ኢሳይያስ 41 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 41:1-29

የእስራኤል ረዳት

1“ደሴቶች ሆይ፤ በፊቴ ዝም በሉ፤

አሕዛብ ኀይላቸውን ያድሱ፤

ቀርበው ይናገሩ፤

በፍርድም ፊት እንገናኝ።

2“ከምሥራቅ አንዱን ያነሣው፣

በጽድቅም ወደ አገልግሎቱ የጠራው ማን ነው?41፥2 ወይም በእያንዳንዱ ርምጃ ድል የሚያጋጥመው

አሕዛብን አሳልፎ ሰጠው፤

ነገሥታትን በፊቱ አስገዛለት

በሰይፉም እንደ ትቢያ አቦነናቸው፤

በቀስቱም በነፋስ እንደ ተበተነ ገለባ አደረጋቸው።

3አሳደዳቸው፤ ያለ ችግርም ዐልፎ ሄደ፤

እግሩም ቀድሞ ባልረገጠው መንገድ ተጓዘ።

4ይህን የሠራና ያደረገ፣

ትውልድን ከጥንት የጠራ ማን ነው?

እኔ እግዚአብሔር ከፊተኛው፣

ከኋለኛውም ጋር፤ እኔው ነኝ።”

5ደሴቶች አይተው ፈሩ፤

የምድር ዳርቾች ደነገጡ፤

ቀረቡ፤ ወደ ፊትም መጡ።

6እያንዳንዱ ይረዳዳል፤

ወንድሙንም፣ “አይዞህ” ይለዋል።

7ባለ እጅ የወርቅ አንጥረኛውን ያበረታታዋል፤

በመዶሻ የሚያሳሳውም፣

በመስፍ ላይ የሚቀጠቅጠውን ያነቃቃዋል፤

ስለ ብየዳም ሥራው፣ “መልካም ነው” ይለዋል፤

የጣዖቱ ምስል እንዳይወድቅም በምስማር ያጣብቀዋል።

8“አንተ ግን፣ ባሪያዬ እስራኤል፣

የመረጥሁህ ያዕቆብ፣

የወዳጄ የአብርሃም ዘር ሆይ፤

9ከምድር ዳርቻ ያመጣሁህ፣

ከአጥናፍም የጠራሁህ፣

‘አንተ ባሪያዬ ነህ’ ያልሁህ፤

መረጥሁህ እንጂ አልጣልሁህም።

10እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤

አምላክህ ነኝና አትደንግጥ።

አበረታሃለሁ፤ እረዳሃለሁ፤

በጽድቄም ቀኝ እጄ ደግፌ እይዝሃለሁ።

11“እነሆ፤ የተቈጡህ ሁሉ፣

እጅግ ያፍራሉ፤ ይዋረዳሉም፤

የሚቋቋሙህ፣

እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤ ይጠፋሉም።

12ጠላቶችህን ብትፈልጋቸው እንኳ፣

አታገኛቸውም፤

የሚዋጉህም፣

እንዳልነበሩ ይሆናሉ።

13እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ‘አትፍራ፤

እረዳሃለሁ’

ብዬ ቀኝ እጅህን እይዛለሁና።

14አንት ትል ያዕቆብ፣

ታናሽ እስራኤል ሆይ፤

‘አትፍራ እኔ እረዳሃለሁ’ ” ይላል እግዚአብሔር

የሚቤዥህ የእስራኤል ቅዱስ ነው።

15“እነሆ፣ አዲስ

የተሳለና ብዙ ጥርስ ያለው ማሄጃ አደርግሃለሁ፤

ተራሮችን ታሄዳለህ፤ ታደቅቃቸዋለህ፤

ኰረብቶችንም ገለባ ታደርጋቸዋለህ።

16ታበጥራቸዋለህ፤ ነፋስ ጠርጎ ይወስዳቸዋል፤

ዐውሎ ነፋስም ይበትናቸዋል።

አንተ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፤

በእስራኤል ቅዱስ ሞገስ ታገኛለህ።

17“ድኾችና ችግረኞች ውሃ ይፈልጋሉ፤

ዳሩ ግን ምንም አያገኙም፤

ጕረሯቸው በውሃ ጥም ደርቋል።

ነገር ግን እኔ እግዚአብሔር እመልስላቸዋለሁ፤

እኔ የእስራኤል አምላክ አልተዋቸውም።

18በተራቈቱ ኰረብቶች ላይ ወንዞችን፣

በሸለቆዎች ውስጥ ምንጮችን አፈልቃለሁ።

ምድረ በዳውን የውሃ ኵሬ፣

የተጠማውን ምድር የውሃ ምንጭ አደርጋለሁ።

19በምድረ በዳ፣

ዝግባን፣ ግራርን፣ ባርሰነትንና ወይራን አበቅላለሁ፤

በበረሓ፣ ጥድን፣ አስታንና

ሸውሸዌን በአንድነት እተክላለሁ።

20ስለዚህ ሰዎች ያያሉ፤ ያውቃሉ፤

የእግዚአብሔር እጅ ይህን እንዳደረገ፣

የእስራኤል ቅዱስ እንደ ፈጠረው፣

በአንድነት ይገነዘባሉ፤ ያስተውላሉም።

21“ሙግታችሁን ይዛችሁ ቅረቡ” ይላል እግዚአብሔር

“ማስረጃችሁን አምጡ” ይላል የያዕቆብ ንጉሥ።

22“የሚሆነውን እንዲነግሩን፣

ጣዖቶቻችሁን አምጡ፤

እንድንገነዘብ፣

ፍጻሜአቸውን እንድናውቅ፣

የቀደሙት ነገሮች ምን እንደ ነበሩ ንገሩን፤

ስለሚመጡትም ነገሮች ግለጹልን።

23እናንት አማልክት መሆናችሁን እናውቅ ዘንድ፣

ወደ ፊት ስለሚሆነው ንገሩን፤

እንድንደነግጥ፣ በፍርሀት እንድንዋጥ፣

መልካምም ሆነ ክፉ፣ አንድ ነገር አድርጉ።

24እነሆ፤ እናንት ከምንም የማትቈጠሩ ናችሁ፤

ሥራችሁ ፈጽሞ ዋጋ ቢስ ነው፤

የመረጣችሁም አስጸያፊ ነው።

25“አንዱን ከሰሜን አስነሣሁት፤ እርሱም ይመጣል፤

ከፀሓይ መውጫ የሚመጣው፣ ስሜን የሚጠራ ነው፤

ሸክላ ሠሪ ዐፈር እንደሚረግጥ፣

አለቆችን እንዲሁ እንደ ጭቃ ይረግጣል።

26እኛ እናውቅ ዘንድ ይህን ከመጀመሪያው የተናገረ፣

‘እርሱ ትክክል ነው’ እንልም ዘንድ ቀድሞ የተናገረ ማነው?

ማንም አልተናገረም፤

ቀደም ብሎ የተናገረ የለም፤

ቃላችሁንም የሰማ የለም።

27በመጀመሪያ፣ ‘እነሆ፤ ተመልከቺአቸው’

ብዬ ለጽዮን የተናገርሁ እኔ ነበርሁ፤

ለኢየሩሳሌምም

የምሥራች ነጋሪን ሰጥቻለሁ።

28ተመለከትሁ ማንም አልነበረም፤

ከመካከላቸው አማካሪ የለም፤

ስጠይቅም መልስ የሚሰጥ የለም።

29እነሆ፤ ሁሉም ከንቱ ናቸው፤

ሥራቸውም መና ነው፤

ምስሎቻቸውም ባዶ ነፋስ ናቸው።

New International Version – UK

Isaiah 41:1-29

The helper of Israel

1‘Be silent before me, you islands!

Let the nations renew their strength!

Let them come forward and speak;

let us meet together at the place of judgment.

2‘Who has stirred up one from the east,

calling him in righteousness to his service41:2 Or east, / whom victory meets at every step?

He hands nations over to him

and subdues kings before him.

He turns them to dust with his sword,

to wind-blown chaff with his bow.

3He pursues them and moves on unscathed,

by a path his feet have not travelled before.

4Who has done this and carried it through,

calling forth the generations from the beginning?

I, the Lord – with the first of them

and with the last – I am he.’

5The islands have seen it and fear;

the ends of the earth tremble.

They approach and come forward;

6they help each other

and say to their companions, ‘Be strong!’

7The metalworker encourages the goldsmith,

and the one who smooths with the hammer

spurs on the one who strikes the anvil.

One says of the welding, ‘It is good.’

The other nails down the idol so that it will not topple.

8‘But you, Israel, my servant,

Jacob, whom I have chosen,

you descendants of Abraham my friend,

9I took you from the ends of the earth,

from its farthest corners I called you.

I said, “You are my servant”;

I have chosen you and have not rejected you.

10So do not fear, for I am with you;

do not be dismayed, for I am your God.

I will strengthen you and help you;

I will uphold you with my righteous right hand.

11‘All who rage against you

will surely be ashamed and disgraced;

those who oppose you

will be as nothing and perish.

12Though you search for your enemies,

you will not find them.

Those who wage war against you

will be as nothing at all.

13For I am the Lord your God

who takes hold of your right hand

and says to you, Do not fear;

I will help you.

14Do not be afraid, you worm Jacob,

little Israel, do not fear,

for I myself will help you,’ declares the Lord,

your Redeemer, the Holy One of Israel.

15‘See, I will make you into a threshing-sledge,

new and sharp, with many teeth.

You will thresh the mountains and crush them,

and reduce the hills to chaff.

16You will winnow them, the wind will pick them up,

and a gale will blow them away.

But you will rejoice in the Lord

and glory in the Holy One of Israel.

17‘The poor and needy search for water,

but there is none;

their tongues are parched with thirst.

But I the Lord will answer them;

I, the God of Israel, will not forsake them.

18I will make rivers flow on barren heights,

and springs within the valleys.

I will turn the desert into pools of water,

and the parched ground into springs.

19I will put in the desert

the cedar and the acacia, the myrtle and the olive.

I will set junipers in the wasteland,

the fir and the cypress together,

20so that people may see and know,

may consider and understand,

that the hand of the Lord has done this,

that the Holy One of Israel has created it.

21‘Present your case,’

says the Lord.

‘Set forth your arguments,’

says Jacob’s King.

22‘Tell us, you idols,

what is going to happen.

Tell us what the former things were,

so that we may consider them

and know their final outcome.

Or declare to us the things to come,

23tell us what the future holds,

so that we may know you are gods.

Do something, whether good or bad,

so that we will be dismayed and filled with fear.

24But you are less than nothing

and your works are utterly worthless;

whoever chooses you is detestable.

25‘I have stirred up one from the north, and he comes –

one from the rising sun who calls on my name.

He treads on rulers as if they were mortar,

as if he were a potter treading the clay.

26Who told of this from the beginning, so that we could know,

or beforehand, so that we could say, “He was right”?

No-one told of this,

no-one foretold it,

no-one heard any words from you.

27I was the first to tell Zion, “Look, here they are!”

I gave to Jerusalem a messenger of good news.

28I look but there is no-one –

no-one among the gods to give counsel,

no-one to give answer when I ask them.

29See, they are all false!

Their deeds amount to nothing;

their images are but wind and confusion.