ኢሳይያስ 49 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 49:1-26

የእግዚአብሔር ባሪያ

1እናንት ደሴቶች ስሙኝ፤

እናንት በሩቅ ያላችሁ ሕዝቦች ይህን አድምጡ፤

በእናቴ ማሕፀን ሳለሁ እግዚአብሔር ጠራኝ፤

ከመወለዴ በፊት በስም ጠራኝ።

2አፌን እንደ ተሳለ ሰይፍ አደረገው፤

በእጁ ጥላ ሰወረኝ፤

የተወለወለ ፍላጻ አደረገኝ፤

በሰገባውም ውስጥ ሸሸገኝ።

3እርሱም፣ “እስራኤል፤ አንተ ባሪያዬ ነህ፤

በአንተ ክብሬን እገልጣለሁ” አለኝ።

4እኔ ግን፣ “ዐላማ ሳይኖረኝ እንዲሁ ደከምሁ፤

ምንም ጥቅም ለሌለውና ለከንቱ ነገር ጕልበቴን ጨረስሁ፤

ሆኖም ግን ብድራቴ በእግዚአብሔር እጅ፣

ዋጋዬም በአምላኬ ዘንድ ነው” አልሁ።

5በእግዚአብሔር ዐይን ፊት ከብሬአለሁ፤

አምላኬ ጕልበት ሆኖልኛል፤

ባሪያው እንድሆን ከማሕፀን የሠራኝ፣

ያዕቆብን ወደ እርሱ እንድመልስ፣

እስራኤልን ወደ እርሱ እንድሰበስብ ያደረገኝ፣

እግዚአብሔር አሁንም እንዲህ ይላል፤

6እርሱም፣

“ባሪያዬ መሆንህ፣

የያዕቆብን ነገዶች እንደ ገና መመለስህ፣

የጠበቅኋቸውን እስራኤል መልሰህ ማምጣት ለአንተ ቀላል ነገር ነው፤

ድነቴን እስከ ምድር ዳርቻ እንድታመጣ፣

ለአሕዛብ ብርሃን አደርግሃለሁ” አለኝ።

7እግዚአብሔር

ታዳጊ የሆነው የእስራኤል ቅዱስ፣

ለተናቀውና በሕዝብ ለተጠላው፣

የገዦች አገልጋይ እንዲህ ይላል፤

“ነገሥታት አይተውህ ይነሣሉ፤

ልዑላንም አይተው፤ ይሰግዳሉ፤

ምክንያቱም የመረጠህ የእስራኤል ቅዱስ፣

እግዚአብሔር ታማኝ ነው።”

የእስራኤል እንደ ገና መቋቋም

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በወደድሁ ጊዜ እመልስልሃለሁ፤

በድነትም ቀን እረዳሃለሁ።

ለሕዝቡ ቃል ኪዳን እንድትሆን፣

ምድሪቱን እንደ ገና እንድትሠራት፣

ጠፍ የሆኑትን ርስቶች ለየባለቤታቸው እንድትመልስ፣

እጠብቅሃለሁ፤ እሠራሃለሁም፤

9የተማረኩትን፣ ‘ኑ ውጡ’

በጨለማ ያሉትን፣ ‘ነጻ ሁኑ’ እንድትል አድርጌሃለሁ።

“በየመንገዱ ዳር ይመገባሉ፤

በተራቈተውም ኰረብታ ሁሉ ላይ መሰማሪያ ያገኛሉ።

10አይራቡም፤ አይጠሙም፤

የምድረ በዳ ትኵሳት ወይም የፀሓይ ቃጠሎ አይጐዳቸውም።

የሚራራላቸው ይመራቸዋል፤

በውሃ ምንጭ ዳርም ያሰማራቸዋል።

11ተራሮቼን ሁሉ መንገድ አደርጋለሁ፤

ጐዳናዎቼም ከፍ ይላሉ።

12እነሆ፤ ከሩቅ አገር ይመጣሉ፤

አንዳንዶች ከሰሜን ሌሎች ከምዕራብ፣

የቀሩት ደግሞ ከሲኒም49፥12 የማሶሬቱ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች ግን፣ አስዋን ይላሉ። ይመጣሉ።”

13ሰማያት ሆይ፤ እልል በሉ፤

ምድር ሆይ፤ ደስ ይበልሽ፤

ተራሮች ሆይ፤ በደስታ ዘምሩ፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን ያጽናናል፤

ለተቸገሩትም ይራራልና።

14ጽዮን ግን፣ “እግዚአብሔር ትቶኛል፤

ጌታም ረስቶኛል” አለች።

15“እናት የምታጠባውን ልጇን ልትረሳ ትችላለችን?

ለወለደችውስ ልጅ አትራራለትምን?

ምናልባት እርሷ ትረሳ ይሆናል፣

እኔ ግን አልረሳሽም።

16እነሆ፤ በእጄ መዳፍ ላይ ቀርጬሻለሁ፤

ቅጥሮችሽ ምንጊዜም በፊቴ ናቸው።

17ወንዶች ልጆችሽ ፈጥነው ይመለሳሉ፤

ያፈራረሱሽም ከአንቺ ይሸሻሉ።

18ዐይንሽን ቀና አድርጊ፤ ዙሪያውንም ተመልከቺ፤

ወንዶች ልጆችሽ ሁሉ ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ።

በሕያውነቴ እምላለሁ፤

እነዚህን ሁሉ እንደ ጌጥ ትለብሻቸዋለሽ፤

እንደ ሙሽራም ትጐናጸፊያቸዋለሽ” ይላል እግዚአብሔር

19“ፈራርሰሽ ባድማ ብትሆኚ፣

ምድርሽ ፈጽሞ ቢጠፋ፣

ዛሬ ለሕዝብሽ ጠባብ ብትሆኚም እንኳ፣

የዋጡሽ ከአንቺ ይርቃሉ።

20በሐዘንሽ ዘመን የወለድሻቸው ልጆች፣

ጆሮሽ እየሰማ፣

‘ይህ ቦታ በጣም ጠብቦናል፤

የምንኖርበት በቂ ስፍራ ስጪን’ ይሉሻል።

21በልብሽም እንዲህ ትያለሽ፣

‘እነዚህን የወለደልኝ ማን ነው?

እኔ ሐዘንተኛና መካን፣

የተሰደድሁና የተጠላሁ ነበርሁ፤

እነዚህን ማን አሳደጋቸው?

ብቻዬን ቀርቼ ነበር፤

ታዲያ፣ እነዚህ ከየት መጡ?’ ”

22ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ አሕዛብን በጥቅሻ እጣራለሁ፤

ዐርማዬንም ለሕዝቦች ከፍ አደርጋለሁ፤

ወንዶች ልጆችሽን በዕቅፋቸው ያመጡልሻል፤

ሴቶች ልጆችሽንም በትከሻቸው ይሸከሙልሻል።

23ነገሥታት አሳዳጊ አባቶችሽ፣

እቴጌዎቻቸው ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ፤

በግንባራቸው ተደፍተው ይሰግዱልሻል፤

የእግርሽን ትቢያ ይልሳሉ፤

አንቺም እኔ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቂያለሽ፤

እኔን ተስፋ የሚያደርጉም አያፍሩም።”

24ከተዋጊ ብዝበዛ ማስጣል፣

ከጨካኝስ49፥24 የሙት ባሕር ጥቅሎች፣ ቩልጌትና የሱርስቱ ቅጅ (እንዲሁም የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም 25 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የማሶሬቱ ቅጅ ግን፣ ከጻድቅስ ይላል። ምርኮኞችን ማዳን ይቻላልን?

25እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፤

“ከተዋጊዎች ላይ ምርኮኞች በርግጥ ይወሰዳሉ፤

ከጨካኞችም ላይ ምርኮ ይበዘበዛል፤

ከአንቺ ጋር የሚጣሉትን እጣላቸዋለሁ፤

ልጆችሽንም እታደጋለሁ።

26አስጨናቂዎችሽ የራሳቸውን ሥጋ እንዲበሉ አደርጋቸዋለሁ፤

በወይን ጠጅ እንደሚሰከር ሁሉ፣ በገዛ ደማቸው ይሰክራሉ።

ከዚያም የሰው ዘር ሁሉ፣

እኔ እግዚአብሔር አዳኝሽ፣

ታዳጊሽም የያዕቆብ ኀያል እንደ ሆንሁ ያውቃል።”

Thai New Contemporary Bible

อิสยาห์ 49:1-26

ผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้า

1จงฟังข้าพเจ้าเถิด บรรดาเกาะแก่งทั้งหลายเอ๋ย

ชนชาติไกลโพ้นทั้งหลาย ฟังทางนี้

องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสเรียกข้าพเจ้าตั้งแต่ข้าพเจ้ายังไม่เกิด

ทรงเอ่ยชื่อข้าพเจ้าตั้งแต่ข้าพเจ้าถือกำเนิด

2พระองค์ทรงทำให้ปากของข้าพเจ้าเหมือนดาบคมกริบ

ทรงซ่อนข้าพเจ้าไว้ในร่มเงาแห่งพระหัตถ์

ทรงทำให้ข้าพเจ้าเป็นลูกธนูคมปลาบ

และทรงเก็บข้าพเจ้าไว้ในแล่งธนูของพระองค์

3พระองค์ตรัสกับข้าพเจ้าว่า “อิสราเอล เจ้าเป็นผู้รับใช้ของเรา

เราจะสำแดงเกียรติบารมีของเราในตัวเจ้า”

4แต่ข้าพเจ้ากล่าวว่า “ข้าพเจ้าตรากตรำไปอย่างไร้จุดหมาย

ลงแรงไปโดยเปล่าประโยชน์และไร้ค่า

ถึงกระนั้นสิ่งที่ข้าพเจ้าควรได้ก็อยู่ในพระหัตถ์ขององค์พระผู้เป็นเจ้า

บำเหน็จของข้าพเจ้าอยู่ที่พระเจ้าของข้าพเจ้า”

5และบัดนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

พระองค์ผู้ทรงสร้างข้าพเจ้าในครรภ์มารดา เพื่อให้เป็นผู้รับใช้ของพระองค์

เพื่อนำยาโคบกลับมายังพระองค์

และรวบรวมอิสราเอลมายังพระองค์เอง

เพราะข้าพเจ้ามีเกียรติในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้า

และพระเจ้าทรงเป็นพละกำลังของข้าพเจ้า

6พระองค์ตรัสว่า

“เป็นการเล็กน้อยเกินไปที่จะให้เจ้าเป็นผู้รับใช้ของเรา

เพื่อฟื้นฟูชนเผ่าต่างๆ ของยาโคบให้กลับสู่สภาพเดิม

และนำชนอิสราเอลเหล่านั้นซึ่งเราสงวนไว้กลับมาหาเรา

เราจะให้เจ้าเป็นแสงสว่างสำหรับชนต่างชาติด้วย

เพื่อเจ้าจะนำความรอดของเราไปจนถึงสุดปลายแผ่นดินโลก”

7พระยาห์เวห์ พระผู้ไถ่

องค์บริสุทธิ์แห่งอิสราเอล

ตรัสแก่ผู้นั้นซึ่งเป็นที่รังเกียจเดียดฉันท์ของชาติ

ผู้เป็นคนรับใช้ของบรรดาผู้ครอบครองนั้นว่า

“กษัตริย์ทั้งหลายจะเห็นเจ้าแล้วยืนขึ้น

เจ้านายทั้งปวงจะเห็นเจ้าแล้วหมอบกราบ

เนื่องด้วยองค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงซื่อสัตย์

องค์บริสุทธิ์แห่งอิสราเอลผู้ทรงเลือกสรรเจ้า”

การกอบกู้อิสราเอล

8องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“ในเวลาแห่งความโปรดปราน เราจะตอบเจ้า

และในวันแห่งความรอด เราจะช่วยเจ้า

เราจะปกป้องเจ้า

และทำให้เจ้าเป็นพันธสัญญาแก่เหล่าประชากร

เพื่อให้ดินแดนนั้นกลับคืนสู่ปกติสุข

และรื้อฟื้นกรรมสิทธิ์ซึ่งถูกทิ้งร้างขึ้นมาใหม่

9เพื่อกล่าวแก่เชลยว่า ‘ออกมาเถิด’

และกล่าวแก่ผู้อยู่ในความมืดมนว่า ‘จงเป็นอิสระ!’

“พวกเขาจะเลี้ยงชีพอยู่ริมทาง

และพบทุ่งหญ้าบนเนินเขาแห้งแล้งทุกแห่ง

10เขาจะไม่หิวหรือกระหาย

แสงอาทิตย์แรงกล้าและลมทะเลทรายอันร้อนระอุจะไม่แผดเผาเขาอีกต่อไป

พระองค์ผู้ทรงเอ็นดูสงสารเขาจะนำเขา

และพาเขามายังริมธารน้ำพุ

11เราจะเปลี่ยนภูเขาทุกลูกของเราให้เป็นทางเรียบ

และทางหลวงของเราจะถูกยกขึ้น

12ดูเถิด พวกเขาจะมาจากแดนไกล

บางคนมาจากทางเหนือ บางคนมาจากทางตะวันตก

บางคนก็มาจากอัสวาน49:12 ฉบับ MT. ว่าสินิม

13ฟ้าสวรรค์เอ๋ย จงโห่ร้องยินดี

โลกเอ๋ย จงเปรมปรีดิ์

ภูเขาทั้งหลายเอ๋ย จงเปล่งเสียงร้องเพลง!

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงปลอบโยนประชากรของพระองค์

และจะทรงเอ็นดูสงสารผู้ที่ทุกข์ทรมานของพระองค์

14แต่ศิโยนกล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าทอดทิ้งข้าแล้ว

องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงลืมข้าไปแล้ว”

15“แม่จะลืมลูกน้อยในอก

และจะไม่เอ็นดูสงสารลูกที่นางให้กำเนิดได้หรือ?

แม้นางอาจจะลืมได้

แต่เราจะไม่ลืมเจ้า!

16ดูเถิด เราได้สลักชื่อของเจ้าไว้บนฝ่ามือของเรา

กำแพงของเจ้าอยู่ตรงหน้าเราเสมอ

17ลูกๆ ของเจ้ารีบรุดมา

และบรรดาผู้ที่ทำให้เจ้าเริศร้างก็ไปจากเจ้า

18เงยหน้าขึ้นมองไปรอบๆ เถิด

ลูกๆ ทั้งหมดของเจ้าพากันมาหาเจ้า”

องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “เรามีชีวิตอยู่แน่ฉันใด

พวกเขาจะเป็นเครื่องประดับตกแต่งของเจ้าฉันนั้น

เจ้าจะเหมือนเจ้าสาว มีพวกเขาเป็นอาภรณ์ประดับ

19“ถึงแม้ว่าเจ้าถูกทำให้เป็นซากปรักหักพังและเริศร้าง

ดินแดนของเจ้าถูกทิ้งร้าง

แต่บัดนี้เจ้าจะกลับคับแคบเกินไปสำหรับประชากรของเจ้า

และผู้ที่ล้างผลาญเจ้าจะไปไกลลิบลับ

20ลูกหลานซึ่งเกิดในช่วงที่เจ้าเป็นเชลย

จะพูดให้เจ้าได้ยินว่า

‘ที่นี่คับแคบเกินไปสำหรับเรา

ขอที่อาศัยกว้างขวางกว่านี้เถิด’

21แล้วเจ้าจะรำพึงว่า

‘ใครหนอได้ให้กำเนิดคนทั้งหมดนี้แก่เรา?

เราถูกพลัดพรากและเป็นหมัน

ตกเป็นเชลยและถูกทอดทิ้ง

ใครหนอเลี้ยงดูคนเหล่านี้ขึ้นมา?

เราถูกทิ้งไว้เดียวดาย

แล้วคนเหล่านี้มาจากไหนกัน?’ ”

22พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า

“ดูเถิด เราจะส่งสัญญาณแก่บรรดาชนชาติต่างๆ

เราจะชูธงของเราให้ชนชาติทั้งหลาย

พวกเขาจะอุ้มลูกชายของเจ้าไว้ในอ้อมแขนพากลับมาหาเจ้า

ส่วนลูกสาวของเจ้าจะให้ขี่คอเขามา

23กษัตริย์ทั้งหลายจะเป็นพ่อบุญธรรมของเจ้า

และราชินีทั้งหลายเป็นแม่ผู้เลี้ยงดูเจ้า

พวกเขาจะหมอบกราบซบหน้าลงที่พื้นตรงหน้าเจ้า

เขาจะเลียธุลีแทบเท้าเจ้า

เมื่อนั้นเจ้าจะรู้ว่าเราคือพระยาห์เวห์

ผู้ที่หวังในเราจะไม่ผิดหวัง”

24จะแย่งชิงเหยื่อไปจากนักรบ

หรือจะช่วยเชลยจากบรรดาผู้ดุร้าย49:24 ฉบับ MT. ว่าผู้ชอบธรรม(ดูฉบับ LXX. และข้อ 25)ได้หรือ?

25แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“เชลยจะถูกริบคืนจากนักรบ

สิ่งที่ถูกปล้นจะถูกริบคืนจากผู้ดุร้าย

เราจะต่อสู้กับบรรดาผู้ที่ต่อสู้เจ้า

และเราจะช่วยลูกๆ ของเจ้าให้รอด

26เราจะทำให้ผู้ที่กดขี่ข่มเหงเจ้ากินเนื้อของตนเอง

พวกเขาจะเมาด้วยเลือดของตนเองเหมือนเมาเหล้าองุ่น

และมวลมนุษยชาติจะรู้ว่า

เรา พระยาห์เวห์ คือพระผู้ช่วยให้รอดของเจ้า

เป็นพระผู้ไถ่ของเจ้า องค์ทรงฤทธิ์ของยาโคบ”