አሞጽ 3 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 3:1-15

በእስራኤል ላይ የተጠሩ ምስክሮች

1የእስራኤል ልጆች ሆይ፤ እግዚአብሔር በእናንተ ከግብፅ ባወጣሁት ሕዝብ ሁሉ ላይ የተናገረውን ይህን ቃል ስሙ፤

2“ከምድር ወገን ሁሉ፣

እናንተን ብቻ መረጥሁ፤

ስለዚህ ስለ ሠራችሁት ኀጢአት ሁሉ፣

እኔ እቀጣችኋለሁ።”

3በውኑ ሁለት ሰዎች ሳይስማሙ፣

አብረው መጓዝ ይችላሉን?

4አንበሳ የሚበላውን ሳያገኝ፣

በጫካ ውስጥ ይጮኻልን?

ምንም ነገርስ ሳይዝ፣

በዋሻው ውስጥ ያገሣልን?

5ወጥመድ ሳይዘረጋ፣

ወፍ በምድር ላይ ይጠመዳልን?

የሚይዘው ነገር ሳይኖርስ፣

ወጥመዱ ከምድር ይፈነጠራልን?

6የመለከት ድምፅ በከተማ ውስጥ ሲሰማ፣

ሰዎች አይደነግጡምን?

ጥፋትስ በከተማ ላይ ቢደርስ፣

ያደረገው እግዚአብሔር አይደለምን?

7በእውነት ጌታ እግዚአብሔር ምስጢሩን

ለአገልጋዮቹ ለነቢያት ሳይገልጥ፣

ምንም ነገር አያደርግም።

8አንበሳ አገሣ፤

የማይፈራ ማን ነው?

ጌታ እግዚአብሔር ተናገረ፤

ትንቢት የማይናገር ማን ነው?

9ለአዛጦን ምሽግ፣

ለግብፅም ምሽግ እንዲህ ብላችሁ ዐውጁ፤

“በሰማርያ ተራሮች ላይ ተሰብሰቡ፤

በውስጧ ያለውን ታላቅ ሁከት፣

በሕዝቧም መካከል ያለውን ግፍ እዩ።”

10“ቅሚያንና ዝርፊያን በምሽጋቸው ውስጥ የሚያከማቹ፣

በጎ ነገር ማድረግን አያውቁም፤”

ይላል እግዚአብሔር

11ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ጠላት ምድሪቱን ይወርራል፤

ምሽጎቻችሁን ያፈርሳል፤ ድንኳኖቻችሁን

ይዘርፋል።”

12እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እረኛ ከአንበሳ መንጋጋ፣

ሁለት የእግር ዐጥንት ወይም የጆሮ ቍራጭ እንደሚያድን፣

እንዲሁም በሰማርያ በዐልጋቸው3፥12 በዕብራይስጡ ለዚህ ዐረፍተ ነገር የተሰጠው ትርጕም አይታወቅም ጫፍ ላይ፣

በደማስቆም በምንጣፋቸው ላይ የተቀመጡ፣

እስራኤላውያን ይድናሉ።”

13“ይህን ስሙ፤ በያዕቆብም ቤት ላይ መስክሩ” ይላል ጌታ፣ ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር

14“እስራኤልን ስለ ኀጢአቷ በምቀጣበት ቀን፣

የቤቴልን መሠዊያዎች አፈርሳለሁ፤

የመሠዊያው ቀንዶች ይቈረጣሉ፤

ወደ ምድርም ይወድቃሉ።

15የክረምቱን ቤት፣

ከበጋው ቤት ጋር እመታለሁ፤

በዝኆን ጥርስ ያጌጡ ቤቶችም ይደመሰሳሉ፤

ታላላቅ አዳራሾችም ይፈርሳሉ፤”

ይላል እግዚአብሔር

Japanese Contemporary Bible

アモス書 3:1-15

3

イスラエルのさばきの証人

1聞きなさい。これがあなたがたの運命です。エジプトから連れ出したイスラエルとユダの全家族に、主はこう言います。

2「地上のすべての民の中から、あなたがただけを選んだ。

それだけに、その罪を罰しないわけにはいかない。

3罪がわたしたちの間にあるのに、

どうして肩を並べて歩けるだろうか。

4わたしは理由もなく、

ライオンのようにほえているのではない。

実は、あなたがたを滅ぼす準備をしている。

幼いライオンでも、うなり声を上げるのは、

えさに飛びかかる前だ。

5罠は、踏みつけなければパチンと閉じたりしない。

あなたがたは当然の刑罰を受ける。

6警告の角笛が鳴っている。

聞け。そして恐れよ。

主であるわたしが

あなたがたの地に災いを下そうとしているからだ。

7わたしはいつも、

事が起こる前に預言者をとおして警告する。

今もそうしている。」

8ライオンがうなり声を上げました。

恐れ、わななきなさい。

神である主の宣告が聞こえます。

それを宣言することをことわろうとは思いません。

9「アシュドデとエジプトの指導者たちを

共に呼び寄せて、こう言え。

『さあ、サマリヤの山々に陣取って、

イスラエルの恥ずべき罪悪の現状を見届けよ。』

10わたしの民は、正しいことを行うとはどういうことか

忘れてしまった」

と主は言います。

「彼らの宮殿は、

盗んだり奪い取ったりした物でいっぱいだ。

11それゆえ、敵が来て、彼らは取り囲まれ、

とりでを破壊され、宮殿も略奪される。」

12主は言います。

「羊飼いは羊をライオンから救い出そうとしたが、

間に合わなかった。

ライオンの口から、

二本の足と耳の一部をもぎ取っただけだった。

サマリヤのイスラエル人が

最後に助け出されるときもそうなる。

彼らに残っているのは、

壊れかかった椅子とぼろぼろの枕だけだ。」

13全能の神である主は言います。

「これから言うことをよく聞き、

イスラエルにくまなく告げよ。

14罪を犯したイスラエルを罰するその同じ日に、

ベテルの偶像の祭壇も取り壊す。

祭壇の角は切り取られ、地に落ちる。

15金持ちの美しい家、冬の家と夏の家を破壊し、

象牙の宮殿も破壊する。」