ኢዮብ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 4:1-21

ኤልፋዝ

1ቴማናዊው ኤልፋዝም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“አንድ ሰው ከአንተ ጋር ለመናገር ቢሞክር፣ ቅር ይልሃልን?

ዳሩ ግን ከመናገር ማን ሊቈጠብ ይችላል?

3እነሆ፤ አንተ ብዙዎችን ታስተምር እንደ ነበር ዐስብ፤

የደከሙትንም እጆች ታበረታ ነበር፤

4ቃልህ የተሰናከሉትን ያነሣ ነበር፤

የሚብረከረከውንም ጕልበት ታጸና ነበር።

5አሁን ግን መከራ አገኘህ፣ አንተም ተስፋ ቈረጥህ፤

ሸነቈጠህ፤ ደነገጥህም።

6እግዚአብሔርን መፍራት መታመኛህ፣

ቀና አካሄድህም ተስፋህ አይደለምን?

7“አሁንም አስተውል፤ ንጹሕ ሆኖ የጠፋ ማን ነው?

ቅኖችስ መች ተደምስሰው ያውቃሉ?

8እኔ እንዳየሁ ክፋትን የሚያርሱ፣

መከራንም የሚዘሩ ያንኑ ያጭዳሉ።

9በእግዚአብሔር እስትንፋስ ይጠፋሉ፤

በቍጣውም ወላፈን ይደመሰሳሉ።

10አንበሳ ያገሣል፤ ቍጡውም አንበሳ ይጮኻል፤

የደቦል አንበሳው ጥርስ ግን ተሰብሯል።

11ብርቱው አንበሳ ዐደን በማጣት ይሞታል፤

የአንበሳዪቱም ግልገሎች ይበተናሉ።

12“ቃል በምስጢር መጣልኝ፤

ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች።

13በሚያስጨንቅ የሌሊት ሕልም ውስጥ፣

ከባድ እንቅልፍም በሰዎች ላይ በወደቀ ጊዜ፣

14ፍርሀትና መንቀጥቀጥ ያዘኝ፤

ዐጥንቶቼም ሁሉ ተናወጡ።

15መንፈስ ሽው ብሎ በፊቴ ዐለፈ፤

የገላዬም ጠጕር ቆመ።

16እርሱም ቆመ፣

ምን እንደ ሆነ ግን መለየት አልቻልሁም፤

አንድ ቅርጽ በዐይኔ ፊት ነበረ፤

በእርጭታ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

17‘ሥጋ ለባሽ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጻድቅ ሊሆን ይችላልን?

ሰውስ ከፈጣሪው ይልቅ ንጹሕ ሊሆን ይችላልን?

18እግዚአብሔር በአገልጋዮቹ ላይ እምነት ካልጣለ፣

መላእክቱንም በስሕተታቸው ከወቀሠ፣

19ይልቁንስ በጭቃ ቤት የሚኖሩ፣

መሠረታቸው ከዐፈር የሆነ፣

ከብልም ይልቅ በቀላሉ የሚጨፈለቁ እንዴት ይሆኑ?

20በንጋትና በምሽት መካከል ይደቅቃሉ፤

ሳይታሰብም ለዘላለም ይጠፋሉ።

21ያለ ጥበብ ይሞቱ ዘንድ፣

የድንኳናቸው ገመድ አልተነቀለምን?’

Thai New Contemporary Bible

โยบ 4:1-21

เอลีฟัส

1แล้วเอลีฟัสชาวเทมานตอบว่า

2“ถ้าใครจะพูดอะไรกับท่านสักคำ ท่านพอจะทนฟังได้ไหม?

แต่ใครเล่าจะอดใจไว้ไม่พูดออกมา?

3คิดดูสิว่าท่านเคยแนะนำคนมากมาย

เคยช่วยให้คนที่อ่อนเปลี้ยเพลียแรงมีกำลังขึ้นมาแล้วอย่างไร

4คำพูดของท่านเคยค้ำจุนผู้ที่สะดุดล้ม

ท่านทำให้คนที่ล้มพับลงเข้มแข็งขึ้นมาได้

5แต่เดี๋ยวนี้เมื่อความทุกข์ร้อนมาถึงท่าน ท่านก็ท้อแท้

เมื่อความทุกข์ร้อนกระหน่ำใส่ ท่านก็หมดกำลังใจ

6ไม่ควรหรือที่คุณธรรมของท่านจะให้ความมั่นใจแก่ท่าน

และความประพฤติดีพร้อมของท่านจะให้ความหวังแก่ท่าน?

7“บัดนี้จงใคร่ครวญดูเถิด มีหรือที่คนบริสุทธิ์ต้องพินาศ?

มีหรือที่คนชอบธรรมต้องถูกทำลาย?

8ข้าสังเกตว่าคนที่ไถความชั่วและหว่านความเดือดร้อน

ก็จะเก็บเกี่ยวสิ่งนั้น

9พวกเขาพินาศโดยลมหายใจของพระเจ้า

ย่อยยับโดยพระพิโรธของพระองค์

10สิงโตอาจจะส่งเสียงขู่คำราม

แต่เขี้ยวเล็บของราชสีห์ก็ยังถูกหัก

11สิงโตย่อยยับเพราะหาเหยื่อไม่ได้

ลูกสิงห์ต้องกระจัดกระจายไป

12“มีถ้อยคำมาถึงข้าอย่างลี้ลับ

เป็นเสียงกระซิบที่หูของข้าได้ยิน

13ในฝันร้ายซึ่งเข้ามายามค่ำคืน

ขณะที่ผู้คนหลับสนิท

14ความหวาดหวั่นพรั่นพรึงจู่โจมข้า

ทำให้กระดูกทุกซี่ของข้าสั่นสะท้าน

15วิญญาณดวงหนึ่งวูบผ่านหน้าข้าไป

ข้าขนลุกซู่

16วิญญาณดวงนั้นหยุด

แต่ข้าบอกไม่ได้ว่ามันเป็นอะไร

มีร่างหนึ่งอยู่ตรงหน้าข้า

และข้าได้ยินเสียงเบาๆ เสียงหนึ่งกล่าวว่า

17‘มนุษย์จะชอบธรรมกว่าพระเจ้าได้หรือ?

คนเราจะบริสุทธิ์กว่าพระผู้สร้างของเขาได้หรือ?

18หากว่าพระเจ้ายังทรงไว้วางพระทัยผู้รับใช้ของพระองค์เองไม่ได้

หากว่าพระองค์ยังทรงกล่าวโทษความผิดพลาดของเหล่าทูตสวรรค์

19แล้วผู้ที่อาศัยในเรือนดินจะยิ่งกว่านั้นสักเท่าใด

ผู้ซึ่งมีรากฐานอยู่ในธุลีดิน

ซึ่งขยี้ให้ตายได้ง่ายดายยิ่งกว่าแมลงเม่า!

20จากรุ่งอรุณถึงสนธยา เขาถูกห้ำหั่นเป็นชิ้นๆ

พินาศไปนิรันดร์โดยไม่มีผู้ใดสังเกต

21เชือกขึงเต็นท์ของพวกเขาถูกดึงออก

จนเขาตายไปโดยปราศจากสติปัญญาไม่ใช่หรือ?’4:21 ผู้ตีความพระคัมภีร์บางคนใส่เครื่องหมายคำพูดปิดหลังข้อ 17