ኢሳይያስ 17 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 17:1-14

በደማስቆ ላይ የተነገረ ንግር

1ስለ ደማስቆ የተነገረ ንግር፤

“እነሆ፤ ደማስቆ ከእንግዲህ ከተማነቷ ይቀራል፤

የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች።

2የአሮኤር ከተሞች ባድማ ይሆናሉ፤

የመንጎች መሰማሪያ ይሆናሉ፤

የሚያስፈራቸውም የለም።

3የተመሸገ ከተማ ከኤፍሬም፣

የመንግሥት ሥልጣን ከደማስቆ ይወርዳል፤

የሶርያም ቅሬታ

እንደ እስራኤላውያን ክብር ይሆናል”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

4“በዚያን ቀን የያዕቆብ ክብር ይደበዝዛል፤

የሰውነቱም ውፍረት ይሟሽሻል።

5ዐጫጅ የቆመውን ሰብል ሰብስቦ፣

ዛላውንም በክንዱ እንደሚያጭድ፣

ይህም በራፋይም ሸለቆ

እንደሚለቀም ቃርሚያ ይሆናል።

6ሆኖም የወይራ ዛፍ ሲመታ፣

ሁለት ወይም ሦስት ፍሬ በቅርንጫፍ ራስ ላይ እንደሚቀር፣

አራት ወይም አምስት ፍሬ ችፍግ ባለው ቅርንጫፍ ላይ እንደሚቀር፣

እንዲሁ ጥቂት ቃርሚያ ይተርፋል”

ይላል የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር

7በዚያ ቀን ሰዎች ወደ ፈጣሪያቸው ይመለከታሉ፤

ዐይኖቻቸውም ወደ እስራኤል ቅዱስ ያያሉ።

8በእጃቸውም ወደ ሠሯቸው መሠዊያዎች አይመለከቱም፤

በጣቶቻቸው ላበጇቸው የዕጣን መሠዊያዎች፣

ለአሼራም የአምልኮ ዐምዶች

ክብር አይሰጡም።

9በዚያን ቀን በእስራኤል ልጆች ምክንያት የተተዉት ጠንካራ ከተሞች ጥሻና ውድማ እንደ ሆኑ ሁሉ፣ እነዚህ ሁሉ ባድማ ይሆናሉ።

10አዳኝ አምላክህን ረስተሃል፤

መሸሸጊያ ዐለትህንም አላስታወስህም፤

ስለዚህ ምርጥ ተክል ብትተክልም፣

እንግዳ ዘርንም ብትዘራ፣

11በተከልህበት ቀን እንዲበቅል፣

በዘራህበትም ማግስት እንዲያብብ ብታደርግ እንኳ፣

መከሩ በደዌና በማይሽር ሕመም ቀን፣

እንዳልነበረ ይሆናል።

12አቤት፤ የብዙ ሕዝቦች የቍጣ ድምፅ

እንደ ባሕር ሞገድ ይጮኻል!

አቤት፤ የሰዎች ከፍተኛ ጩኸት

እንደ ኀይለኛ ውሃ ያስገመግማል!

13ሰዎቹ እንደ ኀይለኛ ውሃ ጩኸት ቢያስገመግሙም፣

እርሱ ሲገሥጻቸው፣

በኰረብታ ላይ በነፋስ እንደሚበንን ትቢያ፣

በዐውሎ ነፋስ ፊት እንደሚበተን ገለባ ይበተናሉ።

14እነሆ፤ ሲመሽ ድንገተኛ ሽብር ሆነ!

ከመንጋቱ በፊት ግን አንዳቸውም አልተገኙም።

የዘረፉን ዕድል ፈንታ፣

የበዘበዙን ዕጣ ይህ ሆነ።

New International Version

Isaiah 17:1-14

A Prophecy Against Damascus

1A prophecy against Damascus:

“See, Damascus will no longer be a city

but will become a heap of ruins.

2The cities of Aroer will be deserted

and left to flocks, which will lie down,

with no one to make them afraid.

3The fortified city will disappear from Ephraim,

and royal power from Damascus;

the remnant of Aram will be

like the glory of the Israelites,”

declares the Lord Almighty.

4“In that day the glory of Jacob will fade;

the fat of his body will waste away.

5It will be as when reapers harvest the standing grain,

gathering the grain in their arms—

as when someone gleans heads of grain

in the Valley of Rephaim.

6Yet some gleanings will remain,

as when an olive tree is beaten,

leaving two or three olives on the topmost branches,

four or five on the fruitful boughs,”

declares the Lord, the God of Israel.

7In that day people will look to their Maker

and turn their eyes to the Holy One of Israel.

8They will not look to the altars,

the work of their hands,

and they will have no regard for the Asherah poles17:8 That is, wooden symbols of the goddess Asherah

and the incense altars their fingers have made.

9In that day their strong cities, which they left because of the Israelites, will be like places abandoned to thickets and undergrowth. And all will be desolation.

10You have forgotten God your Savior;

you have not remembered the Rock, your fortress.

Therefore, though you set out the finest plants

and plant imported vines,

11though on the day you set them out, you make them grow,

and on the morning when you plant them, you bring them to bud,

yet the harvest will be as nothing

in the day of disease and incurable pain.

12Woe to the many nations that rage—

they rage like the raging sea!

Woe to the peoples who roar—

they roar like the roaring of great waters!

13Although the peoples roar like the roar of surging waters,

when he rebukes them they flee far away,

driven before the wind like chaff on the hills,

like tumbleweed before a gale.

14In the evening, sudden terror!

Before the morning, they are gone!

This is the portion of those who loot us,

the lot of those who plunder us.