሎንን ንጉሥ የናቡከደነፆርን ቀንበር ከሕዝቡ ሁሉ ጫንቃ ላይ ልክ እንደዚህ እሰብራለሁ’ ” አለ። በዚህ ጊዜ፣ ነቢዩ ኤርምያስ ትቶት መንገዱን ቀጠለ።

12ነቢዩም ሐናንያ ቀንበሩን ከነቢዩ ከኤርምያስ ዐንገት ወስዶ ከሰበረ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ፤ 13“ሄደህ ለሐናንያ እንዲህ ብለህ ንገረው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ አንተ የዕንጨት ቀንበር ሰብረሃል፤ እኔ ግን በምትኩ የብረት ቀንበር እሠራለሁ። 14የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የባቢሎንን ንጉሥ ናቡከደነፆርን እንዲያገለግሉ፣ በእነዚህ ሕዝቦች ላይ የብረት ቀንበር አደርጋለሁ፤ እነርሱም ይገዙለታል፤ በዱር አራዊት ላይ እንኳ ሥልጣን እሰጠዋለሁ።’ ”

15ነቢዩ ኤርምያስም ለነቢዩ ሐናንያ እንዲህ አለው፤ “ሐናንያ ሆይ፤ ስማ! እግዚአብሔር ሳይልክህ ይህ ሕዝብ በሐሰት እንዲታመን አድርገሃል፤ 16ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘ከምድር ገጽ አስወግድሃለሁ፤ በእግዚአብሔርም ላይ ዐመፅ ተናግረሃልና፣ በዚህ ዓመት ትሞታለህ።’ ”

17ነቢዩም ሐናንያ በዚያው ዓመት በሰባተኛው ወር ሞተ።

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 28:1-17

ฮานันยาห์ผู้พยากรณ์เท็จ

1ในเดือนที่ห้าปีเดียวกันนั้น ซึ่งเป็นปีที่สี่ของรัชกาลกษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์ ผู้พยากรณ์ฮานันยาห์บุตรอัสซูร์ซึ่งมาจากกิเบโอน กล่าวกับข้าพเจ้าในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าต่อหน้าบรรดาปุโรหิตและประชากรทั้งปวงว่า 2“พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ‘เราจะหักแอกของกษัตริย์บาบิโลน 3เราจะนำภาชนะต่างๆ ซึ่งกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนริบจากพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าไปไว้ที่บาบิโลนนั้นกลับคืนมาที่นี่ภายในสองปี 4และเราจะนำเยโฮยาคีนโอรสของกษัตริย์เยโฮยาคิมแห่งยูดาห์ กับบรรดาเชลยจากยูดาห์ซึ่งไปยังบาบิโลนนั้นกลับมาที่นี่อีก เพราะเราจะทำลายแอกของกษัตริย์บาบิโลน’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น”

5แล้วผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์กล่าวกับฮานันยาห์ต่อหน้าปุโรหิตและประชากรทั้งปวงซึ่งยืนอยู่ในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้า 6เขากล่าวว่า “อาเมน! ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงทำเช่นนั้นเถิด! ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงโปรดให้เป็นไปตามคำพยากรณ์ของท่าน ที่พระองค์จะทรงนำภาชนะประจำพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า และเชลยทั้งปวงจากบาบิโลนคืนสู่แผ่นดินนี้ 7แต่ขอจงฟังสิ่งที่ข้าพเจ้าต้องกล่าวให้ท่านและประชาชนทั้งปวงได้ยินคือ 8ตั้งแต่กาลก่อนบรรดาผู้เผยพระวจนะก่อนหน้าท่านและข้าพเจ้าได้พยากรณ์ถึงสงคราม ภัยพิบัติ และโรคระบาด ซึ่งจะเกิดขึ้นในหลายประเทศและอาณาจักรที่ยิ่งใหญ่ทั้งหลาย 9แต่ผู้เผยพระวจนะซึ่งพยากรณ์ถึงสันติภาพนั้นจะได้รับการยอมรับว่าเป็นผู้ที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงใช้มาจริงๆ ก็ต่อเมื่อคำพยากรณ์ของเขาเป็นจริง”

10แล้วผู้เผยพระวจนะฮานันยาห์ จึงปลดแอกจากคอของผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์แล้วหักทิ้งเสีย 11แล้วกล่าวต่อหน้าประชาชนทั้งปวงว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘ในทำนองเดียวกัน เราจะทำลายแอกของกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนออกจากคอของบรรดาประชาชาติภายในสองปี’ ” ถึงตอนนี้ผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์ก็เดินจากไป

12ไม่นานหลังจากที่ผู้เผยพระวจนะฮานันยาห์ได้ทำลายแอกจากคอของผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์ พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้าก็มาถึงเยเรมีย์ว่า 13“จงไปบอกฮานันยาห์ว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสดังนี้ว่า เจ้าหักแอกไม้ออก แต่เจ้าจะได้แอกเหล็กแทน 14พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสดังนี้ว่า เราจะวางแอกเหล็กบนคอของประชาชาติเหล่านี้ และให้พวกเขาปรนนิบัติรับใช้กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลน และพวกเขาจะรับใช้เนบูคัดเนสซาร์ แม้แต่สัตว์ป่า เราก็จะทำให้สยบต่อเนบูคัดเนสซาร์ด้วยเช่นกัน’ ”

15แล้วผู้เผยพระวจนะเยเรมีย์กล่าวแก่ผู้เผยพระวจนะฮานันยาห์ว่า “ฮานันยาห์ จงฟัง! องค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ใช้ท่านมา แต่ท่านก็ยังโน้มน้าวชนชาตินี้ให้เชื่อคำโกหกพกลม 16ฉะนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า ‘เราจะกำจัดเจ้าไปจากพื้นโลก เจ้าจะตายในปีนี้ เพราะเจ้าได้สอนให้กบฏต่อองค์พระผู้เป็นเจ้า’ ”

17ในเดือนที่เจ็ดของปีนั้นเองผู้เผยพระวจนะฮานันยาห์ก็สิ้นชีวิต