ኢሳይያስ 24 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 24:1-23

እግዚአብሔር ምድርን ፈጽሞ ያጠፋታል

1እነሆ፤ እግዚአብሔር ምድርን ባድማ ያደርጋታል፤

ፈጽሞ ያጠፋታል፤

የፍርስራሽ ክምር ያደርጋታል፤

ነዋሪዎቿንም ይበትናል።

2ነገሩ ሁሉ አንድ ዐይነት ይሆናል፤

በሕዝቡ ላይ የሚሆነው በካህኑ፣

በአገልጋዩ ላይ የሚሆነው በጌታው፣

በአገልጋይዋ ላይ የሚሆነው በእመቤቷ፣

በገዥው ላይ የሚሆነው በሻጩ፣

በተበዳሪው ላይ የሚሆነው በአበዳሪው፣

በብድር ከፋይ ላይ የሚሆነው በብድር ሰጪው ይሆናል።

3ምድር ፈጽሞ ባድማ ትሆናለች፤

ጨርሶም ትበዘበዛለች፤

እግዚአብሔር ይህን ቃል ተናግሯልና።

4ምድር ትደርቃለች፤ ትረግፋለች፤

ዓለም ትዝላለች፤ ትረግፋለች፤

የምድርም መሳፍንት ይዝላሉ።

5ምድር በሕዝቧ ትረክሳለች፤

ሕግን ጥሰዋል፤

ሥርዐትን ተላልፈዋል፤

ዘላለማዊውንም ኪዳን አፍርሰዋል።

6ስለዚህ ርግማን ምድርን ትበላለች፤

ሕዝቦቿም ስለ በደላቸው ይቀጣሉ፤

ስለዚህ የምድር ነዋሪዎች ተቃጥለዋል፤

በጣም ጥቂት የሆኑት ቀርተዋል።

7አዲሱ የወይን ጠጅ ዐለቀ፤ የወይኑም ተክል ደረቀ፤

ደስተኞችም ሁሉ አቃሰቱ።

8የከበሮ ደስታ ጸጥ አለ፤

የጨፋሪዎች ጩኸት አበቃ፤

ደስ የሚያሰኘውም በገና እረጭ አለ።

9ከእንግዲህ እየዘፈኑ የወይን ጠጅ አይጠጡም፤

መጠጡም ለሚጠጡት ይመርራል።

10የፈራረሰችው ከተማ ባድማ ሆነች፤

የየቤቱም መግቢያ ተዘጋ።

11በየአደባባዩ የወይን ጠጅ ያለህ እያሉ ይጮኻሉ፤

ደስታው ሁሉ ወደ ሐዘን ይለወጣል፤

ሐሤቱም ሁሉ ከምድር ገጽ ጠፍቷል።

12ከተማዪቱ ፈጽማ ፈርሳለች፤

በሮቿም ደቅቀው ወድቀዋል።

13የወይራ ዛፍ ሲመታ፣

የወይንም ዘለላ ሲቈረጥ ቃርሚያ እንደሚቀር ሁሉ፣

በምድሪቱ ላይ፣

በሕዝቦችም ላይ እንዲሁ ይሆናል።

14ድምፃቸውን ከፍ ያደርጋሉ፤ በደስታም ይጮኻሉ፤

ከምዕራብም የእግዚአብሔርን ክብር ያስተጋባሉ።

15ስለዚህ በምሥራቅ ለእግዚአብሔር ክብር ስጡ፤

ከባሕር ደሴቶችም፣

የእስራኤልን አምላክ፣ የእግዚአብሔርን ስም ከፍ ከፍ አድርጉ።

16“ለጻድቁ ክብር ይሁን” የሚል ዝማሬ፣

ከምድር ዳርቻ ሰማን፤

እኔ ግን፣ “ከሳሁ፤ መነመንሁ፤

ወዮልኝ!

ከዳተኞች አሳልፈው ሰጡ፤

ከዳተኞች በክሕደታቸው አሳልፈው ሰጡ” አልሁ።

17በምድር የምትኖር ሕዝብ ሆይ፤

ሽብር፣ ጕድጓድና ወጥመድ ይጠብቁሃል።

18ከሽብር ድምፅ የሚሸሽ፣

ወደ ጕድጓድ ይገባል፤

ከጕድጓድ የወጣም፣

በወጥመድ ይያዛል።

የሰማይ መስኮቶች ተከፍተዋልና፤

የምድርም መሠረት ተናወጠ።

19ምድር ተከፈለች፤

ምድር ተሰነጠቀች፤

ምድር ፈጽማ ተናወጠች።

20ምድር እንደ ሰካራም ዞረባት፤

ነፋስ እንደሚወዘውዘውም ጐጆ ሆነች፣

የዐመፅዋ ሸክም ከባድ ስለሆነ ትወድቃለች፤

እንደ ገናም አትነሣም።

21በዚያ ቀን እግዚአብሔር

በላይ በሰማያት ያሉትን ኀይሎች፣

በታችም በምድር ያሉትን ነገሥታት ይቀጣቸዋል።

22በጕድጓድ ውስጥ እንዳሉ እስረኞች፣

በአንድ ላይ ይታጐራሉ፤

በእስር ቤት ይዘጋባቸዋል24፥22 ወይም፣ ይላቀቃሉ

ከብዙ ቀንም በኋላ ለፍርድ ይቀርባሉ።

23የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም፣

በሽማግሌዎቹም ፊት በክብሩ ይነግሣል፤

ጨረቃ ትሸማቀቃለች፤ ፀሓይም ታፍራለች።

Thai New Contemporary Bible

อิสยาห์ 24:1-23

องค์พระผู้เป็นเจ้า

1ดูเถิด องค์พระผู้เป็นเจ้ากำลังจะทรงทิ้งโลกให้ร้าง

และทำให้มันย่อยยับ

พระองค์จะทรงทำลายพื้นผิวของโลก

ทำให้ผู้อยู่อาศัยกระจัดกระจายไป

2ทุกคนจะเหมือนกันหมด

ไม่ว่าประชาชนหรือปุโรหิต

ไม่ว่านายหรือบ่าว

ไม่ว่านายหญิงหรือสาวใช้

ไม่ว่าผู้ซื้อหรือผู้ขาย

ไม่ว่าเจ้าหนี้หรือลูกหนี้

ไม่ว่าผู้ยืมหรือผู้ให้ยืม

3โลกจะว่างเปล่า

และยับเยินอย่างสิ้นเชิง

องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ตรัสถ้อยคำเหล่านี้

4โลกก็เหือดแห้งและโรยรา

พิภพก็ซบเซาและเหี่ยวเฉา

ผู้สูงศักดิ์ของโลกก็อ่อนระโหย

5โลกนี้สกปรกโสมมเพราะผู้คนที่อยู่ในโลก

พวกเขาไม่เชื่อฟังบทบัญญัติ

ละเมิดกฎเกณฑ์

และฝ่าฝืนพันธสัญญานิรันดร์

6ฉะนั้นคำสาปแช่งจึงล้างผลาญโลก

ชาวพิภพต้องรับโทษความผิดของตน

ฉะนั้นผู้อาศัยอยู่ในโลกจึงถูกเผาผลาญ

และรอดชีวิตอยู่ไม่กี่คน

7เหล้าองุ่นใหม่ก็เหือดแห้ง และเถาองุ่นก็เหี่ยวเฉา

บรรดาผู้ให้ความบันเทิงได้แต่โอดครวญ

8เสียงสนุกสนานร่าเริงของรำมะนาเงียบไป

เสียงบันเทิงยุติลง

เสียงพิณไพเราะก็เงียบไป

9ไม่มีการจิบเหล้าเคล้าเสียงเพลงอีกแล้ว

สุราก็ขมแก่ผู้ดื่ม

10นครอันล่มจมก็เริศร้าง

ทางเข้าบ้านทุกหลังถูกปิดไม่ให้ใครเข้า

11ตามท้องถนน ผู้คนร้องหาเหล้าองุ่น

ความยินดีกลายเป็นความหม่นหมอง

ความรื่นเริงบันเทิงใจถูกกำจัดไปจากโลก

12นครนั้นตกอยู่ในสภาพปรักหักพัง

ประตูเมืองถูกทุบเป็นชิ้นเล็กชิ้นน้อย

13โลกและชนชาติต่างๆ

จะเป็นเช่นนั้น

เหมือนต้นมะกอกที่ถูกฟาด

หรือเหมือนเศษเล็กเศษน้อยที่ยังเหลืออยู่หลังเก็บองุ่น

14คนหยิบมือที่เหลือจะโห่ร้องอย่างชื่นบาน

และจะประกาศพระบารมีขององค์พระผู้เป็นเจ้าจากแถบตะวันตก

15ดังนั้นคนทางตะวันออกจงถวายเกียรติแด่องค์พระผู้เป็นเจ้า

จงเทิดทูนพระนามของพระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอล

บนเกาะต่างๆ ในทะเล

16จากสุดโลกเราได้ยินเพลงขับร้องว่า

“พระเกียรติสิริจงมีแด่องค์ทรงธรรม”

แต่ข้าพเจ้ากล่าวว่า “ข้าพเจ้าหมดแรง ข้าพเจ้าหมดแรง!

วิบัติแก่ข้าพเจ้า!

มีคนคิดคดทรยศ

และก่อการกบฏ!”

17ชาวโลกเอ๋ย

ความสยดสยอง หลุมพราง และกับดักคอยท่านอยู่

18ใครก็ตามที่เตลิดหนีเมื่อได้ยินเสียงสยดสยอง

จะตกลงในหลุมพราง

ใครก็ตามที่ปีนออกมาจากหลุมพราง

จะติดบ่วงแร้ว

ประตูน้ำของสวรรค์ก็เปิดออก

รากฐานของโลกถูกเขย่า

19โลกทลายล่มจม

แตกออกเป็นเสี่ยงๆ

ถูกเขย่าสั่นคลอน

20โลกโซซัดโซเซเหมือนคนเมา

มันพะเยิบพะยาบเหมือนเพิงกลางพายุ

โทษกบฏของโลกหนักหนาสาหัส

จนทำให้มันล้มลงและไม่อาจลุกขึ้นได้อีกเลย

21ในวันนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงลงโทษ

บรรดาอำนาจในฟ้าสวรรค์เบื้องบน

และบรรดากษัตริย์ในโลกเบื้องล่าง

22พวกเขาจะถูกคุมตัวรวมกัน

เหมือนนักโทษที่ถูกขังไว้ในคุกใต้ดิน

พวกเขาจะถูกจองจำไว้

และหลังจากนั้นหลายวันก็ถูกลงโทษ24:22 หรือได้รับการปลดปล่อย

23ดวงจันทร์จะอับแสง ดวงอาทิตย์จะอดสู

เพราะพระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์จะทรงครอบครอง

เหนือภูเขาศิโยนและในเยรูซาเล็ม

และทรงครอบครองด้วยพระเกียรติสิริต่อหน้าเหล่าผู้อาวุโส