ነህምያ 3 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ነህምያ 3:1-32

የቅጥሩ ሠራተኞች

1ሊቀ ካህናቱ ኤልያሴብና ወንድሞቹ ካህናት ለሥራ ተነሡ፤ የበጎች በር የተባለውንም እንደ ገና ሠሩ። ቀደሱት፤ መዝጊያዎቹንም በየቦታቸው ላይ አቆሙ። መቶ ማማ እስከሚባለው ግንብና ሐናንኤል ማማ ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ሠርተው ቀደሱት፤ 2ቀጥሎ ያለውንም የኢያሪኮ ሰዎች ሠሩ፤ እነርሱ ከሠሩት ቀጥሎ ደግሞ የአምሪ ልጅ ዘኩር ሠራ።

3የዓሣ በሩን የሃስናአ ልጆች ሠሩ፤ እነርሱም ምሰሶዎቹን አቁመው መዝጊያዎቹን፣ መቀርቀሪያዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ።

4የአቆስ ልጅ የኦርዮ ልጅ ሜሪሞት ከዚያ ቀጥሎ ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን የሜሴዜቤል ልጅ የበራክያ ልጅ ሜሱላም መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን የበዓና ልጅ ሳዶቅ መልሶ ሠራ፤ 5የሚቀጥለውን ክፍል የቴቁሐ ሰዎች መልሰው ሠሩ፤ መኳንንቶቻቸው ግን በተቈጣጣሪ አሠሪዎቻቸው3፥5 ጌቶቻቸው፤ ወይም ገዦቻቸው ሥር ሆነው በሥራው መጠመድ አልፈለጉም።

6አሮጌውን3፥6 ወይም የይሻናን በር የፋሴሐ ልጅ ዮዳሄና የበሶድያ ልጅ ሜሱላም መልሰው ሠሩ፤ እነርሱም ምሰሶዎቹን አቁመው መዝጊያዎቹን፣ ማያያዣዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ። 7ከእነርሱም ቀጥሎ የዕድሳቱ ሥራ የተከናወነው በኤፍራጥስ ማዶ በሚገኘው አገረ ገዥ ሥልጣን ሥር ባሉት በገባዖንና በምጽጳ ሰዎች በገባዖናዊው በመልጥያና በሜሮኖታዊው በያዶን ነበር። 8ከወርቅ አንጥረኞች አንዱ የሆነው የሐርሃያ ልጅ ዑዝኤል የሚቀጥለውን ክፍል ሠራ፤ ከሽቱ ቀማሚዎች አንዱ የሆነው ሐናንያ ደግሞ ከዚያ ቀጥሎ ያለውን መልሶ ሠራ። እነርሱም “ሰፊው ቅጥር” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ኢየሩሳሌምን መልሰው ሠሩ። 9ከዚያ የሚቀጥለውን ክፍል የኢየሩሳሌም አውራጃ እኩሌታ ገዥ የሆነው የሆር ልጅ ረፋያ መልሶ ሠራ። 10የኤርማፍ ልጅ ይዳያ ከቤቱ ፊት ለፊት ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ፤ የአሰበንያ ልጅ ሐጡስ ደግሞ ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን መልሶ ሠራ። 11የካሪም ልጅ መልክያና የፈሐት ሞዓብ ልጅ አሱብ ሌላውን ክፍልና “የእቶን ግንብ” ተብሎ የሚጠራውን መልሰው ሠሩ። 12የኢየሩሳሌም አውራጃ እኩሌታ ገዥ የሆነው የአሎኤስ ልጅ ሰሎም ከሴት ልጆቹ ጋር በመሆን ቀጥሎ ያለውን ክፍል መልሶ ሠራ።

13“የሸለቆ በር” ተብሎ የሚጠራውን የሐኖንና የዛኖ ነዋሪዎች ዐደሱት፤ መልሰው ሠሩት፤ ከሠሩትም በኋላ መዝጊያዎቹን በየቦታቸው አኖሩ፤ መወርወሪያዎቹንና መቀርቀሪያዎቹንም አበጁ። እንዲሁም “የቈሻሻ መጣያ በር” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ያለውን አንድ ሺሕ ክንድ3፥13 450 ሜትር ያህል ነው። ቅጥር መልሰው ሠሩ።

14“የቈሻሻ መጣያ በር” ተብሎ የሚጠራው የቤት ሐካሪም አውራጃ ገዥ የሆነው የሬካብ ልጅ መልክያ መልሶ ሠራ፤ መልሶ ከሠራ በኋላም መዝጊያዎቹን፣ መቀርቀሪያዎቹንና መወርወሪያዎቹን በየቦታቸው አኖረ።

15የምጽጳ አውራጃ የኮልሖዜ ልጅ ሰሎም “የምንጭ በር” ተብሎ የሚጠራውን መልሶ ሠራ፤ መልሶ ከሠራም በኋላ ከድኖ መዝጊያዎቹን በየቦታቸው አኖረ፤ መወርወሪያዎቹንና መቀርቀሪያዎቹንም አበጀ። “የንጉሥ አትክልት ቦታ” ተብሎ በሚጠራው አጠገብ የሚገኘውን የሼላን መዋኛ ግንብም፣ ከዳዊት ከተማ ጀምሮ ቍልቍል እስከሚወርደው ደረጃ ድረስ መልሶ ሠራ። 16ከእርሱም በኋላ የቤት ጹር አውራጃ እኩሌታ ገዥ የዓዝቡቅ ልጅ ነህምያ እስከ ዳዊት መቃብር ትይዩ እስከ ሰው ሠራሹ ኵሬና “የጀግኖች ቤት” ተብሎ እስከሚጠራው ድረስ ያለውን መልሶ ሠራ።

17ከእርሱ ቀጥሎ ሌዋውያኑ በባኒ ልጅ በሬሁ ሥር ሆነው የዕድሳት ሥራ ሠሩ። ከእርሱ ቀጥሎ የቅዒላ አውራጃ እኩሌታ ገዥ ሐሸብያ አውራጃውን መልሶ ሠራ። 18ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ክፍል ደግሞ የሌላው የቅዒላ አውራጃ እኩሌታ ገዥ የኤንሐዳድ ልጅ በዋይና በእርሱም ሥር የነበሩት የአገሩ ሰዎች መልሰው ሠሩ። 19ከእርሱም ቀጥሎ ወደ ጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት በሚያወጣውና እስከ ማእዘኑ በሚደርሰው ትይዩ ያለውን ሌላ ክፍል የምጽጳ ገዥ የኢያሱ ልጅ ኤጽር መልሶ ሠራ። 20ከእርሱም ቀጥሎ የዘባይ ልጅ ባሮክ ከማእዘኑ ጀምሮ እስከ ሊቀ ካህኑ እስከ ኤልያሴብ ቤት መግቢያ ያለውን ሌላ ክፍል በትጋት መልሶ ሠራ። 21ከእርሱ ቀጥሎ ከኤልያሴብ ቤት መግቢያ ጀምሮ እስከ መጨረሻው ያለውን ሌላ ክፍል የአቆስ ልጅ የኦርዮ ልጅ ሜሪሞት መልሶ ሠራ።

22ከእርሱም ቀጥሎ ያለውን ክፍል ከአካባቢው የመጡት ካህናት መልሰው ሠሩ። 23ከእነርሱ ቀጥሎ ብንያምና አሱብ ከቤታቸው ፊት ለፊት ያለውን መልሰው ሠሩ፤ ከእነርሱም ቀጥሎ የሐናንያ ልጅ የመዕሤያ ልጅ ዓዛርያስ በቤቱ አጠገብ ያለውን መልሶ ሠራ። 24ከእርሱም ቀጥሎ ከዓዛርያስ ቤት ጀምሮ እስከ ማእዘኑና እስከ ማእዘኑም ጫፍ ያለውን ሌላውን ክፍል የኤንሐደድ ልጅ ቢንዊ መልሶ ሠራ፤ 25የኡዛይ ልጅ ፋላል ከቅጥሩ ማእዘን ትይዩና በዘብ መጠበቂያው አደባባይ አጠገብ ካለው ከላይኛው ቤተ መንግሥት መጠበቂያ ግንብ ጀምሮ ያለውን መልሶ ሠራ። ከእርሱም ቀጥሎ የፋሮስ ልጅ ፈዳያና 26በዖፌል ኰረብታ ላይ የሚኖሩት የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች “የውሃ በር” ተብሎ ከሚጠራው ትይዩ ጀምሮ በስተ ምሥራቅ እስከሚገኘው ግንብ ድረስ መልሰው ሠሩ። 27ከእነርሱ ቀጥሎ የቴቁሐ ሰዎች ከታላቁ ግንብ ትይዩ ጀምሮ እስከ ዖፌል ቅጥር ድረስ ያለውን ሌላ ክፍል መልሰው ሠሩ።

28“የፈረስ በር” ተብሎ ከሚጠራው በላይ ያለውን ደግሞ ካህናቱ እያንዳንዳቸው በየመኖሪያ ቤታቸው ትይዩ ያለውን መልሰው ሠሩ። 29ከእነርሱም ቀጥሎ የኢሜር ልጅ ሳዶቅ በቤቱ ትይዩ ያለውን መልሶ ሠራ። ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን “የምሥራቅ በር” ጠባቂ የሆነው የሴኬንያ ልጅ ሸማያ መልሶ ሠራ። 30ከእርሱ ቀጥሎ ያለውን ሌላ ክፍል ደግሞ የሰሌምያ ልጅ ሐናንያና የሴሌፍ ስድስተኛ ልጅ ሐኖን መልሰው ሠሩ። ከእነርሱም ቀጥሎ የበራክያ ልጅ ሜሱላም ከመኖሪያው ትይዩ ያለውን መልሶ ሠራ። 31ከእርሱ ቀጥሎ ከወርቅ አንጥረኞች አንዱ መልክያ በመቈጣጠሪያው በር ትይዩ እስከሚገኘው እስከ ቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና እስከ ነጋዴዎቹ ቤት፣ እንዲሁም ከማእዘኑ በላይ እስከሚገኘው ክፍል ያለውን መልሶ ሠራ፤ 32ከማእዘኑ በላይ ከሚገኘው ክፍል ጀምሮ እስከ በጎች በር ያለውን ደግሞ ወርቅ አንጥረኞቹና ነጋዴዎቹ መልሰው ሠሩ።

New International Reader’s Version

Nehemiah 3:1-32

A List of the People Who Repaired the Wall

1Eliashib the high priest and the other priests went to work. They rebuilt the Sheep Gate. They set it apart to God. They put its doors in place. They continued to rebuild the wall up to the Tower of the Hundred. They set the tower apart to God. Then they continued to rebuild the wall all the way to the Tower of Hananel. 2Some men from Jericho rebuilt the next part of the wall. And Zakkur rebuilt the next part. He was the son of Imri.

3The sons of Hassenaah rebuilt the Fish Gate. They laid its beams. They put in place its doors with their metal bolts and bars. 4Meremoth repaired the next part of the wall. He was the son of Uriah. Uriah was the son of Hakkoz. Next to Meremoth, Meshullam made some repairs. He was the son of Berekiah. Berekiah was the son of Meshezabel. Next to Meshullam, Zadok also made some repairs. He was the son of Baana. 5Some men from Tekoa repaired the next part of the wall. But their nobles refused to do any work at all. They didn’t pay any attention to the people who were in charge of the work.

6Joiada and Meshullam repaired the Jeshanah Gate. Joiada was the son of Paseah. Meshullam was the son of Besodeiah. Joiada and Meshullam laid the beams of the gate. They put in place its doors with their metal bolts and bars. 7Next to them, some men from Gibeon and Mizpah made repairs. They included Melatiah from Gibeon and Jadon from Meronoth. Those places were under the authority of the governor of the land west of the Euphrates River. 8Uzziel repaired the next part of the wall. He made his living by working with gold. He was the son of Harhaiah. Hananiah made repairs on the next part. He made his living by making perfume. So the wall of Jerusalem was made like new again all the way to the Broad Wall. 9Rephaiah repaired the next part. He was the son of Hur. Rephaiah ruled over half of the territory where Jerusalem was located. 10Jedaiah repaired the part of the wall that was across from his house. He was the son of Harumaph. Hattush made repairs next to Jedaiah. Hattush was the son of Hashabneiah. 11Malkijah and Hasshub repaired another part of the wall. They also repaired the Tower of the Ovens. Malkijah was the son of Harim. Hasshub was the son of Pahath-Moab. 12Shallum repaired the next part. His daughters helped him. He was the son of Hallohesh. Shallum ruled over the other half of the territory where Jerusalem was located.

13Hanun repaired the Valley Gate. Some people who lived in Zanoah helped him. They rebuilt it. They put in place its doors with their metal bolts and bars. They also repaired 1,500 feet of the wall. They repaired it all the way to the Dung Gate.

14Malkijah repaired the Dung Gate. He was the son of Rekab. Malkijah ruled over the territory where Beth Hakkerem was located. He rebuilt the gate. He put in place its doors with their metal bolts and bars.

15Shallun repaired the Fountain Gate. He was the son of Kol-Hozeh. Shallun ruled over the territory where Mizpah was located. He rebuilt the gate. He put a roof over it. And he put in place the doors of the gate with their metal bolts and bars. He also repaired the wall by the Pool of Siloam. It was near the King’s Garden. Shallun repaired the wall as far as the steps that go down from the City of David. 16Next to Shallun, Nehemiah made some repairs. He was the son of Azbuk. Nehemiah ruled over half of the territory where Beth Zur was located. He repaired the wall up to the part that was across from the tombs of David. He repaired it all the way to the man-made pool and the House of the Heroes.

17Next to Nehemiah, some Levites made repairs. They worked under the direction of Rehum. He was the son of Bani. Next to Rehum, Hashabiah made repairs for his territory. He ruled over half of the territory where Keilah was located. 18Next to him, other Levites made some repairs. They worked under the direction of Binnui. He was the son of Henadad. Binnui ruled over the other half of the territory where Keilah was located. 19Next to Binnui, Ezer repaired another part of the wall. He was the son of Jeshua. Ezer ruled over Mizpah. He repaired the part across from the place that went up to the storeroom where the weapons were kept. He repaired the wall up to the angle of the wall. 20Next to Ezer, Baruch worked hard to repair another part of the wall. He was the son of Zabbai. He repaired the part from the angle of the wall to the entrance to Eliashib’s house. Eliashib was the high priest. 21Next to Baruch, Meremoth repaired another part. He was the son of Uriah. Uriah was the son of Hakkoz. Meremoth repaired the part from the entrance to Eliashib’s house to the end of the house.

22Next to Meremoth, some priests from the surrounding area made repairs. 23Next to them, Benjamin and Hasshub repaired the part of the wall that was in front of their house. Next to them, Azariah repaired the part that was beside his house. He was the son of Maaseiah. Maaseiah was the son of Ananiah. 24Next to Azariah, Binnui made repairs on another part. Binnui was the son of Henadad. Binnui repaired the wall from Azariah’s house to the angle and the corner. 25Palal worked across from the angle. He was the son of Uzai. Palal also worked across from the tower that was part of the upper palace. It was near the courtyard of the guard. Next to him, Pedaiah made some repairs. He was the son of Parosh. 26The temple servants who lived on the hill of Ophel helped Pedaiah. They repaired the wall up to the part that was across from the Water Gate. It was toward the east and the palace tower. 27Next to the temple servants, the men from Tekoa repaired another part. They made repairs from the large palace tower to the wall of Ophel.

28The priests made repairs above the Horse Gate. Each priest repaired the part of the wall that was in front of his own house. 29Next to them, Zadok made repairs across from his house. He was the son of Immer. Next to Zadok, Shemaiah made some repairs. He was the son of Shekaniah. Shemaiah guarded the East Gate. 30Next to him, Hananiah and Hanun repaired another part of the wall. Hananiah was the son of Shelemiah. Hanun was the sixth son of Zalaph. Next to Hananiah and Hanun, Meshullam made some repairs. He was the son of Berekiah. Meshullam repaired the part that was across from where he lived. 31Next to him, Malkijah made some repairs. He made his living by working with gold. He repaired the wall up to the house of the temple servants and the traders. It was across from the Inspection Gate. He also repaired the wall as far as the room above the corner. 32The traders and those who made their living by working with gold made some repairs. They repaired the wall from the room above the corner to the Sheep Gate.