ኢዩኤል 3 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 3:1-21

የተፈረደባቸው ሕዝቦች

1“በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜ፣

የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ምርኮ ስመልስ፣

2አሕዛብን ሁሉ እሰበስባለሁ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም3፥2 ኢዮሣፍጥ፣ የስሙ ትርጕም እግዚአብሔር ይፈርዳል ማለት ነው፤ 12 ላይም እንዲሁ፤ ሸለቆ አወርዳቸዋለሁ፤

ስለ ርስቴ፣ ስለ ሕዝቤ፣ ስለ እስራኤል፣

በዚያ ልፈርድባቸው እገባለሁ፤

ምድሬን ከፋፍለዋል፤

ሕዝቤንም በሕዝቦች መካከል በታትነዋልና።

3በሕዝቤ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ፤

ወንዶች ልጆችን በዝሙት ዐዳሪዎች ለወጡ፤

ወይን ጠጅ ለመጠጣትም፣

ሴቶች ልጆችን ሸጡ።

4“ጢሮስና ሲዶና እንዲሁም እናንተ የፍልስጥኤም ግዛቶች ሁሉ ሆይ፤ እንግዲህ በእኔ ላይ ምን አላችሁ? ስላደረግሁት ነገር ብድር ልትመልሱልኝ ነውን? የምትመልሱልኝ ከሆነ፣ በፍጥነትና በችኰላ እናንተ ያደረጋችሁትን በራሳችሁ ላይ መልሼ አደርግባችኋለሁ። 5ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤ የተመረጠውንም ንብረቴን ተሸክማችሁ ወደ ቤተ መቅደሳችሁ አስገብታችኋልና። 6ከገዛ ምድራቸው ልታርቋቸው፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሰዎች ለግሪኮች ሸጣችኋቸው።

7“እነሆ፤ እነርሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች አነሣሣቸዋለሁ፤ እናንተም ያደረጋችሁትን በገዛ ራሳችሁ ላይ እመልስባችኋለሁ። 8ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻችሁን ለይሁዳ ሰዎች ሸጣለሁ፤ እነርሱም መልሰው በሩቅ ላሉት ለሳባ ሰዎች ይሸጧቸዋል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሯልና።

9በሕዝቦች መካከል ይህን ዐውጁ፤

ለጦርነት ተዘጋጁ፤

ተዋጊዎችን አነሣሡ፤

ጦረኞችም ሁሉ ቀርበው ያጥቁ።

10ማረሻችሁ ሰይፍ፣

ማጭዳችሁም ጦር እንዲሆን ቀጥቅጡት፤

ደካማውም ሰው፣

“እኔ ብርቱ ነኝ” ይበል።

11እናንት በዙሪያ ያላችሁ ሕዝቦች ሁላችሁ፤

ፈጥናችሁ ኑ፤ በዚያም ተሰብሰቡ።

እግዚአብሔር ሆይ፤ ተዋጊዎችህን ወደዚያ አውርድ!

12“ሕዝቦች ይነሡ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም ሸለቆ ፈጥነው ይውረዱ፤

ዙሪያውን ባሉት ሕዝቦች ሁሉ ላይ ልፈርድ፣

በዚያ እቀመጣለሁና።

13ማጭዱን ስደዱ፤

መከሩ ደርሷልና፤

ኑ ወይኑን ርገጡ፤

የወይን መጭመቂያው ሞልቶ፣

ከጕድጓዶቹም ተርፎ ፈስሷልና፤

ክፋታቸው እንደዚህ ታላቅ ነው።”

14ብዙ ሕዝብ፣ በጣም ብዙ ሕዝብ፣

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ ተሰብስቧል፤

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ፣

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና።

15ፀሓይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤

ከዋክብትም ከእንግዲህ አያበሩም።

16እግዚአብሔር ከጽዮን ጮኾ ይናገራል፤

ከኢየሩሳሌም ያንጐደጕዳል፤

ሰማይና ምድርም ይናወጣሉ፤

እግዚአብሔር ግን ለሕዝቡ መሸሸጊያ፣

ለእስራኤልም ልጆች መጠጊያ ይሆናል።

በረከት ለእግዚአብሔር ሕዝብ

17“ከዚያም እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር

በቅዱሱ ተራራዬ በጽዮን እንደምኖር ታውቃላችሁ፤

ኢየሩሳሌም የተቀደሰች ትሆናለች፤

ከእንግዲህም ወዲያ ባዕዳን አይወርሯትም።

18“በዚያ ጊዜ ተራሮች፣ አዲስ የወይን ጠጅ ያንጠባጥባሉ፤

ኰረብቶችም ወተት ያፈስሳሉ፤

በይሁዳ ያሉ ሸለቆዎች3፥18 ወይም የሸጢም ሸለቆ ሁሉ ውሃ ያጐርፋሉ፤

ከእግዚአብሔር ቤት ምንጭ ይፈልቃል፤

የሰጢምን ሸለቆ ያጠጣል።

19ግብፅ ባድማ፣

ኤዶምም ምድረ በዳ ትሆናለች፤

በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ፣

በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ፈጽመዋልና።

20ይሁዳ ለዘላለም፣

ኢየሩሳሌምም ለትውልድ ሁሉ መኖሪያ ትሆናለች፤

21ደማቸውን እበቀላለሁ፤

በደለኛውንም ንጹሕ አላደርግም።”

እግዚአብሔር በጽዮን ይኖራል!

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

约珥书 3:1-21

上帝要审判万国

1“到那日,在我复兴犹大耶路撒冷的时候, 2我要聚集万国,带他们下到约沙法3:2 约沙法”意思是“耶和华审判”。谷,在那里审判他们,因为他们把我的子民,就是我的产业以色列,分散到各国,并瓜分我的土地。 3他们抽签分了我的子民,将男童换妓女,卖女童买酒喝。

4泰尔西顿非利士境内所有的人啊,你们为什么这样对我?你们要报复我吗?如果你们是报复我,我必速速使你们遭报应。 5你们夺去我的金银,抢走我的珍宝,拿去放在你们的庙中, 6并把犹大耶路撒冷的居民卖给希腊人,使他们远离家乡。 7然而,他们被卖到哪里,我要从哪里把他们带回来,并要使你们得到报应, 8我要把你们的儿女卖给犹大人,犹大人必把他们卖给远方的示巴人。这是耶和华说的。”

9你们去向万国宣告:

“要召集勇士,征调军队,

前去打仗!

10要将犁头打成刀剑,

把镰刀铸成矛头,

软弱的人也要做勇士!

11四围的列国啊,

你们快快聚集到那里吧!”

耶和华啊,

求你差遣大能的勇士降临。

12“万国都要起来,

上到约沙法谷受审判,

因为我要坐在那里审判他们。

13开镰吧,因为庄稼熟了;

踩踏吧,因为榨酒池的葡萄满了。

他们恶贯满盈,如酒池满溢。”

14千千万万的人聚集在审判谷,

因为耶和华的日子要临到那里。

15日月昏暗,

星辰无光。

16耶和华从锡安发出怒吼,

耶路撒冷发出雷声,

天地为之震动。

但耶和华却是祂子民的避难所,

以色列人的堡垒。

17“这样,你们就知道我是你们的上帝耶和华,

我住在锡安——我的圣山上。

耶路撒冷必成为圣地,

外族人必不再侵犯它。

18“到那日,群山要滴下甜酒,

丘陵要流出乳汁。

犹大的溪涧碧水常流,

必有清泉从耶和华的殿中流出,

浇灌什亭谷。

19埃及必一片荒凉,

以东必成为不毛之地,

因为他们曾残暴地对待犹大人,

犹大滥杀无辜。

20犹大必人口兴盛,

耶路撒冷必存到万代。

21我必追讨3:21 追讨”希伯来文是“洗净”。尚未追讨的血债,

因为耶和华住在锡安。”