ኢዮብ 36 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 36:1-33

1ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2“በእግዚአብሔር ፈንታ ሆኜ የምለው አለኝ፤

ጥቂት ታገሠኝና እነግርሃለሁ።

3ዕውቀቴን ከሩቅ አመጣለሁ፤

ፈጣሪዬ ጻድቅ እንደ ሆነ እገልጻለሁ።

4ቃሌ ሐሰት እንዳልሆነ አረጋግጣለሁ፤

በዕውቀቱ ፍጹም የሆነ ሰው ከአንተ ጋር ነው።

5“እግዚአብሔር ኀያል ነው፤ ግን ማንንም አይንቅም፤

ኀያል፣ በዐላማውም ጽኑ ነው።

6ክፉዎችን በሕይወት አያኖርም፤

ለተቸገሩት ግን በቅን ይፈርዳል።

7ዐይኖቹን ከጻድቃን ላይ አያነሣም፤

ከነገሥታት ጋር በዙፋን ላይ ያስቀምጣቸዋል፤

ለዘላለምም ከፍ ከፍ ያደርጋቸዋል።

8ነገር ግን ሰዎች በሰንሰለት ቢታሰሩ፣

በመከራም ገመድ ቢጠፈሩ፣

9በእብሪት የፈጸሙትን በደል፣

ተግባራቸውን ይነግራቸዋል።

10ተግሣጽን እንዲሰሙ ያደርጋቸዋል፤

ከክፋታቸውም እንዲመለሱ ያዝዛቸዋል።

11ታዝዘው ቢያገለግሉት፣

ቀሪ ዘመናቸውን በተድላ፣

ዕድሜያቸውንም በርካታ ይፈጽማሉ።

12ባይሰሙ ግን፣

በሰይፍ36፥12 ወይም፣ ወንዙን ያቋርጣሉ ይጠፋሉ፤

ያለ ዕውቀትም ይሞታሉ።

13“ልባቸው ከእግዚአብሔር የራቀ፣ ቍጣን ያስተናግዳሉ፤

በሰንሰለት ባሰራቸውም ጊዜ እንኳ ወደ እርሱ አይጮኹም።

14በቤተ ጣዖት ውስጥ ዝሙት በሚፈጽሙት መካከል፣

ገና በወጣትነታቸው ይቀጫሉ።

15ነገር ግን የሚሠቃዩትን ከሥቃያቸው ያድናቸዋል፤

በመከራቸውም ውስጥ ይናገራቸዋል።

16“አንተንም ከመከራ መንጋጋ፣

ጭንቀት ወደሌለበት ወደ ሰፊ ስፍራ፣

ምርጥ ምግብ ወደ ሞላበት ማእድ ያወጣሃል።

17አሁን ግን ለክፉዎች የሚገባው ፍርድ በላይህ ተጭኗል፤

ፍርድና ብይን ይዘውሃል።

18ባለጠግነት እንዳያታልልህ፣

የእጅ መንሻ ብዛትም እንዳያስትህ ተጠንቀቅ።

19ባለጠግነትህም ሆነ ብርቱ ጥረትህ ሁሉ፣

ችግር ውስጥ እንዳትገባ ሊረዳህ ይችላልን?

20ሰዎች ከቤታቸው36፥20 በዕብራይስጥ ከ18-20 ያለው ክፍል ትርጕሙ በትክክል አይታወቅም። የሚወሰዱበትን፣

ሌሊት አትመኝ።

21ከመከራ ይልቅ መርጠኸዋልና፣

ወደ ክፋት እንዳትመለስ ተጠንቀቅ።

22“እነሆ፤ እግዚአብሔር በኀይሉ ከፍ ከፍ ብሏል፤

እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው?

23እርሱን መንገድ የሚመራው፣

ወይም ‘ይህን አጥፍተሃል’ የሚለው ማን ነው?

24ሰዎች በመዝሙር ያወደሱትን፣

የእርሱን ሥራ ማወደስ አትዘንጋ።

25ሰው ሁሉ አይቶታል፤

ሰዎችም በትኵረት ተመልክተውታል።

26እነሆ፤ እግዚአብሔር ከአእምሯችን በላይ ታላቅ ነው!

የዘመኑም ቍጥር ከመታወቅ ያልፋል።

27“የውሃን ነጠብጣብ ወደ ላይ ያተንናል፤

መልሶም በዝናብ መልክ በጅረቶች ላይ ያወርዳል፤

28ደመናት ጠል ያንጠባጥባሉ፤

ዶፍም በሰው ላይ ይወርዳል።

29ደመናትን እንዴት እንደሚዘረጋ፣

ከድንኳኑም እንዴት እንደሚያንጐደጕድ ሊረዳ የሚችል ማን ነው?

30መብረቁን በዙሪያው እንዴት እንደሚበትን ተመልከት፤

የባሕሩንም ወለል ይሸፍናል።

31እርሱ ሕዝብን የሚያስተዳድረው፣36፥31 ወይም፣ የሚያስተዳድረው ምግብንም አትረፍርፎ የሚሰጣቸው

በዚህ መንገድ ነው።

32እጆቹን በመብረቅ ይሞላቸዋል፤

ዒላማውንም እንዲመታ ያዝዘዋል።

33ነጐድጓዱ ውሽንፍር እንደሚከተለው ያመለክታል፤

ከብቶችም እንኳ መምጣቱን ይጠቍማሉ።

Thai New Contemporary Bible

โยบ 36:1-33

1เอลีฮูกล่าวต่อไปว่า

2“ขอให้รับฟังอีกสักหน่อย และข้าพเจ้าจะแสดงให้ท่านเห็นว่า

มีอย่างอื่นอีกมากมายที่ต้องพูดแทนพระเจ้า

3ข้าพเจ้าได้ความรู้มาจากแดนไกล

ข้าพเจ้าจะชี้แจงให้ฟังว่าความยุติธรรมนั้นเป็นของพระผู้สร้างของข้าพเจ้า

4มั่นใจเถิดว่าคำพูดของข้าพเจ้าเป็นความจริง

ผู้รอบรู้แท้จริงอยู่กับท่านแล้ว

5“พระเจ้าทรงฤทธิ์ แต่ก็ไม่ได้ทรงเหยียดหยามผู้ใด

พระองค์ทรงฤทธิ์และแน่วแน่ในพระประสงค์

6พระองค์ไม่ทรงปล่อยให้คนชั่วมีชีวิตอยู่

แต่ประทานสิทธิ์ให้แก่ผู้ที่ทุกข์ทรมาน

7พระเนตรของพระองค์ไม่หันไปจากคนชอบธรรม

แต่ทรงให้เขานั่งบนบัลลังก์ร่วมกับเหล่ากษัตริย์

และเชิดชูเขาตลอดไป

8แต่หากมนุษย์ถูกพันธนาการ

ถูกมัดด้วยบ่วงทุกข์ทรมาน

9พระองค์ก็ตรัสบอกพวกเขาว่าพวกเขาได้ทำอะไรลงไป

ว่าพวกเขาทำบาปด้วยความผยองอย่างไรบ้าง

10พระองค์ทรงทำให้พวกเขารับฟังการเตือนสอน

และทรงบัญชาให้พวกเขากลับใจจากความชั่วร้าย

11หากพวกเขาเชื่อฟังและปรนนิบัติพระเจ้า

พวกเขาจะใช้ชีวิตที่เหลือด้วยความเจริญรุ่งเรือง

และปีเดือนของพวกเขาจะเป็นที่อิ่มเอมใจ

12แต่หากพวกเขาไม่ยอมฟัง

พวกเขาจะพินาศด้วยคมดาบ36:12 หรือจะข้ามแม่น้ำนั้น

และตายโดยปราศจากความรู้

13“คนอธรรมเก็บความขุ่นเคืองไว้ในใจ

แม้เมื่อพระองค์ทรงล่ามพวกเขาไว้ พวกเขาก็ไม่ร้องขอความช่วยเหลือ

14พวกเขาเสียชีวิตตั้งแต่วัยฉกรรจ์

ตายในหมู่ผู้ชายขายตัวตามสถานบูชา

15แต่พระเจ้าทรงกอบกู้ผู้ที่ตกอยู่ในห้วงทุกข์

พระองค์ตรัสกับเขายามทุกข์ลำเค็ญ

16“พระองค์ทรงเกลี้ยกล่อมท่านให้ออกจากความทุกข์ยาก

มายังสถานที่กว้างขวางไร้ข้อจำกัด

มาสู่โต๊ะอาหารอันน่าอภิรมย์ของท่านซึ่งเพียบพร้อมด้วยอาหารอันโอชะ

17แต่บัดนี้ท่านมัวแต่หมกมุ่นอยู่กับการพิพากษาโทษอันควรแก่คนชั่วร้าย

พระอาญาและความยุติธรรมจู่โจมจับท่านแล้ว

18ระวังเถิด อย่าให้ผู้ใดล่อลวงท่านด้วยทรัพย์สมบัติ

อย่าให้สินบนก้อนใหญ่ทำให้ท่านเขวไป

19ทรัพย์สินหรือความทุ่มเทเพียรพยายามใดๆ ของท่านนั้น

จะช่วยค้ำชูท่านไม่ให้ตกอยู่ในความทุกข์ได้หรือ?

20อย่าปรารถนายามค่ำคืน

เพื่อจะพรากผู้คนจากเหย้าเรือน36:20 ในภาษาฮีบรูข้อ 18-20 มีความหมายไม่ชัดเจน

21จงระมัดระวังที่จะไม่หันไปหาความชั่วร้าย

ซึ่งดูเหมือนท่านเต็มใจจะเลือกเอามากกว่าความทุกข์ทรมาน

22“ฤทธิ์อำนาจของพระเจ้าเป็นที่ยกย่องเทิดทูน

ผู้ใดเล่าเป็นครูเสมอเหมือนพระองค์?

23ใครจะบงการวิถีทางของพระองค์ได้

หรือกล่าวกับพระองค์ว่า ‘พระองค์ทรงกระทำผิด’?

24อย่าลืมยกย่องพระราชกิจของพระเจ้า

ซึ่งมนุษย์ร้องเพลงสดุดี

25มวลมนุษยชาติได้เห็นพระราชกิจเหล่านั้น

เหล่ามนุษย์เพ่งดูแต่ไกล

26พระเจ้าทรงยิ่งใหญ่นัก! เกินกว่าที่เราจะเข้าใจ

พระองค์ดำรงอยู่มานานเท่าใด เกินกว่าเราจะรู้

27“พระองค์ทรงรวบรวมหยดน้ำขึ้นไป

แล้วกลั่นเป็นฝนรดธารน้ำ36:27 หรือกลั่นละอองน้ำมาเป็นฝน

28หมู่เมฆเทความชุ่มชื้นลงมาให้

และโปรยปรายสายฝนแก่มนุษยชาติอย่างเหลือเฟือ

29ผู้ใดเล่าสามารถเข้าใจได้ถ่องแท้ถึงการกระจายตัวของหมู่เมฆ

และการคำรนคำรามของฟ้าผ่า?

30จงดูวิธีการที่ทรงกระจายฟ้าแลบรอบพระองค์

อาบที่ลึกแห่งท้องทะเล

31โดยวิธีนี้พระองค์ทรงปกครอง36:31 หรือเลี้ยงดูมวลประชาชาติ

และประทานอาหารอย่างอุดมสมบูรณ์

32พระองค์ทรงกุมสายฟ้าแลบไว้ในพระหัตถ์

และบงการให้มันผ่าตรงจุดที่หมายไว้

33ฟ้าคำรนของพระองค์ประกาศว่าพายุกำลังจะมา

แม้แต่ฝูงสัตว์ก็บอกให้รู้ว่าพายุใกล้เข้ามาแล้ว36:33 หรือประกาศการเสด็จมาของพระองค์ / องค์ผู้ทรงต่อต้านความชั่วร้ายอย่างแข็งขัน