ኢዮብ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 5:1-27

1“እስቲ ተጣራ፤ የሚመልስልህ አለን?

ከቅዱሳንስ ወደ ማንኛው ዘወር ትላለህ?

2ሞኙን ሰው ብስጭት ይገድለዋል፤

ቂሉንም ቅናት ያጠፋዋል።

3ቂል ሰው ሥር ሰድዶ አየሁት፤

ግን ድንገት ቤቱ ተረገመ።

4ልጆቹ የኑሮ ዋስትና የራቃቸው፤

በፍርድ አደባባይ ጥቃት የደረሰባቸው፣ ታዳጊ የሌላቸው ናቸው።

5ከእሾኽ መካከል እንኳ አውጥቶ፣

ራብተኛ ሰብሉን ይበላበታል፤

ጥማተኛም ሀብቱን ይመኝበታል።

6ችግር ከምድር አይፈልቅም፤

መከራም ከመሬት አይበቅልም።

7ፍንጣሪው ከእሳቱ ላይ ሽቅብ እንደሚወረወር፣

ሰውም ለመከራ ይወለዳል።

8“እኔ ብሆን ኖሮ፣ ወደ እግዚአብሔር በቀረብሁ፣

ጕዳዬንም በፊቱ በገለጽሁለት ነበር።

9እርሱ፣ የማይመረመሩ ድንቅ ነገሮች፣

የማይቈጠሩም ታምራት ያደርጋል።

10ምድሪቱን በዝናብ ያረሰርሳል፤

ሜዳውንም ውሃ ያጠጣል።

11የተዋረዱትን በከፍታ ቦታ ያስቀምጣል፤

ያዘኑትንም ወደ አስተማማኝ ስፍራ ያወጣቸዋል።

12እጃቸው ያሰቡትን እንዳይፈጽም፣

የተንኰለኞችን ዕቅድ ያከሽፋል።

13ጠቢባንን በጥበባቸው ይይዛል፤

የተንኰለኞችንም ሤራ ያጠፋል።

14ቀኑ ጨለማ ይሆንባቸዋል፤

በቀትርም ጊዜ በሌሊት እንዳለ ሰው በዳበሳ ይሄዳሉ።

15ችግረኛውን ከአፋቸው ሰይፍ፣

ከኀይለኛውም እጅ ያድነዋል።

16ስለዚህ ድኻ ተስፋ አለው፤

ዐመፅም አፏን ትዘጋለች።

17“እነሆ፤ እግዚአብሔር የሚገሥጸው ሰው ምስጉን ነው፤

ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን5፥17 በዕብራይስጥ ሻዳይ ማለት ሲሆን፣ በዚህ ቍጥርና በኢዮብ መጽሐፍ ውስጥም እንዲሁ ነው። አምላክ ተግሣጽ አትናቅ።

18እርሱ ያቈስላል፤ ይፈውሳል፤

እርሱ ይሰብራል፤ በእጁም ይጠግናል፤

19እርሱ ከስድስት መቅሠፍት ይታደግሃል፤

በሰባተኛውም ጕዳት አያገኝህም።

20በራብ ጊዜ ከሞት፣

በጦርነትም ከሰይፍ ያድንሃል።

21ከምላስ ጅራፍ ትሰወራለህ፤

ጥፋት ሲመጣም አትፈራም።

22በጥፋትና በራብ ላይ ትሥቃለህ፤

የምድርንም አራዊት አትፈራም።

23ከሜዳ ድንጋዮች ጋር ትዋዋላለህና፤

የዱር አራዊትም ከአንተ ጋር ይስማማሉ።

24ድንኳንህ በሚያስተማምን ሁኔታ እንዳለ ታውቃለህ፤

በረትህን ትቃኛለህ፤ አንዳችም አይጐድልብህም።

25ዘሮችህ አያሌ እንደሚሆኑ፣

የምትወልዳቸውም እንደ ሣር እንደሚበዙ ታውቃለህ።

26የእህል ነዶ ጐምርቶ በወቅቱ እንደሚሰበሰብ፣

ዕድሜ ጠግበህ ወደ መቃብር ትሄዳለህ።

27“እነሆ፤ ይህን ሁሉ መርምረናል፤ እውነት ሆኖ አግኝተነዋል፤

ስለዚህ ልብ በል፤ ተቀበለውም።”

Thai New Contemporary Bible

โยบ 5:1-27

1“ร่ำร้องไปเถิด แต่ใครเล่าจะตอบท่าน?

ท่านจะหันหน้าไปหาเทพเจ้าองค์ไหน?

2คนโง่ตายเพราะโทสะจริต

ความอิจฉาริษยาเข่นฆ่าคนเขลา

3ข้าเองเคยเห็นคนโง่สร้างตัวเป็นหลักเป็นฐาน

แต่ทันใดนั้นบ้านของเขาก็ถูกสาปแช่ง

4ลูกหลานของเขาอยู่อย่างไร้ความปลอดภัย

และถูกคาดคั้นในศาลโดยไม่มีใครปกป้อง

5พืชผลของเขาถูกคนหิวโหยผลาญหมด

แม้แต่ที่ขึ้นในพงหนามก็หมดสิ้น

ทรัพย์สินของเขาถูกคนกระหายฉกฉวยไป

6เพราะความทุกข์ไม่ได้ผุดขึ้นมาจากดิน

ความเดือดร้อนไม่ได้งอกขึ้นจากพื้น

7แต่คนเราเกิดมาเพื่อความทุกข์ยาก

เหมือนประกายไฟย่อมพุ่งขึ้นฟ้า

8“หากเป็นข้า ข้าจะวิงวอนต่อพระเจ้า

ข้าจะนำเรื่องราวของข้าร้องทูลต่อพระองค์

9พระองค์ทรงกระทำการอัศจรรย์

ที่เกินการหยั่งรู้และเหลือคณานับ

10พระองค์ทรงให้ฝนตกลงมาบนโลก

ทรงส่งน้ำเข้ามาในท้องทุ่ง

11ทรงเชิดชูผู้ที่ต่ำต้อย

และทรงยกชูผู้คร่ำครวญขึ้นสู่สวัสดิภาพ

12พระองค์ทรงขัดขวางแผนการของคนเจ้าเล่ห์

เพื่อการงานของเขาจะไม่สำเร็จ

13พระองค์ทรงจับคนฉลาดด้วยเล่ห์เหลี่ยมของเขาเอง

และทรงล้มแผนการของคนชั่ว

14ความมืดมนมาเหนือเขาในยามกลางวัน

กลางวันแสกๆ เขาคลำสะเปะสะปะเหมือนอยู่ในยามกลางคืน

15พระเจ้าทรงช่วยผู้ยากไร้จากวาจาเชือดเฉือนของพวกเขา

ทรงกู้เขาจากอุ้งมือของผู้มีอิทธิพล

16ดังนั้นคนยากจนยังมีความหวัง

และความอยุติธรรมก็เป็นฝ่ายปิดปากเงียบ

17“ความสุขมีแก่ผู้ที่พระเจ้าทรงตักเตือน

ฉะนั้นอย่าดูหมิ่นการตีสั่งสอนขององค์ทรงฤทธิ์

18เพราะพระองค์ทรงทำให้เป็นแผล แต่ก็ทรงสมานรอยแผล

พระองค์ทรงทำให้บาดเจ็บ แต่ก็ทรงรักษาให้หาย

19พระองค์จะทรงกอบกู้ท่านจากอันตรายหกครั้ง

แม้จะมีครั้งที่เจ็ดก็ไม่อาจทำอันตรายท่านได้

20พระองค์จะทรงช่วยท่านให้พ้นจากความตายในยามกันดารอาหาร

และจากคมดาบในยามสงคราม

21ท่านจะได้รับการปกป้องจากคำนินทาว่าร้าย

และไม่จำเป็นต้องหวั่นกลัวเมื่อความพินาศมาถึง

22ท่านจะยิ้มเยาะให้แก่ความพินาศและการกันดารอาหาร

และไม่ต้องหวาดกลัวสัตว์ร้าย

23ท่านจะผูกมิตรกับก้อนหินในทุ่งนา

และหมู่สัตว์ป่าจะญาติดีกับท่าน

24ท่านจะมั่นใจว่าเต็นท์ของท่านมั่นคงปลอดภัย

ตรวจดูทรัพย์สินก็ไม่มีอะไรขาดหาย

25ท่านจะได้ทราบว่าลูกหลานของท่านจะมีมากมาย

และพงศ์พันธุ์ของท่านจะมีมากมายเหมือนหญ้าบนแผ่นดินโลก

26แม้มาถึงหลุมฝังศพ ท่านก็ยังแข็งแรง

เหมือนฟ่อนข้าวที่เก็บเกี่ยวตามฤดูกาล

27“เราได้ตรวจสอบสิ่งเหล่านี้ก็พบว่าเป็นความจริง

ฉะนั้นท่านเองโปรดรับฟังและนำไปปฏิบัติเถิด”