ኢሳይያስ 52 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 52:1-15

1ጽዮን ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤

ኀይልን ልበሺ፤

ቅድስቲቱ ከተማ፤ ኢየሩሳሌም ሆይ!

የክብር ልብስሽን ልበሺ፤

ያልተገረዘ የረከሰም

ከእንግዲህ ወደ አንቺ አይገባም።

2ትቢያሽን አራግፊ፤

ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ በዙፋንሽ ላይ ተቀመጪ፤

ምርኮኛዪቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፤

የዐንገትሽን የእስራት ሰንሰለት አውልቀሽ ጣዪ።

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ያለ ዋጋ ተሸጣችሁ ነበር፤

ያለ ገንዘብ ትቤዣላችሁ።”

4ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በመጀመሪያ ሕዝቤ ይኖር ዘንድ ወደ ግብፅ ወረደ፤

በኋላም አሦር ያለ ምክንያት አስጨንቆ ገዛው።

5“አሁን እዚህ ምን አለኝ?” ይላል እግዚአብሔር

“ሕዝቤ ያለ ምክንያት ተወስዷል፤

የገዟቸው ተሣልቀውባቸዋል”52፥5 የሙት ባሕር ጥቅሎችና ቩልጌት ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ሙሾ ይላል።

ይላል እግዚአብሔር

“ቀኑን ሙሉ፣

ስሜ ያለ ማቋረጥ ይሰደባል።

6ስለዚህ ሕዝቤ ስሜን ያውቃል፤

በዚያ ቀንም፣

አስቀድሜ የተናገርሁ እኔ መሆኔን ይረዳል፤

እነሆ፤ እኔው ነኝ።”

7በተራሮች ላይ የቆሙ፣

የምሥራች ይዘው የሚመጡ እግሮች፣

ሰላምን የሚናገሩ፣

መልካም ዜና የሚያበሥሩ፣

ድነትን የሚያውጁ፣

ጽዮንንም፣

“አምላክሽ ነግሧል” የሚሉ እንዴት ያማሩ ናቸው።

8ስሚ፤ ጠባቂዎችሽ ድምፃቸውን ከፍ አድርገዋል፤

በአንድነት በእልልታ ይዘምራሉ።

እግዚአብሔር ወደ ጽዮን ሲመለስ፣

በዐይኖቻቸው ያያሉ።

9እናንት የኢየሩሳሌም ፍርስራሾች፣

በአንድነት በእልልታ ዘምሩ፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን አጽናንቷል፤

ኢየሩሳሌምንም ተቤዥቷልና።

10እግዚአብሔር በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣

የተቀደሰ ክንዱን ይገልጣል፤

በምድር ዳርቻዎች ያሉ ሁሉ፣

የአምላካችንን ማዳን ያያሉ።

11እናንት የእግዚአብሔርን ዕቃ የምትሸከሙ፣

ተለዩ፤ ተለዩ፤ ከዚያ ውጡ፤

ርኩስ ነገር አትንኩ፤

ከዚያ ውጡ ንጹሓንም ሁኑ።

12ሆኖም በችኰላ አትወጡም፤

ሸሽታችሁም አትሄዱም፤

እግዚአብሔር ፊት ፊታችሁ ይሄዳል፤

የእስራኤል አምላክ ደጀን ይሆናችኋል።

የባሪያው ሥቃይና ክብር

13እነሆ፤ ባሪያዬ የሚያከናውነው በማስተዋል ነው፤52፥13 ወይም ባሪያዬ ይበለጽጋል

ገናና ይሆናል፤ ከፍ ከፍ ይላል፤ እጅግ ይከብራልም።

14ብዙዎች በእርሱ52፥14 ዕብራይስጡ፣ በአንተ ይላል። እስኪደነግጡ ድረስ፣

መልኩ ከማንም ሰው ተለየ፤

ከሰው ልጆችም ሁሉ ይልቅ ተጐሳቈለ።

15ስለዚህ ብዙ መንግሥታትን ያስደንቃል፤

በእርሱ ምክንያት ነገሥታት አፋቸውን ይይዛሉ፤

ያልተነገራቸውን ያያሉ፤

ያልሰሙትን ያስተውላሉ።

Thai New Contemporary Bible

อิสยาห์ 52:1-15

1ตื่นเถิด ตื่นเถิด ศิโยนเอ๋ย

จงสวมกำลังวังชา

เยรูซาเล็มนครบริสุทธิ์เอ๋ย

จงสวมอาภรณ์งามตระการของเจ้าเถิด

ผู้ไม่ได้เข้าสุหนัตและผู้มีมลทิน

จะไม่เข้ามาในเจ้าอีก

2จงสะบัดฝุ่นธุลีทิ้งไป

จงลุกขึ้น นั่งบนบัลลังก์เถิด เยรูซาเล็มเอ๋ย

จงปลดโซ่ตรวนที่ล่ามคอของเจ้าเถิด

ธิดาแห่งศิโยน52:2 คือ ชาวเยรูซาเล็มผู้ตกเป็นเชลย

3เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“เจ้าถูกขายโดยไม่มีราคาค่างวด

เจ้าก็จะได้รับการไถ่คืนมาโดยไม่ต้องจ่ายเงิน”

4เพราะพระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า

“เดิมทีประชากรของเราลงไปอาศัยอยู่ที่อียิปต์

บัดนี้อัสซีเรียได้กดขี่ข่มเหงพวกเขา”

5องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า “และบัดนี้เรามีอะไรที่นี่บ้าง?

“เพราะประชากรของเราถูกพาตัวไปเปล่าๆ

และผู้ครอบครองเขาก็เย้ยหยัน52:5 ฉบับ MT. ว่าคร่ำครวญ

องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

“ตลอดทั้งวัน

นามของเราถูกหมิ่นประมาทอยู่เสมอ

6ดังนั้นประชากรของเราจะรู้จักนามของเรา

เพราะฉะนั้นในวันนั้นเขาจะรู้ว่า

เราเองเป็นผู้บอกไว้ล่วงหน้า

ใช่ เป็นเราเอง”

7เท้าของผู้นำข่าวดีมาบนภูเขา

ช่างงดงามยิ่งนัก

ผู้ประกาศสันติภาพ

ผู้แจ้งข่าวดี

ผู้ประกาศความรอด

ผู้กล่าวกับศิโยนว่า

“พระเจ้าของเจ้าทรงครอบครอง!”

8จงฟังเถิด! พวกยามของเจ้าส่งเสียงร้อง

ร่วมกันโห่ร้องด้วยความชื่นชมยินดี

เมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าเสด็จกลับมายังศิโยน

พวกเขาจะเห็นกับตา

9จงร่วมกันเปล่งเสียงร้องเพลงเบิกบานเถิด

ซากปรักหักพังของเยรูซาเล็มเอ๋ย

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงปลอบโยนประชากรของพระองค์แล้ว

พระองค์ได้ทรงไถ่เยรูซาเล็มแล้ว

10องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงเผยพระกรอันบริสุทธิ์

ต่อหน้าต่อตาประชาชาติทั้งปวง

ทั่วโลกจะเห็น

ความรอดแห่งพระเจ้าของเรา

11ไปเถิด ไปเสีย จงออกจากที่นั่น!

อย่าแตะต้องสิ่งมลทิน!

จงออกมาจากที่นั่น และรักษาตัวให้บริสุทธิ์

พวกเจ้าผู้อัญเชิญภาชนะขององค์พระผู้เป็นเจ้า

12แต่เจ้าจะไม่จากมาด้วยความรีบร้อน

หรือเตลิดหนีมา

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าจะเสด็จนำหน้าเจ้า

พระเจ้าแห่งอิสราเอลจะทรงระวังหลังให้เจ้า

การทนทุกข์และสง่าราศีของผู้รับใช้

13ดูเถิด ผู้รับใช้ของเราจะทำการอย่างชาญฉลาด52:13 หรือจะเจริญรุ่งเรือง

เขาจะได้รับการยกย่องเทิดทูนและสดุดีอย่างสูงส่ง

14คนเป็นอันมากตื่นตะลึงเพราะเขา52:14 ภาษาฮีบรูว่าท่าน

เพราะรูปลักษณ์ของเขาเสียโฉมไปจนไม่มีใครเหมือน

และรูปร่างของเขาก็เสียไปจนดูไม่เหมือนมนุษย์

15เขาก็จะทำให้หลายประชาชาติตกตะลึง52:15 ภาษาฮีบรูว่าเขาก็จะประพรมหลายประชาชาติ

และเขาจะทำให้บรรดากษัตริย์ปิดปาก

เพราะพวกเขาจะเห็นสิ่งที่ไม่เคยมีใครบอกพวกเขามาก่อน

และจะเข้าใจสิ่งที่ไม่เคยได้ยินได้ฟังมาก่อน