ኢያሱ 6 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 6:1-27

1በዚህ ጊዜ እስራኤላውያንን ከመፍራት የተነሣ፣ ኢያሪኮ ፈጽማ ተዘግታ ነበር፤ ወደ ውጭ የሚወጣም ሆነ ወደ ውስጥ የሚገባ አልነበረም።

2እግዚአብሔርም ኢያሱን እንዲህ አለው፤ “እነሆ፤ ኢያሪኮን ከንጉሥዋና ከተዋጊዎቿ ጋር አሳልፌ በእጅህ ሰጥቻለሁ። 3ከተማዪቱን ከተዋጊዎቻችሁ ጋር አንድ ጊዜ ዙሩ፤ ይህንም ስድስት ቀን አድርጉ። 4ሰባት ካህናት፣ ሰባት ቀንደ መለከት ተሸክመው በታቦቱ ፊት ይውጡ፤ በሰባተኛውም ቀን ካህናቱ መለከት እየነፉ ከተማዪቱን ሰባት ጊዜ ይዙሩ። 5የማያቋርጥ የመለከት ድምፅ ሲነፋ በምትሰሙበት ጊዜ፣ ሕዝቡ ሁሉ ከፍ ያለ ጩኸት ያሰማ፤ ከዚያም የከተማዪቱ ቅጥር ይፈርሳል፤ ሕዝቡም ወደ ላይ ይወጣል፤ እያንዳንዱም ሰው በቀጥታ ይገባል።”

6ስለዚህ የነዌ ልጅ ኢያሱ ካህናቱን ጠርቶ፣ “የቃል ኪዳኑን ታቦት ተሸከሙ፤ ሰባት ካህናትም ሰባት ቀንደ መለከት ይዘው በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ይሂዱ” አላቸው። 7ሕዝቡንም፣ “ወደ ፊት ሂዱ፤ ከተማዋን ዙሩ፤ የታጠቁ ተዋጊዎችም በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ቀድመው ይሂዱ፤ ከተማዪቱንም ዙሩ” ሲል አዘዛቸው።

8ኢያሱም ለሕዝቡ ከተናገረ በኋላ፣ ሰባቱ ካህናት በእግዚአብሔር ፊት ሰባት ቀንደ መለከት ይዘው መለከታቸውን እየነፉ ወደ ፊት ቀደሙ፤ የእግዚአብሔር የቃል ኪዳን ታቦትም ተከተላቸው። 9የታጠቁ ተዋጊዎችም መለከት ከሚነፉት ካህናት ፊት ቀድመው ሲሄዱ፣ ደጀን የሆኑት ጠባቂዎች ደግሞ ታቦቱን ተከተሉ፤ በዚህ ጊዜ ሁሉ መለከቶቹ ባለማቋረጥ ይነፉ ነበር። 10ኢያሱ ሕዝቡን፣ “የማሸበሪያ ጩኸት አታሰሙ፤ ድምፃችሁ ከፍ ብሎ አይሰማ፤ ጩኹ እስከምላችሁም ቀን ድረስ ከአፋችሁ አንዲት ቃል አትውጣ፤ የምትጮኹት ከዚያ በኋላ ነው” ሲል አዘዛቸው።

11ስለዚህ ኢያሱ የእግዚአብሔርን ታቦት ተሸክመው፣ ከተማዪቱን አንድ ጊዜ እንዲዞሩ አደረገ። ከዚያም ሕዝቡ ወደ ሰፈር ተመልሰው ዐደሩ።

12ኢያሱ በማግስቱም ማልዶ ተነሣ፤ ካህናቱም የእግዚአብሔርን ታቦት ተሸከሙ። 13ሰባቱም ካህናት ሰባት ቀንደ መለከት ይዘው በእግዚአብሔር ታቦት ፊት እየሄዱ፣ መለከቱን ባለማቋረጥ ይነፉ ጀመር፤ የታጠቁ ተዋጊዎችም እነዚህን በመቅደም ሲሄዱ፣ የደጀን ጠባቂዎቹ ደግሞ የእግዚአብሔርን ታቦት ይከተሉ ነበር፤ ካህናቱም ሳያቋርጡ መለከት ይነፉ ነበር። 14በሁለተኛውም ቀን ከተማዪቱን አንድ ጊዜ ከዞሩ በኋላ ወደ ሰፈር ተመለሱ፤ ስድስት ቀን ሙሉም እንዲሁ አደረጉ።

15በሰባተኛው ቀን ገና ጎሕ ሲቀድ ተነሡ፤ እንደ በፊቱም ከተማዪቱን ሰባት ጊዜ ዞሩ፤ ከተማዪቱን ሰባት ጊዜ የዞሯትም በዚያን ቀን ብቻ ነው። 16በሰባተኛው ዙር ላይ ካህናቱ መለከቱን ሲነፉ፣ ኢያሱ ሕዝቡን እንዲህ ሲል አዘዘ፤ “እግዚአብሔር ይህችን ከተማ ሰጥቷችኋልና ጩኹ 17ከተማዪቱና በውስጧ ያለው ሁሉ ለእግዚአብሔር የተለየ ስለሆነ ፈጽማችሁ ዐጥፉ6፥17 የዕብራይስጡ ቃል አንድን ሰው ወይም ነገር ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ለእግዚአብሔር መስጠት ማለት ነው። እኛ የላክናቸውን ሰላዮች ስለ ሸሸገች ጋለሞታዪቱ6፥17 በዚህም ሆነ በቍጥር 22 እና 25 ላይ፣ የእንግዳ ማረፊያ ተብሎ ሊተረጐም ይችላል። ረዓብ ብቻና ከእርሷ ጋር በቤቷ ውስጥ ያሉት ሁሉ ይትረፉ። 18እናንተ ግን ዕርም ከሆኑት ነገሮች አንዳች በመውሰድ በራሳችሁ ላይ ጥፋት እንዳታመጡ እጃችሁን ሰብስቡ፤ ያለዚያ የእስራኤልን ሰፈር ለጥፋት ትዳርጋላችሁ፤ ክፉ ነገር እንዲደርስበትም ታደርጋላችሁ፤ 19ብሩና ወርቁ እንዲሁም የናሱና የብረቱ ዕቃ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ስለሆነ፣ ወደ እግዚአብሔር ግምጃ ቤት ይግባ።”

20መለከቱ ሲነፋ ሕዝቡ ጮኸ፤ የመለከቱ ድምፅ ተሰምቶ፣ ሕዝቡ በኀይል ሲጮኽ ቅጥሩ ፈረሰ፤ እያንዳንዱም ሰው ሰተት ብሎ ገባ፤ ከተማዪቱም በእጃቸው ወደቀች። 21በከተማዪቱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፣ ማለትም ወንዱንና ሴቱን፣ ወጣቱንና ሽማግሌውን፣ ከብቱንና በጕን እንዲሁም አህያውን በሰይፍ ስለት ፈጽመው አጠፉ።

22ኢያሱ ምድሪቱን የሰለሉትን ሁለቱን ሰዎች፣ “ወደ ጋለሞታዪቱ ቤት ሂዱ፤ በማላችሁላትም መሠረት እርሷንና የእርሷ የሆነውን ሁሉ ከዚያ አውጡ” አላቸው። 23ስለዚህ ሁለቱ ወጣት ሰላዮች ገብተው ረዓብን፣ አባቷንና እናቷን፣ ወንድሞቿንና የእርሷ የሆኑትን ሁሉ ከዚያ አወጧቸው። ቤተ ዘመዶቿንም ሁሉ አውጥተው ከእስራኤል ሰፈር ውጭ አስቀመጧቸው።

24ከዚያም ከተማዪቱን በሙሉ፣ በውስጧ ያለውንም ሁሉ አቃጠሉ፤ ብሩንና ወርቁን፣ የናሱንና የብረቱን ዕቃ ግን በእግዚአብሔር ግምጃ ቤት አኖሩ። 25ኢያሪኮን እንዲሰልሉ ኢያሱ የላካቸውን ሰዎች ስለ ደበቀች፣ ጋለሞታዪቱን ረዓብን፣ ቤተ ሰቧንና የእርሷ የሆኑትን ሁሉ አዳናቸው፤ እርሷም እስከ ዛሬ ድረስ በእስራኤላውያን መካከል ትኖራለች።

26በዚያን ጊዜም ኢያሱ፣ እንዲህ ሲል ማለ፤ “ይህችን ከተማ መልሶ የሚሠራት ሰው በእግዚአብሔር ፊት የተረገመ ይሁን፤

“መሠረቷን ሲጥል፣

የበኵር ልጁ ይጥፋ፤

ቅጥሮቿንም ሲያቆም፣

የመጨረሻ ልጁ ይጥፋ”

ብሎ ማለ።

27ስለዚህ እግዚአብሔር ከኢያሱ ጋር ነበር፤ ዝናውም በምድሪቱ ሁሉ ላይ ወጣ።

New International Reader’s Version

Joshua 6:1-27

1The gates of Jericho were shut tight and guarded closely because of the Israelites. No one went out. No one came in.

2Then the Lord said to Joshua, “I have handed Jericho over to you. I have also handed over to you its king and its fighting men. 3March around the city once with all your fighting men. In fact, do it for six days. 4Have seven priests get trumpets made out of rams’ horns. They must carry them in front of the ark. On the seventh day, march around the city seven times. Tell the priests to blow the trumpets as you march. 5You will hear them blow a long blast on the trumpets. When you do, tell the whole army to give a loud shout. The wall of the city will fall down. Then the whole army will march up to the city. Everyone will go straight in.”

6So Joshua, the son of Nun, called for the priests. He said to them, “Go and get the ark of the covenant of the Lord. I want seven of you to carry trumpets in front of it.” 7He gave an order to the army. He said, “Move out! March around the city. Some of the fighting men must march in front of the ark of the Lord.”

8When Joshua had spoken to the men, the seven priests went forward. They were carrying the seven trumpets as they marched in front of the ark of the Lord. They were blowing the trumpets. The ark of the Lord’s covenant was carried behind the priests. 9Some of the fighting men marched ahead of the priests who were blowing the trumpets. The others followed behind the ark and guarded all the priests. That whole time the priests were blowing the trumpets. 10But Joshua had given an order to the army. He had said, “Don’t give a war cry. Don’t raise your voices. Don’t say a word until the day I tell you to shout. Then shout!” 11So he had the ark of the Lord carried around the city once. Then the army returned to camp. They spent the night there.

12Joshua got up early the next morning. The priests went and got the ark of the Lord. 13The seven priests carrying the seven trumpets started out. They marched in front of the ark of the Lord. They blew the trumpets. Some of the fighting men marched ahead of them. The others followed behind the ark and guarded all of them. The priests kept blowing the trumpets. 14On the second day they marched around the city once. Then the army returned to camp. They did all those things for six days.

15On the seventh day, they got up at sunrise. They marched around the city, just as they had done before. But on that day they went around it seven times. 16On the seventh time around, the priests blew a long blast on the trumpets. Then Joshua gave a command to the army. He said, “Shout! The Lord has given you the city! 17The city and everything in it must be set apart to the Lord to be destroyed. But the prostitute Rahab and all those with her in her house must be spared. That’s because she hid the spies we sent. 18But keep away from the things that have been set apart to the Lord. If you take any of them, you will be destroyed. And you will bring trouble on the camp of Israel. You will cause it to be destroyed. 19All the silver and gold is holy. It is set apart to the Lord. So are all the things made out of bronze and iron. All those things must be added to the treasures kept in the Lord’s house.”

20The priests blew the trumpets. As soon as the army heard the sound, they gave a loud shout. Then the wall fell down. Everyone charged straight in. So they took the city. 21They set it apart to the Lord to be destroyed. They destroyed every living thing in it with their swords. They killed men and women. They wiped out young people and old people. They destroyed cattle, sheep and donkeys.

22Then Joshua spoke to the two men who had gone in to check out the land. He said, “Go into the prostitute’s house. Bring her out. Also bring out everyone with her. That’s what you promised her you would do.” 23So the young men who had checked out the land went into Rahab’s house. They brought her out along with her parents and brothers and sisters. They brought out everyone else there with her. They put them in a place outside the camp of Israel.

24Then they burned the whole city and everything in it. But they added the silver and gold to the treasures kept in the Lord’s house. They also put there the things made out of bronze and iron. 25But Joshua spared the prostitute Rahab. He spared her family. He also spared everyone else in the house with her. He did it because she hid the spies he had sent to Jericho. Rahab lives among the Israelites to this day.

26At that time Joshua made a promise and called down a curse. He said, “May the person who tries to rebuild this city of Jericho be under the Lord’s curse.

“If that person lays its foundations,

it will cost the life of his oldest son.

If he sets up its gates,

it will cost the life of his youngest son.”

27So the Lord was with Joshua. And Joshua became famous everywhere in the land.