ኢሳይያስ 39 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 39:1-8

ከባቢሎን የመጡ መልእክተኞች

1በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ፣ የባልዳን ልጅ፣ መሮዳክ ባልዳን የሕዝቅያስን መታመምና መፈወስ ሰምቶ ስለ ነበር፣ ደብዳቤና ስጦታ ላከለት። 2ሕዝቅያስም መልእክተኞቹን በደስታ ተቀበለ፤ ለእነርሱም በግምጃ ቤቱ ውስጥ ያለውን ብሩን፣ ወርቁን፣ ቅመማ ቅመሙን፣ ምርጡን ዘይት እንዲሁም የጦር መሣሪያውን በሙሉ፣ ያለውንም ንብረት አንዳች ሳያስቀር አሳያቸው። በቤተ መንግሥቱም ሆነ በግዛቱ ሁሉ ሕዝቅያስ ያላሳያቸው ነገር አልነበረም።

3ከዚያም ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ንጉሡ ሕዝቅያስ መጥቶ፣ “እነዚያ ሰዎች ምን አሉህ? ወደ አንተ ዘንድ የመጡትስ ከየት ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “ወደ እኔ የመጡት ከሩቅ አገር፣ ከባቢሎን ነው” አለው።

4ነቢዩም፣ “በቤተ መንግሥትህ ያዩት ምንድን ነው?” አለው።

ሕዝቅያስም፣ “በቤተ መንግሥቴ ያለውን ሁሉ አይተዋል፤ ከንብረቴ ያላሳየኋቸው ምንም ነገር የለም” አለ።

5ኢሳይያስም ሕዝቅያስን እንዲህ አለው፤ “የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ 6እነሆ፤ በቤተ መንግሥትህ ያለው ሁሉ፣ አባቶችህ እስከዚህች ቀን ድረስ ያከማቹትም ሁሉ ወደ ባቢሎን ተማርኮ የሚወሰድበት ቀን ይመጣል፤ አንዳች የሚተርፍ ነገር የለም፤ ይላል እግዚአብሔር7ከአብራክህ ከሚከፈሉት፣ ከዘርህ፣ ከአንተ ከሚወለዱት ልጆች ተወስደው፣ በባቢሎን ንጉሥ ቤተ መንግሥት ጃንደረባዎች ይሆናሉ።”

8ሕዝቅያስም፣ “የተናገርኸው የእግዚአብሔር ቃል መልካም ነው” አለው፤ “በዘመኔ ሰላምና ጸጥታ ከኖረ ዘንድ” ብሎ ዐስቦ ነበርና።

Persian Contemporary Bible

اشعيا 39:1-8

فرستادگان بابلی

1در آن روزها «مردوک بلدان» (پسر «بلدان») پادشاه بابل، نامه‌ای همراه با هديه‌ای برای حزقيا فرستاد، زيرا شنيده بود كه پس از يک بيماری سخت اينک بهبود يافته است. 2حزقيا فرستادگان بابلی را به خوشی پذيرفت و آنان را به كاخ سلطنتی برد و تمام خزانه‌های طلا و نقره، عطريات و روغنهای معطر، و نيز اسلحه‌خانهٔ خود را به ايشان نشان داد. بدين ترتيب، فرستادگان بابلی تمام خزاين او را ديدند و چيزی از نظر آنان پوشيده نماند.

3آنگاه اشعيای نبی نزد حزقيای پادشاه رفت و از او پرسيد: «اين مردان از كجا آمده بودند و چه می‌خواستند؟»

حزقيا جواب داد: «از جای دور! آنها از بابل آمده بودند.»

4اشعيا پرسيد: «در كاخ تو چه ديدند؟»

حزقيا جواب داد: «تمام خزاين مرا.»

5اشعيا به او گفت: «پس به اين پيام كه از سوی خداوند قادر متعال است گوش كن:

6«زمانی می‌رسد كه هر چه در كاخ داری و گنجهايی كه اجدادت اندوخته‌اند به بابل برده خواهد شد و چيزی از آنها باقی نخواهد ماند. 7بابلی‌ها برخی از پسرانت را به اسارت گرفته، آنان را خواجه خواهند كرد و در كاخ پادشاه بابل به خدمت خواهند گماشت.»

8حزقيا جواب داد: «آنچه خداوند فرموده، نيكوست. لااقل تا وقتی كه زنده‌ام اين اتفاق نخواهد افتاد و صلح و امنيت برقرار خواهد بود.»