አሞጽ 4 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 4:1-13

እስራኤል ወደ እግዚአብሔር አልተመለሰም

1እናንተ በሰማርያ ተራራ የምትኖሩ የባሳን ላሞች፤

ድኾችን የምትጨቍኑና ችግረኞችን የምታስጨንቁ፣

ባሎቻችሁንም፣ “መጠጥ አቅርቡልን”

የምትሉ ሴቶች ይህን ቃል ስሙ፤

2ጌታ እግዚአብሔር በቅድስናው እንዲህ ሲል ምሏል፤

“እነሆ፤ በመንጠቆ ተይዛችሁ የምትወሰዱበት

ትሩፋናችሁ እንኳ፣ በዓሣ መንጠቆ

የሚወሰድበት ጊዜ ይመጣል።

3እያንዳንዳችሁ በቅጥሩ በተነደለው መሽሎኪያ

ወደ ሬማንም4፥3 በተለያዩ የዕብራይስጥ ቃላት የተከፈለው የመጀመሪያው የዕብራይስጥ ቅጅ (የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ይመ) የጭቈና ተራራ ሆይ ራቅ ይላል። ትጣላላችሁ፤”

ይላል እግዚአብሔር

4“ወደ ቤቴል ሂዱና ኀጢአትን ሥሩ፤

ወደ ጌልገላም ሂዱና ኀጢአትን አብዙ፤

በየማለዳው መሥዋዕቶቻችሁን፣

በየሦስቱ4፥4 በየሦስቱ ቀናት ዐሥራታችሁን የሚሉ አሉ። ዓመት ዐሥራታችሁን አቅርቡ።

5እርሾ ያለበትን እንጀራ የምስጋና

መሥዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡ፤

በፈቃዳችሁም በምታቀርቡት ቍርባን ተመኩ፤

እናንት እስራኤላውያን በእነርሱም ተኵራሩ፤ ማድረግ የምትወድዱት ይህን ነውና፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

6“በየከተማው ሆዳችሁን4፥6 ዕብራይስጡ ጥርሳችሁን አጠራለሁ ይላል። ባዶ አደረግሁት፤

በየመንደሩም የምትበሉትን

አሳጣኋችሁ፤ እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም”

ይላል እግዚአብሔር

7“መከር ሊደርስ ሦስት ወር ሲቀረውም፣

ዝናብ ከለከልኋችሁ፤

በአንዱ ከተማ ላይ አዘነብሁ፤

በሌላው ላይ ግን እንዳይዘንብ

አደረግሁ፤ አንዱ ዕርሻ ሲዘንብለት፣

ሌላው ዝናብ ዐጥቶ ደረቀ።

8ሰዎች ውሃ ፍለጋ ከከተማ ወደ ከተማ ባዘኑ፣

ይሁን እንጂ ጠጥተው አልረኩም፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

9“የአትክልትና የወይን ቦታዎቻችሁን ብዙ ጊዜ መታሁ፤

በዋግና በአረማሞም አጠፋኋቸው፤

አንበጦችም የበለስና የወይራ ዛፎቻችሁን በሉ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

10“በግብፅ ላይ እንዳደረግሁት፣

መቅሠፍትን ላክሁባችሁ፤

ከተማረኩት ፈረሶቻችሁ ጋር፣

ጕልማሶቻችሁን በሰይፍ ገደልሁ፤

የሰፈራችሁ ግማት አፍንጫችሁ እንዲገባ አደረግሁ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም”

ይላል እግዚአብሔር

11“ሰዶምንና ገሞራን እንደ ገለበጥኋቸው፣

አንዳንዶቻችሁን ገለበጥሁ፤

ከእሳት እንደ ተነጠቀ ትንታግ ሆናችሁ፤

እናንተ ግን ወደ እኔ4፥11 ዕብራይስጡ አምላክ ይላል። አልተመለሳችሁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

12“ስለዚህ እስራኤል ሆይ፤ እንደዚህ አደርግብሃለሁ፤

እንደዚህም ስለማደርግብህ፣ እስራኤል ሆይ፤

አምላክህን ለመገናኘት ተዘጋጅ።”

13ተራሮችን የሚሠራ፣

ነፋስን የሚፈጥር፣

ሐሳቡንም ለሰው የሚገልጥ፣

ንጋትን ጨለማ የሚያደርግ፣

የምድርንም ከፍታዎች የሚረግጥ፣

ስሙ የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ነው።

Japanese Contemporary Bible

アモス書 4:1-13

4

神に立ち返らないイスラエル

1私の言うことを聞きなさい、

サマリヤに住むバシャンの太った雌牛たち。

夫をけしかけて貧しい人から取り上げ、

困っている者からしぼり取っている女たち。

いくら飲んでも十分でない者たちよ。

2あなたがたの鼻に鼻輪をつけて、

牛のように引いて行く時がくると

神である主は、ご自分のきよさにかけて誓いました。

最後の一人まで、

釣り鉤にかけられて引かれて行きます。

3美しい家から引きずり出され、

城壁の破れ口から放り出されます。

主がそう言ったのです。

4ベテルとギルガルの偶像に

もっといけにえをささげなさい。

いつまでも逆らい続けなさい。

あなたがたの罪は山のように積まれていきます。

いけにえは毎朝、

十分の一のささげ物は週に二回持ってきなさい。

5すべて適切な方法で行い、特別のささげ物もしなさい。

あなたがたは、そうすることを得意がり、

どこでもそれを自慢しています。

6主はこう言います。

「あなたがたを飢えさせたが、何にもならなかった。

それでも、わたしのもとに帰ろうとはしなかった。

7収穫の前に三か月間雨を降らせないで

作物をだめにした。

ある町には雨を降らせたが、

他の町には降らせなかった。

ある畑には雨が降っているのに、

他の畑は乾ききっていた。

8二、三の町の住民が飲み水を求めて、

雨の降った町へ疲れきった体で出かけて行った。

それでも満ち足りることはなかった。

そんなことがあっても、

あなたがたはわたしのもとへ帰ろうとしなかった」

と主は言います。

9主はこう告げます。

「立ち枯れ病と黒穂病を、農場やぶどう畑ではやらせた。

いなごがいちじくとオリーブの木を食った。

それでもあなたがたは、

わたしのもとへ帰ろうとしなかった。

10昔のエジプトのように、わたしは疫病を送った。

戦争で若者を殺し、馬を追い払った。

死体からの悪臭が鼻をついた。

それでもあなたがたは、帰ることを拒んだ。

11わたしはソドムとゴモラにしたように、

あなたがたの町の幾つかを破壊した。

生き残った者たちは、

火の中から取り出された燃えさしのようだ。

それでも、わたしのもとへ帰ろうとしない。

12それゆえ、話しておいたとおり、

あなたがたをもっとひどい災いに会わせる。

イスラエルよ、

さばきの中で神に会う備えをせよ。」

13山々を造り、風を造り、あなたがたの思いを

全部知っている方と向かい合うことになるからだ。

その方は、朝を暗闇に変え、山を踏み砕く。

その名は、全能の神、主である。