ኤርምያስ 27 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 27:1-22

የይሁዳ በናቡከደነፆር ሥር መውደቅ

1በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በሴዴቅያስ27፥1 ጥቂት የዕብራይስጥ ጽሑፎችና የሱርሰት ትርጕም (ኤር 27፥312 እና 28፥1 ይመ)፣ አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ኢዮአቄም ይላሉ (አብዛኛዎቹ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች ይህ ጥቅስ ቍጥር የላቸውም)። ዘመነ መንግሥት መጀመሪያ ላይ ይህ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 2እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “የዕንጨት ቀንበር ሠርተህ በጠፍር ማነቆ አያይዘውና በዐንገትህ አስገባው፤ 3ወደ ይሁዳ ንጉሥ ወደ ሴዴቅያስ፣ ወደ ኢየሩሳሌም በመጡት ሰዎች በኩል ለኤዶም፣ ለሞዓብ፣ ለአሞን፣ ለጢሮስና ለሲዶና ነገሥታት መልእክት ላክ። 4ለጌቶቻቸውም እንዲያሳውቁ እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ‘የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ለጌቶቻችሁ ይህን ንገሯቸው፤ 5በታላቁ ኀይሌና በተዘረጋው ክንዴ ምድርን፣ በላይዋ የሚኖሩትን ሰዎችና እንስሳት ፈጥሬአለሁ፤ ለምወድደውም እሰጣለሁ። 6አሁንም እነዚህን አገሮች ሁሉ ለአገልጋዬ ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር አሳልፌ እሰጣለሁ፤ የዱር አራዊት እንኳ እንዲገዙለት አደርጋለሁ። 7የእርሱ አገር በተራው ለሌሎች እስከሚገዛበት ጊዜ ድረስ፣ ሕዝቦች ሁሉ ለእርሱ፣ ለልጁና ለልጅ ልጁ ይገዛሉ፤ በዚያን ጊዜ ብዙ ሕዝቦችና ታላላቅ ነገሥታት እርሱን ይገዙታል።

8“ ‘ “ነገር ግን ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደነፆር የማይገዛ፣ ዐንገቱንም ከቀንበሩ በታች ዝቅ የማያደርግ ማንኛውንም ሕዝብ ወይም መንግሥት በእጁ እስከማጠፋው ድረስ በሰይፍና በራብ፣ በመቅሠፍትም እቀጣዋለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር9ስለዚህ፣ ‘የባቢሎንን ንጉሥ አታገለግሉም’ የሚሏችሁን ነቢያታችሁን፣ ሟርተኞቻችሁን፣ ሕልመኞቻችሁን፤ መናፍስት ጠሪዎቻችሁንና መተተኞቻቸሁን አትስሙ፤ 10ከምድራችሁ እንድትፈናቀሉ፣ እኔም እንዳሳድዳችሁና እንዳጠፋችሁ የሐሰት ትንቢት ይነግሯችኋልና። 11ነገር ግን ከባቢሎን ንጉሥ ቀንበር በታች ዐንገቱን ዝቅ የሚያደርገውንና የሚያገለግለውን ማንኛውንም ሕዝብ በገዛ ምድሩ እንዲቀርና እያረሰም በዚያ እንዲኖር አደርገዋለሁ፤ ይላል እግዚአብሔር።” ’ ”

12ለይሁዳ ንጉሥ ለሴዴቅያስም ይህንኑ መልእክት እንዲህ ብዬ ነገርሁት፤ “ዐንገታችሁን ከባቢሎን ንጉሥ ቀንበር በታች ዝቅ አድርጉ፤ እርሱንና ሕዝቡን አገልግሉ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ። 13አንተና ሕዝብህ፣ እግዚአብሔር ለባቢሎን ንጉሥ አልገዛም ያለውን ሕዝብ ባስጠነቀቀበት በሰይፍ፣ በራብና በመቅሠፍት ለምን ታልቃላችሁ? 14ሐሰተኛ ትንቢት ስለሚነግሯችሁ፣ ‘የባቢሎንን ንጉሥ አታገለግሉም’ የሚሏችሁን ነቢያት አትስሙ፤ 15‘እኔ አልላክኋቸውም’ ይላል እግዚአብሔር ‘የሐሰት ትንቢት በስሜ ይናገራሉ፤ ስለዚህ እናንተንና ትንቢት የሚናገሩላችሁን ነቢያት አሳድዳለሁ፤ እናንተም ትጠፋላችሁ።’ ”

16እኔም ለካህናቱና ለዚህ ሕዝብ ሁሉ እንዲህ አልሁ፤ “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የእግዚአብሔር ቤት ዕቃ ከባቢሎን ቶሎ ይመለሳል’ የሚሏችሁን ነቢያት አትስሟቸው፤ የሚነግሯችሁ የሐሰት ትንቢት ነውና። 17ስለዚህ እነርሱን መስማት ትታችሁ ለባቢሎን ንጉሥ ተገዙ፤ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ ባለመታዘዛችሁስ ይህች ከተማ ለምን ትፈራርስ? 18እውነተኞች ነቢያት ከሆኑና በርግጥ የእግዚአብሔር ቃል ካላቸው፣ በእግዚአብሔር ቤትና በይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት በኢየሩሳሌምም የቀሩት ዕቃዎች ወደ ባቢሎን እንዳይወሰዱ ወደ ሰራዊት ጌታ ወደ እግዚአብሔር እስቲ ይማልዱ! 19የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በዚህች ከተማ ስለ ቀሩት ዐምዶች፣ ከናስ ስለ ተሠራው ትልቁ ገንዳ፣ ስለ ተንቀሳቃሽ ማስቀመጫዎችና ስለ ሌሎቹም ዕቃዎች እንዲህ ይላልና፤ 20የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር የይሁዳን ንጉሥ የኢዮአቄምን ልጅ ኢኮንያንን፣27፥20 ኢኮንያን የኢዮአኪን ሌላው አቻ ስም ነው። ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ መኳንንት ጋር ማርኮ ወደ ባቢሎን በወሰደ ጊዜ እነዚህ በከተማዪቱ የቀሩ ዕቃዎች ስለሆኑ፣ 21በእግዚአብሔር ቤትና በይሁዳ ንጉሥ ቤተ መንግሥት በኢየሩሳሌምም ስለ ቀሩት ዕቃዎች፣ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ 22‘ወደ ባቢሎን ይወሰዳሉ፤ እስከምጐበኛቸውም ቀን ድረስ በዚያ ይቀመጣሉ’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘በዚያ ጊዜም እመልሳቸዋለሁ፤ ወደዚህም ስፍራ አመጣቸዋለሁ።’ ”

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 27:1-22

ยูดาห์จะปรนนิบัติเนบูคัดเนสซาร์

1ในต้นรัชกาลเศเดคียาห์27:1 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูส่วนใหญ่ว่าเยโฮยาคิม(ดู 27:3,12 และ 18:1)โอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ มีพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ความว่า 2องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงทำแอกจากไม้พร้อมสายรัดแล้วคล้องคอเจ้าไว้ 3และฝากข้อความไปถึงกษัตริย์เอโดม โมอับ อัมโมน ไทระ และไซดอนผ่านทางบรรดาทูตซึ่งมาเฝ้ากษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์ที่เยรูซาเล็ม 4ให้ไปทูลเจ้านายของตนว่า ‘พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า “จงไปบอกนายของเจ้าว่า 5เราได้สร้างโลก มนุษย์ และสัตว์ต่างๆ ในโลกนี้ โดยฤทธิ์อำนาจอันยิ่งใหญ่และมือที่เงื้ออยู่ และเรายกสิ่งเหล่านี้แก่ใครก็ได้ที่เราพอใจ 6บัดนี้เราจะมอบแผ่นดินทั้งปวงของพวกเจ้าให้แก่กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนผู้รับใช้ของเรา แม้แต่สัตว์ป่าเราก็จะทำให้ยอมสยบต่อเขา 7ประชาชาติทั้งปวงจะรับใช้เขาและลูกหลานของเขาจนกว่าจะหมดเวลาของเขา จากนั้นประชาชาติต่างๆ และเหล่ากษัตริย์ผู้ยิ่งใหญ่จะพิชิตบาบิโลน

8“ ‘ “แต่หากชนชาติใดหรืออาณาจักรใดไม่ยอมปรนนิบัติรับใช้กษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลน หรือไม่ยอมอยู่ใต้แอกของเขา เราจะลงโทษชนชาตินั้นด้วยสงคราม การกันดารอาหาร และโรคระบาด จนกว่าเราจะทำลายชาตินั้นให้สิ้นไปด้วยมือเนบูคัดเนสซาร์ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น 9เพราะฉะนั้นอย่าไปฟังผู้พยากรณ์ หมอดู ผู้ทำนายฝัน คนทรง และหมอผีของพวกเจ้า ผู้ที่บอกว่า ‘เจ้าจะไม่ต้องเป็นข้ารับใช้กษัตริย์บาบิโลน’ 10พวกเขาพยากรณ์เท็จให้เจ้าฟัง ซึ่งมีแต่จะทำให้เจ้าพลัดพรากจากดินแดนของเจ้า เราจะเนรเทศเจ้าไปและเจ้าจะพินาศ 11แต่ถ้าชาติใดยอมค้อมคออยู่ใต้แอกของกษัตริย์บาบิโลนและปรนนิบัติรับใช้เขา เราจะอนุญาตให้ชาตินั้นคงอยู่ในดินแดนของตน ทำไร่ไถนาอาศัยอยู่ต่อไป องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น” ’ ”

12ข้าพเจ้าได้แจ้งข้อความเดียวกันแก่กษัตริย์เศเดคียาห์แห่งยูดาห์คือ “จงค้อมคออยู่ใต้แอกของกษัตริย์บาบิโลน ปรนนิบัติรับใช้เขากับราษฎรของเขา แล้วท่านจะมีชีวิตรอด 13ทำไมท่านกับเหล่าประชากรจะต้องตายเพราะสงคราม การกันดารอาหาร และโรคระบาด ซึ่งองค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสไว้ว่าจะตกอยู่แก่ชนชาติใดก็ตามที่ไม่ยอมสวามิภักดิ์ต่อกษัตริย์บาบิโลนเล่า? 14อย่าไปฟังบรรดาผู้พยากรณ์ที่บอกกับท่านว่า ‘พวกเจ้าจะไม่ต้องรับใช้กษัตริย์บาบิโลน’ เพราะพวกเขาพยากรณ์เท็จให้เจ้าฟัง 15องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า ‘เราไม่ได้ส่งพวกเขามา เขาพยากรณ์เท็จให้เจ้าฟังโดยอ้างนามของเรา ฉะนั้นเราจะเนรเทศเจ้าไปและเจ้าจะพินาศ ทั้งเจ้าและบรรดาผู้เผยพระวจนะซึ่งพยากรณ์ให้เจ้าฟัง’ ”

16แล้วข้าพเจ้ากล่าวแก่บรรดาปุโรหิตและประชากรทั้งปวงว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า อย่าไปฟังถ้อยคำต่างๆ ที่ผู้พยากรณ์กล่าวว่า ‘ในไม่ช้าภาชนะซึ่งถูกริบจากพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าจะได้คืนมาจากบาบิโลน’ พวกเขากำลังพยากรณ์เท็จให้เจ้าฟัง 17อย่าไปฟังเลย จงยอมรับใช้กษัตริย์บาบิโลน แล้วพวกท่านจะรักษาชีวิตไว้ได้ จะยอมให้เมืองนี้เป็นซากปรักหักพังไปทำไม? 18หากคนเหล่านั้นเป็นผู้เผยพระวจนะและมีพระดำรัสจากองค์พระผู้เป็นเจ้า ก็ให้พวกเขาอธิษฐานต่อพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ ไม่ให้ภาชนะเครื่องใช้ต่างๆ ที่เหลืออยู่ในพระวิหารขององค์พระผู้เป็นเจ้า ในวังของกษัตริย์ยูดาห์ และในเยรูซาเล็มต้องถูกริบไปบาบิโลน 19เพราะพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ตรัสเกี่ยวกับเสาหาน ขันสาคร แท่นเคลื่อนที่ และเครื่องตกแต่งอื่นๆ ที่ยังเหลืออยู่ในเมืองนี้ 20ซึ่งกษัตริย์เนบูคัดเนสซาร์แห่งบาบิโลนไม่ได้ริบไป เมื่อครั้งที่เยโฮยาคีน27:20 ภาษาฮีบรูว่าเยโคนิยาห์เป็นอีกรูปหนึ่งของเยโฮยาคีนโอรสกษัตริย์เยโฮยาคิมแห่งยูดาห์ถูกจับไปเป็นเชลยที่บาบิโลนพร้อมกับบรรดาเจ้าขุนมูลนายของยูดาห์และเยรูซาเล็มนั้น 21พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสเกี่ยวกับสิ่งต่างๆ ที่เหลืออยู่ในพระนิเวศขององค์พระผู้เป็นเจ้าในราชวังกษัตริย์ยูดาห์และในเยรูซาเล็มไว้ดังนี้ 22‘สิ่งต่างๆ เหล่านี้จะถูกริบไปไว้ที่บาบิโลนจนกว่าจะถึงวันที่เรามาเยือน แล้วเราจึงจะนำมันกลับมายังที่เดิม’ องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น”