ኢዮብ 24 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 24:1-25

1“ሁሉን የሚችል አምላክ ለምን የፍርድ ቀን አይወስንም?

እርሱን የሚያውቁትስ ለምን ያን ቀን እንዲያው ይጠባበቃሉ?

2ሰዎች ድንበር ይገፋሉ፤

የሰረቁትን መንጋ ያሰማራሉ።

3የድኻ ዐደጉን አህያ ቀምተው ይሄዳሉ፤

የመበለቲቱንም በሬ በመያዣነት ይወስዳሉ።

4ችግረኛውን ከመንገድ ያስወግዳሉ፤

የምድሪቱም ድኾች ይሸሸጋሉ።

5በምድረ በዳ እንዳሉ የሜዳ አህዮች፣

ድኾች ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ፤

ከበረሓው ምድር ለልጆቻቸው ምግብ ይሻሉ።

6ከሜዳ መኖ ይሰበስባሉ፤

ከክፉዎች የወይን ቦታም ይቃርማሉ።

7ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ያድራሉ፤

በብርድም ጊዜ የሚለብሱት የላቸውም።

8ከተራራ በሚወርድ ዝናብ በስብሰዋል፤

መጠለያ ዐጥተው ቋጥኝ ዐቅፈዋል።

9አባት የሌለው ልጅ ከዕቅፍ ተነጥቋል፤

የድኻውም ልጅ በዕዳ ተይዟል።

10ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ይሄዳሉ፤

ነዶ ይሸከማሉ፤ ግን ይራባሉ።

11በየተረተሩ24፥11 ወይም ከወፍጮዎች መካከል የወይራ ዘይት ማለት ነው፤ ሆኖም የዚህ ቃል የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። የወይራ ዘይት ያወጣሉ፤

ወይን እየጠመቁ፣ ራሳቸው ግን ይጠማሉ፤

12የሟቾች ጣር ጩኸት ከከተማዋ ይሰማል፤

የቈሰሉት ሰዎች ነፍስ ለርዳታ ይጮኻል፤

እግዚአብሔር ግን ተጠያቂዎቹን ዝም ብሏል።

13“በብርሃን ላይ የሚያምፁ፣

ጐዳናውን የማያውቁ፣

በመንገዱም የማይጸኑ አሉ።

14ቀኑ ሲመሽ፣ ነፍሰ ገዳይ ይነሣል፤

ድኾችንና ችግረኞችን ይገድላል፤

በሌሊትም እንደ ሌባ ያደባል፤

15አመንዝራ በዐይኑ ድንግዝግዝታን ይጠባበቃል፤

‘ማንም አያየኝም’ ብሎ ያስባል፤

ፊቱንም ይሸፍናል።

16በጨለማ፣ ቤት ሰርስረው ይገባሉ፤

በቀን ግን ይሸሸጋሉ፤

ብርሃንንም አይፈልጉም።

17ድቅድቅ ጨለማ ለሁላቸው እንደ ንጋት24፥17 ወይም ለእነርሱ ንጋት እንደ ሞት ጥላ ነው ነው፤

አሸባሪውን ጨለማ24፥17 ወይም ከሞት ጥላ ማለት ነው። ይወዳጃሉ።

18“ይሁን እንጂ፣ በውሃ ላይ የሚኵረፈረፍ ዐረፋ ናቸው፤

የወይን ቦታው ሰው የማይደርስበት፣

ርስታቸው ርጉም ነው።

19ድርቅና ሙቀት የቀለጠውን በረዶ ከቦታው እንደሚያስወግድ፣

ሲኦልም24፥19 አንዳንድ ቅጆች፣ መቃብር ይሉታል ኀጢአተኞችን ትነጥቃለች።

20የተሸከመቻቸው ማሕፀን ትረሳቸዋለች፤

ትል ይቦጠቡጣቸዋል፤

ክፉዎች እንደ ዛፍ ይሰበራሉ፤

የሚያስታውሳቸውም የለም።

21የማትወልደውን መካኒቱን ይቦጠቡጣሉ፤

ለመበለቲቱም አይራሩም።

22ነገር ግን እግዚአብሔር ብርቱዎችን በኀይሉ ጐትቶ ይጥላል፤

ቢደላደሉም የሕይወት ዋስትና የላቸውም።

23ያለ ሥጋት እንዲኖሩ ትቷቸው ይሆናል፤

ዐይኖቹ ግን በመንገዳቸው ላይ ናቸው።

24ለጥቂት ጊዜ ከፍ ከፍ ይላሉ፤ ሆኖም ይጠፋሉ፤

ዝቅ ዝቅ ብለው፤ እንደ ሌሎቹ ይከማቻሉ።

እንደ እህል ራስም ይታጨዳሉ።

25“ይህ እንዲህ ካልሆነማ፣ የሚያስተባብለኝ ማን ነው?

ቃሌን ከንቱ የሚያደርገውስ ማን ነው?”

Thai New Contemporary Bible

โยบ 24:1-25

1“ทำไมหนอองค์ทรงฤทธิ์จึงไม่ทรงกำหนดเวลาไว้เพื่อการพิพากษา?

ทำไมบรรดาผู้ที่รู้จักพระองค์ต้องชะเง้อหาวันเวลาเช่นนั้นโดยเปล่าประโยชน์?

2มีคนโยกย้ายหลักเขต

พวกเขาขโมยฝูงสัตว์มาเลี้ยง

3พวกเขาริบเอาลาของลูกกำพร้าพ่อ

และยึดวัวของแม่ม่ายเป็นของค้ำประกัน

4พวกเขาผลักไสคนขัดสนออกไปให้พ้นทาง

และบีบบังคับคนยากไร้ให้ต้องหลบๆ ซ่อนๆ

5ดั่งลาป่าในถิ่นกันดาร

คนยากไร้ต้องตรากตรำ

กระเสือกกระสนหาอาหารจากถิ่นกันดารเพื่อเลี้ยงลูก

6เขาเก็บหญ้าแห้งตามท้องทุ่ง

และเก็บของเหลือในสวนองุ่นของคนชั่ว

7ยามค่ำคืนต้องนอนหนาวเหน็บไม่มีผ้าจะพันกาย

ไม่มีผ้าห่มกันหนาว

8กายของเขาเปียกโชกเพราะสายฝนแห่งภูเขา

และเขาเกาะหินแน่นเพราะไม่มีที่กำบัง

9ลูกกำพร้าพ่อถูกคร่าจากอกแม่

ทารกของคนยากไร้ถูกจับไปเพราะเป็นหนี้

10พวกเขาจึงต้องระหกระเหินไปด้วยกายเปลือยเปล่า

ต้องแบกฟ่อนข้าวทั้งๆ ที่หิวโซ

11เขาคั้นน้ำมันมะกอกในดงมะกอก24:11 หรือคั้นน้ำมันมะกอกระหว่างหินโม่ ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจน

และย่ำน้ำองุ่นทั้งๆ ที่กำลังทุกข์ทรมานด้วยความกระหาย

12เสียงครวญครางของคนใกล้ตายดังมาจากตัวเมือง

วิญญาณของผู้บาดเจ็บร้องวิงวอนขอความช่วยเหลือ

แต่พระเจ้าไม่เห็นเอาผิดกับใคร

13“มีผู้กบฏต่อความสว่าง

ผู้ไม่รู้จัก

และไม่ยอมดำเนินในทางของความสว่างนั้น

14เมื่อสิ้นแสงตะวันแล้ว ฆาตกรก็ลุกขึ้น

สังหารคนยากไร้และคนขัดสน

ยามค่ำคืนเขาลอบออกไปเหมือนขโมย

15ตาของคนล่วงประเวณีจ้องรอคอยเวลาพลบค่ำ

เขาคิดว่า ‘ไม่มีใครเห็นเรา’

และคลุมหน้าเพื่อพรางตาคน

16ในความมืดมีคนแอบย่องเข้าไปในบ้าน

แต่ตอนกลางวันเขาก็เก็บตัวอยู่

ไม่อยากยุ่งเกี่ยวกับความสว่าง

17สำหรับพวกเขาทุกคน ความมืดสนิทเป็นยามเช้า24:17 หรือสำหรับพวกเขาทุกคน ยามเช้าของเขาก็เหมือนเงาแห่งความตาย

เขาเป็นมิตรกับความมืดมนอันน่าสยดสยอง24:17 หรือเขาเป็นมิตรกับเงาแห่งความตาย

18“ถึงกระนั้นเขาก็เป็นฟองบนผิวน้ำ

ที่ดินส่วนของเขาถูกสาปแช่ง

จึงไม่มีใครไปที่สวนองุ่นของเขา

19ความร้อนระอุแห้งแล้งดูดซับหิมะที่ละลายไปฉันใด

แดนมรณาก็พรากผู้ที่ทำบาปไปฉันนั้น

20ครรภ์มารดาก็ลืมเขา

ตัวหนอนรุมกินเขา

ไม่มีใครจดจำคนชั่วร้ายอีกต่อไป

แต่พวกเขาถูกโค่นลงเหมือนต้นไม้

21เพราะพวกเขาเอารัดเอาเปรียบหญิงที่เป็นหมันและหญิงที่ไม่มีลูกๆ ดูแล

เขาไม่ปรานีหญิงม่าย

22แต่พระเจ้าทรงลากผู้ยิ่งใหญ่ไปด้วยฤทธิ์อำนาจของพระองค์

แม้พวกเขาเป็นปึกแผ่น แต่ก็ไม่มีความมั่นคงในชีวิต

23พระองค์อาจจะปล่อยให้เขาพักอยู่ด้วยความรู้สึกมั่นคงปลอดภัย

แต่ทรงจับตาดูวิถีทางของเขา

24เขาได้รับการยกย่องเทิดทูนอยู่ชั่วครู่หนึ่ง แล้วก็ผ่านพ้นไป

พวกเขาต้องตกต่ำลงและถูกรวบไปเหมือนคนอื่นๆ

เขาถูกตัดออกเหมือนยอดรวงข้าว

25“ถ้าไม่ได้เป็นอย่างนี้ ใครจะพิสูจน์ได้ว่าข้าพูดผิด

และทำให้เห็นว่าสิ่งที่ข้ากล่าวมานี้ไม่เป็นความจริง”