ኤርምያስ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኤርምያስ 1:1-19

1የኬልቅያስ ልጅ፣ ኤርምያስ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤ አባቱ በብንያም አገር በዓናቶት ከሚገኙት ካህናት አንዱ ነበረ። 2የእግዚአብሔር ቃል የይሁዳ ንጉሥ፣ የአሞን ልጅ ኢዮስያስ በነገሠ በዐሥራ ሦስተኛው ዓመት ወደ ኤርምያስ መጣ፤ 3ደግሞም በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ንግሠ ዘመን፤ እንዲሁም በይሁዳ ንጉሥ፣ በኢዮስያስ ልጅ በሴዴቅያስ ንግሠ ዘመን፤ እስከ ዐሥራ አንደኛው ዓመት መጨረሻ ድረስ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ተማርኮ እስከ ሄደበት እስከ አምስተኛው ወር ድረስ ወደ እርሱ ይመጣ ነበር።

የኤርምያስ መጠራት

4የእግዚአብሔር ቃል ወደ እኔ መጣ፤ እንዲህም አለኝ፤

5“በማሕፀን ሳልሠራህ ዐወቅሁህ፤

ከመወለድህ በፊት ለየሁህ፤1፥5 ወይም መረጥሁህ

ለሕዝቦችም ነቢይ እንድትሆን ሾምሁህ።”

6እኔም፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዴት እንደምናገር አላውቅም፤ ገና ሕፃን ልጅ ነኝና” አልሁ።

7እግዚአብሔር ግን እንዲህ አለኝ፤ “ ‘ገና ሕፃን ልጅ ነኝ’ አትበል፤ ወደምልክህ ሁሉ ሄደህ፣ ያዘዝሁህን ሁሉ ትናገራለህ፤ 8እኔ አድንህ ዘንድ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራቸው” ይላል እግዚአብሔር

9እግዚአብሔርም እጁን ዘርግቶ አፌን ዳሰሰና እንዲህ አለኝ፤ “እነሆ፤ ቃሌን በአፍህ አኑሬአለሁ፤ 10እንግዲህ፣ እንድትነቅልና እንድታፈርስ፣ እንድታጠፋና እንድትገለብጥ፣ እንድታንጽና እንድትተክል በአሕዛብና በመንግሥታት ላይ ዛሬ ሾምሁህ።”

11የእግዚአብሔር ቃል፣ “ኤርምያስ ሆይ፣ ምን ታያለህ?” ሲል ወደ እኔ መጣ።

እኔም፣ “የለውዝ በትር አያለሁ” አልሁ።

12እግዚአብሔርም፣ “ትክክል አይተሃል፤ ቃሌን እፈጽመው ዘንድ እተጋለሁና”1፥12 እተጋለሁ ለሚለው የዕብራይስጡ አነባበብ የለውዝ በትር ከሚለው ጋር ይመሳሰላል። አለኝ።

13ዳግመኛም የእግዚአብሔር ቃል፣ “ምን ታያለህ?” ሲል ወደ እኔ መጣ።

እኔም፣ “አንድ የሚፈላ ማሰሮ አያለሁ፤ አፉም ከሰሜን ወደዚህ ያዘነበለ ነው” አልሁ።

14እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ፤ “ከሰሜን በምድሪቱ በሚኖሩ ሁሉ ላይ ድንገት መዓት ይወርድባቸዋል። 15እነሆ፤ የሰሜን መንግሥታትን ሕዝቦች ሁሉ እጠራለሁ” ይላል እግዚአብሔር

“ንጉሦቻቸው ይመጣሉ፤

ዙፋናቸውን በኢየሩሳሌም መግቢያ በሮች፣

በቅጥሮቿ ዙሪያ ሁሉ፣

በይሁዳም ከተሞች ሁሉ ይዘረጋሉ።

16እኔን በመተው ክፋት ስለ ሠሩ፣

ለሌሎች አማልክት ዕጣን ስላጠኑ፣

እጆቻቸው የሠሯቸውን ስላመለኩ፣

በሕዝቤ ላይ ፍርድን ዐውጄአለሁ።

17“አንተ ግን ወገብህን ታጠቅ፤ ተነሥተህም ያዘዝሁን ሁሉ ንገራቸው፤ አትፍራቸውም፤ አለዚያ በፊታቸው አስፈራሃለሁ። 18እነሆ፤ ዛሬ በመላዪቱ ምድር ላይ አስነሣሃለሁ፤ ይኸውም የይሁዳን ነገሥታት፣ አለቆቿን፣ ካህናቷንና የምድሪቱን ሕዝብ ሁሉ መቋቋም እንድትችል የተመሸገ ከተማ፣ የብረት ምሰሶና የናስ ቅጥር አድርጌሃለሁ። 19ይዋጉሃል፤ ዳሩ ግን አድንህ ዘንድ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አያሸንፉህም” ይላል እግዚአብሔር

Thai New Contemporary Bible

เยเรมีย์ 1:1-19

1นี่คือถ้อยคำของเยเรมีย์บุตรฮิลคียาห์ เยเรมีย์เป็นปุโรหิตคนหนึ่งอยู่ที่อานาโธทในเขตเบนยามิน 2พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงเยเรมีย์ในปีที่สิบสามของรัชกาลโยสิยาห์ซึ่งเป็นโอรสกษัตริย์อาโมนแห่งยูดาห์ 3และตลอดรัชกาลเยโฮยาคิมซึ่งเป็นโอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์จนถึงเดือนที่ห้าของปีที่สิบเอ็ดแห่งรัชกาลเศเดคียาห์ซึ่งเป็นโอรสกษัตริย์โยสิยาห์แห่งยูดาห์ เมื่อชาวกรุงเยรูซาเล็มถูกกวาดต้อนไปเป็นเชลย

พระเจ้าทรงเรียกเยเรมีย์

4พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าความว่า

5“เรารู้จัก1:5 หรือเลือกสรรเจ้าตั้งแต่ก่อนที่เราจะปั้นเจ้าในครรภ์มารดา

ก่อนเจ้าจะคลอดออกมา เราได้แยกเจ้าไว้แล้ว

เราได้แต่งตั้งเจ้าให้เป็นผู้เผยพระวจนะแก่ประชาชาติทั้งหลาย”

6ข้าพเจ้ากราบทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิต ข้าพระองค์ไม่รู้ว่าจะพูดอย่างไร เพราะข้าพระองค์ยังเด็กเกินไป”

7แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “อย่าพูดว่า ‘ข้าพระองค์ยังเด็กเกินไป’ เจ้าต้องไปพบทุกคนที่เราใช้เจ้าไป ไม่ว่าเราสั่งอย่างไร เจ้าต้องพูดไปตามนั้น 8อย่ากลัวพวกเขาเลย เพราะเราอยู่กับเจ้าและจะช่วยกู้เจ้า” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

9แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงยื่นพระหัตถ์มาแตะปากของข้าพเจ้าและตรัสว่า “บัดนี้เราเอาถ้อยคำของเราใส่ไว้ในปากของเจ้า 10ดูเถิด วันนี้เราแต่งตั้งเจ้าไว้เหนือบรรดาประชาชาติและอาณาจักรต่างๆ ให้รื้อออกและทลายลง ให้ทำลายและโค่นล้ม ให้สร้างและปลูก”

11องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “เยเรมีย์ เจ้าเห็นอะไรบ้าง?”

ข้าพเจ้ากราบทูลว่า “ข้าพระองค์เห็นกิ่งอัลมอนด์พระเจ้าข้า”

12องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “ถูกต้องแล้ว นั่นหมายความว่าเรากำลังเฝ้าดู1:12 เป็นการเล่นคำภาษาฮีบรูที่มีเสียงใกล้เคียงกันคือกิ่งอัลมอนด์ในข้อ 11 และเฝ้าดูในข้อ 12ให้เป็นไปตามคำที่เราได้ลั่นวาจาไว้”

13พระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาถึงข้าพเจ้าอีกครั้งว่า “เจ้าเห็นอะไรบ้าง?”

ข้าพเจ้ากราบทูลว่า “ข้าพระองค์เห็นหม้อน้ำที่กำลังเดือดพล่าน เอียงเทลงมาจากทางทิศเหนือ”

14องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “ภัยพิบัติจากทางเหนือจะถูกเทลงมาบนคนทั้งปวงที่อาศัยในดินแดนนี้ 15เรากำลังจะเรียกกองทัพของบรรดาอาณาจักรทางเหนือมา” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น

“บรรดากษัตริย์ของพวกเขาจะมาตั้งบัลลังก์ของตน

ที่ทางเข้าประตูเมืองทั้งหลายของเยรูซาเล็ม

พวกเขาจะยกทัพมาล้อมรอบกำแพงเมืองต่างๆ

และล้อมหัวเมืองทั้งหมดของยูดาห์

16เราจะประกาศคำพิพากษาประชากรของเรา

เพราะความชั่วร้ายของเขา โทษฐานที่ได้ละทิ้งเราไป

ที่ได้ถวายเครื่องเผาบูชาแก่พระต่างๆ

และที่ได้นมัสการสิ่งที่มือของเขาได้สร้างขึ้น

17“เจ้าจงเตรียมตัวให้พร้อม! ยืนขึ้นพูดกับพวกเขาตามที่เราสั่ง อย่ากลัวพวกเขา มิฉะนั้นเราจะทำให้เจ้ากลัวเมื่ออยู่ต่อหน้าพวกเขา 18วันนี้เราได้ทำให้เจ้าแข็งแกร่งเหมือนเมืองป้อมปราการ เหมือนเสาเหล็กและกำแพงทองสัมฤทธิ์ ที่จะยืนต้านทานต่อทั้งดินแดน คือต่อบรรดากษัตริย์ยูดาห์ ข้าราชการ ปุโรหิต และประชากรทั้งปวง 19พวกเขาจะต่อสู้เจ้า แต่จะไม่ชนะ เพราะเราอยู่กับเจ้า เราจะช่วยกู้เจ้า” องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศดังนั้น