ኤርምያስ 19 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 19:1-15

1እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ሄደህ፣ ከሸክላ ሠሪ ገንቦ ግዛ፤ ከሕዝቡና ከካህናቱ መካከል ታላላቅ የሆኑትን አንዳንዶቹን ይዘህ፣ 2በገል በር መግቢያ አጠገብ ወዳለው ወደ ሄኖም ልጅ ሸለቆ ውጣ። በዚያም የምነግርህን ቃል ተናገር፤ 3እንዲህም በል፤ ‘የይሁዳ ነገሥታትና በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ለሰሚው ሁሉ ጆሮ የሚዘገንን ክፉ ነገር እነሆ በዚህ ስፍራ አመጣለሁ፤ 4እኔን ትተውኝ፣ ይህን ስፍራ የባዕድ አማልክት ቦታ አድርገውታልና። እነርሱም ሆኑ አባቶቻቸው፣ የይሁዳ ነገሥታትም ለማያውቋቸው አማልክት ሠውተዋል፤ ይህንም ስፍራ በንጹሓን ደም ሞልተውታል፤ 5እኔም ያላዘዝኋቸውን፣ ያልተናገርኋቸውን፣ ፈጽሞም ያላሰብሁትን፣ ወንዶች ልጆቻቸውን በእሳት ሊሠዉለት ለበኣል መስገጃ ኰረብታዎች ሠርተዋል። 6ስለዚህ ሰዎች ይህን ስፍራ የዕርድ ሸለቆ እንጂ ከእንግዲህ ቶፌት ወይም የሄኖም ልጅ ሸለቆ ብለው የማይጠሩበት ዘመን ይመጣል፤” ይላል እግዚአብሔር

7“ ‘በዚህ ስፍራ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ዕቅድ አፈርሳለሁ፤19፥7 አፈርሳለሁ የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አነባበብ ገንቦ ከሚለው ጋር ይመሳሰላል (1 እና 10 ይመ)። በጠላቶቻቸው ፊት ሕይወታቸውን በሚሹት እጅ በሰይፍ እንዲወድቁ አደርጋለሁ፤ ሬሳቸውንም ለሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት ምግብ አድርጌ እሰጣለሁ። 8ይህችን ከተማ ድምጥማጧን አጠፋለሁ፤ ለመሣለቂያም አደርጋታለሁ፤ በዚያም የሚያልፉ ሁሉ ከደረሰባት ጕዳት የተነሣ ወይ ጉድ! ይላሉ፣ ያሾፋሉም። 9የወንዶችና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንዲበሉ አደርጋለሁ፤ ሕይወታቸውን ለማጥፋት የሚሹ ጠላቶቻቸው ከብበው ሲያስጨንቋቸው፣ አንዱ የሌላውን ሥጋ ይበላል።’

10“ገንቦውንም ከአንተ ጋር በሄዱ ሰዎች ፊት ትሰብራለህ፤ 11እንዲህም ትላቸዋለህ፤ ‘የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የሸክላ ሠሪው ገንቦ እንደ ተሰበረና ሊጠገን እንደማይቻል፣ ይህን ሕዝብና ይህችን ከተማ እንዲሁ እሰብራለሁ፤ የቀብር ቦታ ከመታጣቱ የተነሣ ሙታናቸውን በቶፌት ይቀብራሉ። 12በዚህ ስፍራና በውስጡም በሚኖሩት ላይ ይህን አደርጋለሁ” ይላል እግዚአብሔር። ይህችን ከተማ እንደ ቶፌት አደርጋታለሁ። 13በጣራዎቻቸው ላይ ለሰማይ ሰራዊት ዕጣን የታጠነባቸውና ለባዕዳን አማልክት የመጠጥ ቍርባን የቀረበባቸው፣ የኢየሩሳሌም ቤቶችና የይሁዳ ነገሥታት ቤቶች እንደ ቶፌት የረከሱ ይሆናሉ።’ ”

14ኤርምያስም እግዚአብሔር ትንቢት እንዲናገር ልኮት ከነበረበት ከቶፌት ተመልሶ፣ በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባይ በመቆም፣ ለሕዝቡ ሁሉ እንዲህ አለ፤ 15“የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እነሆ ዐንገታቸውን በማደንደን ቃሌን ስላልሰሙ በዚህች ከተማና በዙሪያዋ ባሉ መንደሮች ሁሉ ላይ ላደርስ ያሰብሁትን ጥፋት ሁሉ አመጣለሁ።’ ”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

耶利米書 19:1-15

瓦瓶的比喻

1耶和華對我說: 2「你去向陶匠買一個瓦瓶,帶著百姓和祭司中的一些首領到哈珥西19·2 哈珥西」意思是「碎陶片」。城門旁的欣嫩子谷,在那裡宣告我的話。 3你要說,『猶大王和耶路撒冷的居民啊,你們要聽耶和華的話!以色列的上帝——萬軍之耶和華說,看啊,我要在這裡降下災禍,聽見這消息的人都必耳鳴。 4因為他們背棄了我,玷污了這地方。他們向自己、自己的祖先及猶大君王都不認識的神明燒香,使這地方流滿了無辜人的血。 5他們為巴力建邱壇,燒死自己的兒子作燔祭獻給巴力。我從未吩咐他們這樣做,連提都沒提過,連想都沒想過。 6因此,看啊,時候將到,這地方不再叫陀斐特欣嫩子谷,要叫殺戮谷。這是耶和華說的。 7我要在這地方挫敗猶大人和耶路撒冷居民的計謀,使他們喪身在敵人刀下,死在仇敵手中,屍體成為飛鳥和野獸的食物。 8我必摧毀這城,使它令人驚懼、嗤笑,它的滿目瘡痍必令路人驚懼、嗤笑。 9我必使他們在敵人的圍困之下陷入絕境,吃兒女和親友的肉。』

10耶利米啊,你要在同去的人面前打碎瓦瓶, 11然後告訴他們萬軍之耶和華說,『我要把這百姓和這城打得粉碎,正如人打碎瓦瓶一樣,再也不能修復。人們要在陀斐特埋死人,直到無處可埋。 12我必這樣懲罰這城和其中的居民,使這城像陀斐特一樣。這是耶和華說的。 13耶路撒冷的房屋和猶大君王的宮殿將被玷污,像陀斐特一樣,因為他們在房頂向天上的萬象燒香,向別的神明奠酒。』」

14耶利米奉耶和華之命到陀斐特說預言回來後,站在耶和華殿的院子中對百姓說: 15以色列的上帝——萬軍之耶和華說,『看啊,我要把我說過的災禍降在這城及其周圍的村莊,因為他們頑固不化,不肯聽我的話。』」