ኢዮብ 39 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 39:1-30

1“የበረሓ ፍየል የምትወልድበትን ጊዜ ታውቃለህን?

ዋሊያ ስታምጥስ ተከታትለህ አይተሃል?

2የእርግዝናቸው ወራት ምን ያህል እንደ ሆነ ትቈጥራለህን?

የሚወልዱበትንስ ጊዜ ታውቃለህን?

3ተንበርክከው ይወልዳሉ፤

ከምጣቸውም ጣር ይገላገላሉ።

4ግልገሎቻቸውም ይጠነክራሉ፤ በሜዳም ያድጋሉ፤

ተለይተው ይሄዳሉ፤ ወደ እነርሱም አይመለሱም።

5“ለሜዳ አህያ ነጻነት የሰጠው ማን ነው?

እስራቱንስ ማን ፈታለት?

6ምድረ በዳውን መኖሪያው፣

የጨውንም ምድር ማደሪያው አድርጌ ሰጠሁት።

7በከተማ ውካታ ይሥቃል፤

የነጂውንም ጩኸት አይሰማም።

8በየተራራው ይሰማራል፤

ሐመልማሉንም ሁሉ ለማግኘት ይወጣል።

9“ጐሽ ያገለግልህ ዘንድ ይታዘዛልን?

በበረትህስ አጠገብ ያድራልን?

10እንዲያርስልህ ልትጠምደው ትችላለህ?

ወይስ እየተከተለህ ዕርሻህን ይጐለጕልልሃልን?

11ጕልበቱ ብርቱ ስለሆነ ትተማመንበታለህ?

ከባዱን ሥራህንስ ለእርሱ ትተዋለህ?

12እህልህን እንዲሰበስብልህ፣

በዐውድማህም ላይ እንዲያከማችልህ ታምነዋለህን?

13“ሰጎን ክንፎቿን በደስታ ታራግባለች፤

ነገር ግን እንደ ሽመላ ላባዎች ሊሆኑ አይችሉም።

14ዕንቍላሏን መሬት ላይ ትጥላለች፤

እንዲሞቅም በአሸዋ ውስጥ ትተወዋለች።

15እግር እንደሚሰብረው፤

የዱር አውሬም እንደሚረግጠው አታስብም።

16የእርሷ እንዳልሆኑ ሁሉ በልጆቿ ትጨክናለች፤

ድካሟም በከንቱ ቢቀር ደንታ የላትም፤

17እግዚአብሔር ጥበብ ነሥቷታልና፤

ማስተዋልንም አልሰጣትም።

18ለመሸምጠጥም ክንፎቿን ስትዘረጋ፣

በፈረስና በጋላቢው ትሥቃለች።

19“ለፈረስ ጕልበትን ትሰጠዋለህን?

ዐንገቱንስ ጋማ ታለብሰዋለህን?

20እንደ አንበጣ የምታስዘልለው አንተ ነህን?

የማንኰራፋቱም ገናናነት አስፈሪ ነው።

21በጕልበቱ እየተመካ በብርቱ ይጐደፍራል፤

ጦርነት ሊገጥም ይወጣል።

22ያለ አንዳች ሥጋት፣ በፍርሀት ላይ ይሥቃል፤

ሰይፍ ቢመዘዝበትም ወደ ኋላ አይልም።

23ከሚብረቀረቀው ጦርና ዐንካሴ ጋር፣

የፍላጻው ኰረጆ ጐኑ ላይ ይንኳኳል።

24በወኔ መሬቱን እየጐደፈረ ወደ ፊት ይሸመጥጣል፤

የመለከት ድምፅ ሲሰማ ያቅበጠብጠዋል።

25መለከቱ ሲያንባርቅ፣ ‘ዕሠይ’ ይላል፤

የአዛዦችን ጩኸትና የሰራዊቱን ውካታ፣

ጦርነትንም ከሩቅ ያሸትታል።

26“ጭልፊት የሚበርረው፣

ክንፎቹንም ወደ ደቡብ የሚዘረጋው፣ በአንተ ጥበብ ነውን?

27ንስር ወደ ላይ የሚመጥቀው፣

ጎጆውንም በከፍታ ላይ የሚሠራው፣

በአንተ ትእዛዝ ነውን?

28በገደል ላይ ይኖራል፤ በዚያም ያድራል፤

ምሽጉም የቋጥኝ ጫፍ ነው።

29እዚያ ሆኖ የሚነጥቀውን ይቃኛል፤

ዐይኑም ከሩቅ አጥርቶ ያያል።

30ጫጩቶቹ ደም ይጠጣሉ፤

እርሱም በድን ካለበት አይታጣም።”

Ketab El Hayat

أيوب 39:1-30

1هَلْ تُدْرِكُ مَتَى تَلِدُ أَوْعَالُ الصُّخُورِ أَمْ تَرْقُبُ مَخَاضَ الأَيَائِلِ؟ 2هَلْ تَحْسُبُ أَشْهُرَ حَمْلِهِنَّ، وَتَعْلَمُ مِيعَادَ وَضْعِهِنَّ، 3حِينَ يَجْثُمْنَ لِيَضَعْنَ صِغَارَهُنَّ، وَيتَخَلَّصْنَ مِنْ آلامِ مَخَاضِهِنَّ؟ 4تَكْبُرُ صِغَارُهُنَّ، وَتَنْمُو فِي الْقَفْرِ، ثُمَّ تَشْرُدُ وَلا تَعُودُ.

5مَنْ أَطْلَقَ سَرَاحَ حِمَارِ الْوَحْشِ وَفَكَّ رُبُطَ حِمَارِ الْوَحْشِ؟ 6لِمَنْ أَعْطَيْتُ الصَّحْرَاءَ مَسْكَناً وَالأَرْضَ الْمِلْحِيَّةَ مَنْزِلاً؟ 7فَيَسْخَرَ مِنْ جَلَبَةِ الْمُدُنِ وَلا يَسْمَعَ نِدَاءَ السَّائِقِ؟ 8يَرْتَادُ الْجِبَالَ مَرْعىً لَهُ، وَيَلْتَمِسُ كُلَّ مَا هُوَ أَخْضَرُ، 9أَيَرْضَى الثَّوْرُ الْوَحْشِيُّ أَنْ يَخْدُمَكَ؟ أَيَبِيتُ عِنْدَ مِعْلِفِكَ؟ 10أَتَرْبِطُهُ بِالنِّيرِ لِيَجُرَّ لَكَ الْمِحْرَاثَ، أَمْ يُمَهِّدُ الْوَادِي خَلْفَكَ؟ 11أَتَتَّكِلُ عَلَيْهِ لِقُوَّتِهِ الْعَظِيمَةِ، وَتُكَلِّفُهُ الْقِيَامَ بِأَعْمَالِكَ؟ 12أَتَثِقُ بِعَوْدَتِهِ حَامِلاً إِلَيْكَ حِنْطَتَكَ لِيُكَوِّمَهَا فِي بَيْدَرِكَ؟

13يُرَفْرِفُ جَنَاحَا النَّعَامَةِ بِغِبْطَةٍ، وَلَكِنْ أَهُمَا جَنَاحَانِ مَكْسُوَّانِ بِرِيشِ الْمَحَبَّةِ؟ 14فَهِيَ تَتْرُكُ بَيْضَهَا عَلَى الأَرْضِ لِيَدْفَأَ بِالتُّرَابِ، 15وَتَنْسَى أَنَّ الْقَدَمَ قَدْ تَطَأُ عَلَيْهِ، وَأَنَّ بَعْضَ الْحَيَوَانَاتِ الْكَاسِرَةِ قَدْ تُحَطِّمُهُ. 16إِنَّهَا تُعَامِلُ صِغَارَهَا بِقَسْوَةٍ كَأَنَّهَا لَيْسَتْ لَهَا، غَيْرَ آسِفَةٍ عَلَى ضَيَاعِ تَعَبِهَا، 17لأَنَّ اللهَ قَدْ أَنْسَاهَا الْحِكْمَةَ، وَلَمْ يَمْنَحْهَا نَصِيباً مِنَ الْفَهْمِ. 18وَلَكِنْ مَا إِنْ تَبْسُطُ جَنَاحَيْهَا، لِتَجْرِيَ حَتَّى تَهْزَأَ بِالْفَرَسِ وَرَاكِبِهِ!

19أَأَنْتَ وَهَبْتَ الْفَرَسَ قُوَّتَهُ، وَكَسَوْتَ عُنُقَهُ عُرْفاً؟ 20أَأَنْتَ تَجْعَلُهُ يَثِبُ كَجَرَادَةٍ؟ إنَّ نَخِيرَهُ الْهَائِلَ لَمُخِيفٌ. 21يَشُقُّ الْوَادِي بِحَوَافِرِهِ، وَيَمْرَحُ فِي جَمِّ نَشَاطِهِ، وَيَقْتَحِمُ الْمَعَارِكَ. 22يَسْخَرُ مِنَ الْخَوْفِ وَلا يَرْتَاعُ، وَلا يَتَرَاجَعُ أَمَامَ السَّيْفِ. 23تَصِلُّ عَلَيْهِ جُعْبَةُ السِّهَامِ، وَأَيْضاً بَرِيقُ الرِّمَاحِ وَالْحِرَابِ. 24فِي جَرْيِهِ يَنْهَبُ الأَرْضَ بِعُنْفُوَانٍ وَغَضَبٍ وَلا يَسْتَقِرُّ فِي مَكَانِهِ عِنْدَ نَفْخِ بُوقِ الْحَرْبِ. 25عِنْدَمَا يُدَوِّي صَوْتُ الْبُوقِ يَقُولُ: هَهْ هَهْ! وَيَسْتَرْوِحُ الْمَعْرَكَةَ عَنْ بُعْدٍ، وَيَسْمَعُ زَئِيرَ الْقَادَةِ وَهُتَافَهُمْ.

26أَبِحِكْمَتِكَ يُحَلِّقُ الصَّقْرُ وَيَفْرِدُ جَنَاحَيْهِ نَحْوَ الْجَنُوبِ؟ 27أَبِأَمْرِكَ يُحَلِّقُ النَّسْرُ وَيَجْعَلُ وَكْرَهُ فِي الْعَلاءِ؟ 28يُعَشِّشُ بَيْنَ الصُّخُورِ، وَيَبِيتُ فِيهَا وَعَلَى جُرْفٍ صَخْرِيٍّ يَكُونُ مَعْقَلُهُ. 29مِنْ هُنَاكَ يَتَرَصَّدُ قُوتَهُ، وَتَرْقُبُ عَيْنَاهُ فَرِيسَتَهُ مِنْ بَعِيدٍ. 30وَتَأْكُلُ فِرَاخُهُ أَيْضاً الدِّمَاءَ، وَحَيْثُ تَكُونُ الْجُثَثُ تَتَجَمَّعُ النُّسُورُ».