ኢሳይያስ 40 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 40:1-31

የእግዚአብሔርን ሕዝብ የሚያጽናና ቃል

1አጽናኑ፤ ሕዝቤን አጽናኑ፤

ይላል አምላካችሁ።

2ለኢየሩሳሌም አለዝባችሁ ንገሯት፤

ዐውጁላትም፤

በባርነት ያገለገለችበት ዘመን አብቅቷል፤

የኀጢአቷም ዋጋ ተከፍሏል፤

ስለ ኀጢአቷ ሁሉ ከእግዚአብሔር እጅ

ሁለት ዕጥፍ ተቀብላለች።

3የዐዋጅ ነጋሪ ድምፅ እንዲህ ይላል፤

የእግዚአብሔርን መንገድ፣

በምድረ በዳ አዘጋጁ፤

ለአምላካችን አውራ ጐዳና፣

በበረሓ አስተካክሉ።

4ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፤

ተራራውና ኰረብታው ሁሉ ዝቅ ይላል፤

ወጣ ገባው ምድር ይስተካከላል፤

ሰርጓጕጡም ሜዳ ይሆናል።

5የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፤

ሰው ሁሉ በአንድነት ያየዋል፤

የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና።”

6ድምፅም፣ “ጩኽ” አለኝ፤

እኔም፣ “ምን ብዬ ልጩኽ?” አልሁ።

“ሰው ሁሉ እንደ ሣር ነው፤

ክብሩም ሁሉ እንደ ሜዳ አበባ ነው።

7ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤

የእግዚአብሔር እስትንፋስ ነፍሶበታልና፤

ሕዝቡ በርግጥ ሣር ነው።

8ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤

የአምላካችን ቃል ግን ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”

9አንተ ለጽዮን የምሥራችን የምትነግር፤

ከፍ ወዳለው ተራራ ውጣ፤

አንተ ለኢየሩሳሌም ብሥራት የምትነግር፣40፥9 ወይም፣ ጽዮን ሆይ፤ የምሥራቹን የምታበሥሪ፣ ወደ ረዥም ተራራ ላይ ውጪ ወይም የምሥራቹን የምታበሥሪ ኢየሩሳሌም ሆይ

ድምፅህን ከፍ አድርገህ ጩኽ።

ከፍ አድርገው፤ አትፍራ፤

ለይሁዳም ከተሞች፣

“እነሆ፤ አምላካችሁ!” በል።

10እነሆ፤ጌታ እግዚአብሔር በኀይል

ይመጣል፤

ክንዱ ስለ እርሱ ይገዛል።

እነሆ፤ ዋጋው ከእርሱ ጋር ነው፤

የሚከፍለውም ብድራት አብሮት አለ።

11መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፤

ጠቦቶቹን በክንዱ ይሰበስባል፤

በዕቅፉም ይይዛቸዋል፤

የሚያጠቡትንም በጥንቃቄ ይመራል።

12ውሆችን በዕፍኙ የሰፈረ፣

ሰማያትን በስንዝሩ የለካ፣

የምድርን ዐፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፣

ተራሮችን በሚዛን፣

ኰረብቶችንም በመድሎት የመዘነ ማነው?

13የእግዚአብሔርን መንፈስ የተረዳ፣

አማካሪውስ ሆኖ ያስተማረው ማነው?

14ዕውቀት ለማግኘት እግዚአብሔር ማንን አማከረ?

ትክክለኛውንስ መንገድ ማን አስተማረው?

ዕውቀትን ያስተማረው፣

የማስተዋልንም መንገድ ያሳየው ማን ነበር?

15እነሆ፤ አሕዛብ በገንቦ ውስጥ እንዳለች ጠብታ ናቸው፤

በሚዛን ላይ እንዳለ ትቢያ ይቈጠራሉ፤

ደሴቶችንም እንደ ደቃቅ ዐፈር ይመዝናቸዋል።

16ሊባኖስ ለመሠዊያ እሳት አትበቃም፤

የእንስሶቿም ቍጥር ለሚቃጠል መሥዋዕት ያንሳል።

17አሕዛብ ሁሉ በፊቱ እንደ ኢምንት ናቸው፤

ከምንም የማይቈጠሩ መና ናቸው።

18እንግዲህ፣ እግዚአብሔርን ከማን ጋር ታወዳድሩታላችሁ?

ከየትኛውስ ምስል ጋር ታነጻጽሩታላችሁ?

19የተቀረጸውንማ ምስል ባለ እጅ ይቀርጸዋል፤

ወርቅ አንጥረኛም በወርቅ ይለብጠዋል፤

የብር ሰንሰለትም ያበጅለታል።

20እንዲህ ያለውን መባ ማቅረብ የማይችል ምስኪን ድኻ፣

የማይነቅዝ ዕንጨት ይመርጣል፤

የማይወድቅ ምስልን ለማቆምም፣

ታዋቂ ባለሙያ ይፈልጋል።

21አላወቃችሁምን?

አልሰማችሁምን?

ከጥንት አልተነገራችሁምን?

ምድር ከተመሠረተች ጀምሮ አላስተዋላችሁምን?

22እርሱ ከምድር ክበብ በላይ በዙፋን ላይ ይቀመጣል፤

ሕዝቦቿም እንደ አንበጣ ናቸው።

ሰማያትን እንደ ድባብ ይዘረጋቸዋል፤

እንደ መኖሪያ ድንኳንም ይተክላቸዋል።

23አለቆችን ኢምንት፣

የዚህን ዓለም ገዦች እንዳልነበሩ ያደርጋቸዋል።

24ተተክለው ምንም ያህል ሳይቈዩ፣

ተዘርተው ምንም ያህል ሳይሰነብቱ፣

ገና ሥር መስደድ ሳይጀምሩ

አነፈሰባቸው፤ እነርሱም ደረቁ፤

ዐውሎ ነፋስም እንደ ገለባ ጠራርጎ ወሰዳቸው።

25ቅዱሱ፣ “ከማን ጋር ታወዳድሩኛላችሁ?

የሚስተካከለኝስ ማን አለ?” ይላል።

26ዐይናችሁን አንሡ፤ ወደ ሰማይ ተመልከቱ፤

እነዚህን ሁሉ የፈጠረ ማን ነው?

የከዋክብትን ሰራዊት አንድ በአንድ የሚያወጣቸው፣

በየስማቸው የሚጠራቸው እርሱ ነው።

ከኀይሉ ታላቅነትና ከችሎታው ብርታት የተነሣ፣

አንዳቸውም አይጠፉም።

27ያዕቆብ ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትላለህ?

እስራኤል ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትናገራለህ?

“መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች፤

ፍርዴም በአምላኬ ቸል ተብላለች” ለምን ትላለህ?

28አታውቅምን?

አልሰማህምን?

እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፣

የምድር ዳርቻ ፈጣሪ ነው።

አይደክምም፤ አይታክትም፤

ማስተዋሉም በማንም አይመረመርም።

29ለደከመው ብርታት ይሰጣል፤

ለዛለው ጕልበት ይጨምራል።

30ወጣቶች እንኳ ይደክማሉ፤ ይታክታሉም፤

ጐበዛዝትም ተሰናክለው ይወድቃሉ።

31እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን፣

ኀይላቸውን ያድሳሉ፤

እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤

ይሮጣሉ፤ አይታክቱም፤

ይሄዳሉ፤ አይደክሙም።

New International Version – UK

Isaiah 40:1-31

Comfort for God’s people

1Comfort, comfort my people,

says your God.

2Speak tenderly to Jerusalem,

and proclaim to her

that her hard service has been completed,

that her sin has been paid for,

that she has received from the Lord’s hand

double for all her sins.

3A voice of one calling:

‘In the wilderness prepare

the way for the Lord40:3 Or A voice of one calling in the wilderness: / ‘Prepare the way for the Lord;

make straight in the desert

a highway for our God.40:3 Hebrew; Septuagint make straight the paths of our God

4Every valley shall be raised up,

every mountain and hill made low;

the rough ground shall become level,

the rugged places a plain.

5And the glory of the Lord will be revealed,

and all people will see it together.

For the mouth of the Lord has spoken.’

6A voice says, ‘Cry out.’

And I said, ‘What shall I cry?’

‘All people are like grass,

and all their faithfulness is like the flowers of the field.

7The grass withers and the flowers fall,

because the breath of the Lord blows on them.

Surely the people are grass.

8The grass withers and the flowers fall,

but the word of our God endures for ever.’

9You who bring good news to Zion,

go up on a high mountain.

You who bring good news to Jerusalem,40:9 Or Zion, bringer of good news, / go up on a high mountain. / Jerusalem, bringer of good news

lift up your voice with a shout,

lift it up, do not be afraid;

say to the towns of Judah,

‘Here is your God!’

10See, the Sovereign Lord comes with power,

and he rules with a mighty arm.

See, his reward is with him,

and his recompense accompanies him.

11He tends his flock like a shepherd:

he gathers the lambs in his arms

and carries them close to his heart;

he gently leads those that have young.

12Who has measured the waters in the hollow of his hand,

or with the breadth of his hand marked off the heavens?

Who has held the dust of the earth in a basket,

or weighed the mountains on the scales

and the hills in a balance?

13Who can fathom the Spirit40:13 Or mind of the Lord,

or instruct the Lord as his counsellor?

14Whom did the Lord consult to enlighten him,

and who taught him the right way?

Who was it that taught him knowledge,

or showed him the path of understanding?

15Surely the nations are like a drop in a bucket;

they are regarded as dust on the scales;

he weighs the islands as though they were fine dust.

16Lebanon is not sufficient for altar fires,

nor its animals enough for burnt offerings.

17Before him all the nations are as nothing;

they are regarded by him as worthless

and less than nothing.

18With whom, then, will you compare God?

To what image will you liken him?

19As for an idol, a metalworker casts it,

and a goldsmith overlays it with gold

and fashions silver chains for it.

20A person too poor to present such an offering

selects wood that will not rot;

they look for a skilled worker

to set up an idol that will not topple.

21Do you not know?

Have you not heard?

Has it not been told you from the beginning?

Have you not understood since the earth was founded?

22He sits enthroned above the circle of the earth,

and its people are like grasshoppers.

He stretches out the heavens like a canopy,

and spreads them out like a tent to live in.

23He brings princes to naught

and reduces the rulers of this world to nothing.

24No sooner are they planted,

no sooner are they sown,

no sooner do they take root in the ground,

than he blows on them and they wither,

and a whirlwind sweeps them away like chaff.

25‘To whom will you compare me?

Or who is my equal?’ says the Holy One.

26Lift up your eyes and look to the heavens:

who created all these?

He who brings out the starry host one by one

and calls forth each of them by name.

Because of his great power and mighty strength,

not one of them is missing.

27Why do you complain, Jacob?

Why do you say, Israel,

‘My way is hidden from the Lord;

my cause is disregarded by my God’?

28Do you not know?

Have you not heard?

The Lord is the everlasting God,

the Creator of the ends of the earth.

He will not grow tired or weary,

and his understanding no-one can fathom.

29He gives strength to the weary

and increases the power of the weak.

30Even youths grow tired and weary,

and young men stumble and fall;

31but those who hope in the Lord

will renew their strength.

They will soar on wings like eagles;

they will run and not grow weary,

they will walk and not be faint.