ሰቈቃወ 1 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ሰቈቃወ 1:1-22

א አሌፍ

1 ይህ ምዕራፍ ጥቅሶቹ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር፣ የመጀመሪያው ወይም የመጨረሻው መሥመር ትርጕም የሚሰጥ ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር ያለው ግጥም ነው። 1በሕዝብ ተሞልታ የነበረችው ከተማ፣

እንዴት የተተወች ሆና ቀረች!

በሕዝቦች መካከል ታላቅ የነበረችው፣

እርሷ እንዴት እንደ መበለት ሆነች!

በአውራጃዎች መካከል ልዕልት የነበረችው፣

አሁን ባሪያ ሆናለች።

ב ቤት

2በሌሊት አምርራ ታለቅሳለች፤

እንባዋ በጕንጮቿ ላይ ይወርዳል፤

ከወዳጆቿ ሁሉ መካከል፣

የሚያጽናናት ማንም የለም፤

ባልንጀሮቿ ሁሉ ከድተዋታል፤

ጠላቶቿም ሆነዋል።

ג ጊሜል

3በመከራና በመረገጥ ብዛት

ይሁዳ ተማርካ ሄደች፤

በሕዝቦችም መካከል ተቀመጠች፤

የምታርፍበትንም ስፍራ ዐጣች፤

በጭንቀቷ መካከል ሳለች፣

አሳዳጆቿ ሁሉ አገኟት።

ד ዳሌት

4የጽዮን መንገዶች ያለቅሳሉ፤

በዓላቷን ለማክበር የሚመጣ የለምና፤

በበሮቿ ሁሉ የሚገባና የሚወጣ የለም፤

ካህናቷ ይቃትታሉ፤

ደናግሏ ክፉኛ ዐዝነዋል፤

እርሷም በምሬት ትሠቃያለች።

ה ሄ

5ባላጋሮቿ ገዦቿ ሆኑ፤

ጠላቶቿ ተመችቷቸዋል፤

ከኀጢአቷ ብዛት የተነሣ፣

እግዚአብሔር ከባድ ሐዘን አምጥቶባታል።

ልጆቿ በጠላት ፊት ተማርከው፣

ወደ ግዞት ሄደዋል።

ו ዋው

6የጽዮን ሴት ልጅ፣

ግርማ ሞገሷ ሁሉ ተለይቷታል፤

መሳፍንቷ፣

መሰማሪያ እንዳጣ ዋሊያ ናቸው፤

በአሳዳጆቻቸው ፊት፣

በድካም ሸሹ።

ז ዛይን

7በተጨነቀችባቸውና በተንከራተተችባቸው ቀናት፣

ኢየሩሳሌም በጥንት ዘመን የነበራትን፣

ሀብት ሁሉ ታስባለች፤

ሕዝቦቿ በጠላት እጅ በወደቁ ጊዜ፣

የረዳት ማንም አልነበረም፤

ጠላቶቿ ተመለከቷት፤

በመፈራረሷም ሣቁ።

ח ኼት

8ኢየሩሳሌም ከባድ ኀጢአት ሠርታለች፤

ስለዚህም የረከሰች ሆናለች፤

ያከበሯት ሁሉ ናቋት፤

ዕራቍቷን ሆና አይተዋታልና፤

እርሷ ራሷ ታጕረመርማለች፤

ወደ ኋላዋም ዘወር ብላለች።

ט ቴት

9ርኩሰቷ በቀሚሷ ላይ ታየ፤ ወደ ፊት የሚሆንባትን አላሰበችም፤

አወዳደቋ አስደንጋጭ ሆነ፤

የሚያጽናናትም አልነበረም፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መከራዬን

ተመልከት፤

ጠላት ድል አድርጓልና!”

י ዮድ

10ዮድ በሀብቷ ሁሉ ላይ፣

ጠላት እጁን ዘረጋ፤

ወደ ጉባኤህ እንዳይገቡ

የከለከልሃቸው፣

ጣዖት የሚያመልኩ አሕዛብ፣

ወደ መቅደሷ ሲገቡ አየች።

כ ካፍ

11እንጀራ በመፈለግ፣

ሕዝቧ ሁሉ በሥቃይ ይጮኻል፤

በሕይወት ለመኖር፣

የከበረ ሀብታቸውን በምግብ ይለውጣሉ፤

“አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አስበኝ፤ ተመልከተኝም፤

እኔ ተዋርጃለሁና።”

ל ላሜድ

12“እናንት መንገድ ዐላፊዎች ሁሉ፤ ይህ ለእናንተ ምንም አይደለምን?

ተመልከቱ፤ እዩም፤

በጽኑ ቍጣው ቀን፣

እግዚአብሔር ያመጣብኝን፣

በእኔ ላይ የደረሰውን፣

የእኔን መከራ የመሰለ መከራ አለን?

מ ሜም

13“ከከፍታ ስፍራ እሳትን ላከ፤

ወደ ታች ወደ ዐጥንቶቼም ሰደደው፤

በእግሮቼ ላይ መረብ ዘረጋ፤

ወደ ኋላም ጣለኝ፤

ቀኑን ሙሉ በማድከም፣

ባዶ አድርጎ አስቀመጠኝ።

נ ኑን

14“ኀጢአቶቼ ቀንበር ሆኑ፤1፥14 አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ ቅጆች እንዲሁ ሲሆኑ ሰብዓ ሊቃናት ግን ኀጢአቶቼን ያለ ማቋረጥ ይከታተላል ይላል።

በእጆቹ አንድ ላይ ተገመዱ፤

በዐንገቴም ላይ ተጭነዋል፤

ኀይሌንም አዳከመ፤

ልቋቋማቸው ለማልችላቸው፣

እርሱ አሳልፎ ሰጠኝ።

ס ሳሜክ

15“በውስጤ ያሉትን ተዋጊዎች ሁሉ፣

እግዚአብሔር ተቃወመ፤

ጕልማሶቼን ለማድቀቅ፣

ሰራዊት በላዬ ላይ ጠራ1፥15 ወይም …በሚያደቅቅበት ጊዜ፣ ለእኔ ጊዜን ወሰነልኝ።

ድንግሊቱን የይሁዳ ሴት ልጅ፣

እግዚአብሔር በወይን መጭመቂያ ውስጥ ረገጣት።

ע ዐዪን

16“የማለቅሰው ስለ እነዚህ ነገሮች ነው፤

ዐይኖቼ በእንባ ተሞልተዋል፣

ሊያጽናናኝ የቀረበ፣

መንፈሴንም ሊያረጋጋ የሞከረ ማንም የለም፤

ጠላት በርትቷልና

ልጆቼ ተጨንቀዋል።”

פ ፌ

17ጽዮን እጆቿን ዘረጋች፤

የሚያጽናናትም የለም፤

ጎረቤቶቹ ጠላቶቹ እንዲሆኑ፣

እግዚአብሔር በያዕቆብ ላይ ትእዛዝ አውጥቷል፤

ኢየሩሳሌምም በመካከላቸው፣

እንደ ርኩስ ነገር ተቈጠረች።

צ ጻዲ

18እግዚአብሔር ጻድቅ ነው፤

እኔ ግን በትእዛዙ ላይ ዐመፅ አድርጌ ነበር፤

እናንተ ሕዝቦች ሁሉ ስሙ፤

መከራዬንም ተመልከቱ፤

ወይዛዝርቶቼና ጐበዛዝቶቼ፣

ተማርከው ሄደዋል።

ק ቆፍ

19“ወዳጆቼን ጠራኋቸው፤

እነርሱ ግን ከዱኝ፤

ካህናቶቼና ሽማግሌዎቼ፣

ሕይወታቸውን ለማትረፍ፣

ምግብ ሲፈልጉ፣

በከተማዪቱ ውስጥ ዐለቁ።

ר ሬሽ

20“አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንዴት ተጨንቄአለሁ!

በውስጤ ተሠቃይቼአለሁ፤

በልቤ ታውኬአለሁ፤

እጅግ ዐመፀኛ ሆኛለሁና፤

በውጭ ሰይፍ ይፈጃል፤

በቤትም ውስጥ ሞት አለ።

ש ሲን እና ሺን

21“ሰዎች የሥቃይ ልቅሶዬን ሰሙ፤

የሚያጽናናኝ ግን ማንም የለም፤

ጠላቶቼ ሁሉ ጭንቀቴን ሰሙ፤

አንተ ባደረግኸውም ደስ አላቸው፤

አቤቱ የተናገርሃት ቀን ትምጣ፤

እነርሱም እንደ እኔ ይሁኑ።

ת ታው

22“ክፋታቸው ሁሉ በፊትህ ይቅረብ፤

ከኀጢአቴ ሁሉ የተነሣ፣

በእኔ ላይ እንዳደረግህብኝ፣

በእነርሱም ላይ አድርግባቸው፤

የሥቃይ ልቅሶዬ በዝቷል፤

ልቤም ደክሟል።”

New International Version

Lamentations 1:1-22

This chapter is an acrostic poem, the verses of which begin with the successive letters of the Hebrew alphabet. 1How deserted lies the city,

once so full of people!

How like a widow is she,

who once was great among the nations!

She who was queen among the provinces

has now become a slave.

2Bitterly she weeps at night,

tears are on her cheeks.

Among all her lovers

there is no one to comfort her.

All her friends have betrayed her;

they have become her enemies.

3After affliction and harsh labor,

Judah has gone into exile.

She dwells among the nations;

she finds no resting place.

All who pursue her have overtaken her

in the midst of her distress.

4The roads to Zion mourn,

for no one comes to her appointed festivals.

All her gateways are desolate,

her priests groan,

her young women grieve,

and she is in bitter anguish.

5Her foes have become her masters;

her enemies are at ease.

The Lord has brought her grief

because of her many sins.

Her children have gone into exile,

captive before the foe.

6All the splendor has departed

from Daughter Zion.

Her princes are like deer

that find no pasture;

in weakness they have fled

before the pursuer.

7In the days of her affliction and wandering

Jerusalem remembers all the treasures

that were hers in days of old.

When her people fell into enemy hands,

there was no one to help her.

Her enemies looked at her

and laughed at her destruction.

8Jerusalem has sinned greatly

and so has become unclean.

All who honored her despise her,

for they have all seen her naked;

she herself groans

and turns away.

9Her filthiness clung to her skirts;

she did not consider her future.

Her fall was astounding;

there was none to comfort her.

“Look, Lord, on my affliction,

for the enemy has triumphed.”

10The enemy laid hands

on all her treasures;

she saw pagan nations

enter her sanctuary—

those you had forbidden

to enter your assembly.

11All her people groan

as they search for bread;

they barter their treasures for food

to keep themselves alive.

“Look, Lord, and consider,

for I am despised.”

12“Is it nothing to you, all you who pass by?

Look around and see.

Is any suffering like my suffering

that was inflicted on me,

that the Lord brought on me

in the day of his fierce anger?

13“From on high he sent fire,

sent it down into my bones.

He spread a net for my feet

and turned me back.

He made me desolate,

faint all the day long.

14“My sins have been bound into a yoke1:14 Most Hebrew manuscripts; many Hebrew manuscripts and Septuagint He kept watch over my sins;

by his hands they were woven together.

They have been hung on my neck,

and the Lord has sapped my strength.

He has given me into the hands

of those I cannot withstand.

15“The Lord has rejected

all the warriors in my midst;

he has summoned an army against me

to1:15 Or has set a time for me / when he will crush my young men.

In his winepress the Lord has trampled

Virgin Daughter Judah.

16“This is why I weep

and my eyes overflow with tears.

No one is near to comfort me,

no one to restore my spirit.

My children are destitute

because the enemy has prevailed.”

17Zion stretches out her hands,

but there is no one to comfort her.

The Lord has decreed for Jacob

that his neighbors become his foes;

Jerusalem has become

an unclean thing among them.

18“The Lord is righteous,

yet I rebelled against his command.

Listen, all you peoples;

look on my suffering.

My young men and young women

have gone into exile.

19“I called to my allies

but they betrayed me.

My priests and my elders

perished in the city

while they searched for food

to keep themselves alive.

20“See, Lord, how distressed I am!

I am in torment within,

and in my heart I am disturbed,

for I have been most rebellious.

Outside, the sword bereaves;

inside, there is only death.

21“People have heard my groaning,

but there is no one to comfort me.

All my enemies have heard of my distress;

they rejoice at what you have done.

May you bring the day you have announced

so they may become like me.

22“Let all their wickedness come before you;

deal with them

as you have dealt with me

because of all my sins.

My groans are many

and my heart is faint.”