ሮሜ 9 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ሮሜ 9:1-33

የእግዚአብሔር ሉዓላዊ ምርጫ

1በክርስቶስ ሆኜ እውነት እናገራለሁ፤ አልዋሽም፤ ኅሊናዬም በመንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል። 2ታላቅ ሐዘንና የማያቋርጥ ጭንቀት በልቤ አለ። 3ለወገኖቼ ስል ስለ ወንድሞቼ እኔ ራሴ የተረገምሁና ከክርስቶስም ተለይቼ የተጣልሁ እንድሆን እንኳ እወድድ ነበር፤ 4እነርሱም የእስራኤል ሕዝብ ናቸው፤ ልጅ መሆን፣ መለኮታዊ ክብር፣ ኪዳን፣ ሕግን መቀበል፣ የቤተ መቅደስ ሥርዐትና ተስፋ የእነርሱ ናቸውና። 5አባቶችም የእነርሱ ናቸው፤ ክርስቶስም በሥጋ የትውልድ ሐረጉ የሚቈጠረው ከእነርሱ ነው፤ እርሱም፣ ከሁሉ በላይ የሆነ ለዘላለም የተመሰገነ አምላክ ነው፤9፥5 ወይም ከሁሉ በላይ የሆነ ለዘላለም የተመሰገነ አምላክ ይሁን ወይም ከሁሉ በላይ የሆነ አምላክ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን አሜን።

6ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ተሽሯል ማለት አይደለም፤ ከእስራኤል የተወለደ ሁሉ እስራኤላዊ አይደለምና። 7ከአብርሃም ዘርም ስለ ሆኑ፣ ሁሉም ልጆቹ አይደሉም፤ ይልቁንስ፣ “ትውልድህ በይሥሐቅ በኩል ይጠራልሃል” እንደ ተባለው ነው። 8ይህም ማለት የእግዚአብሔር ልጆች የተባሉት የሥጋ ልጆች አይደሉም፤ ነገር ግን የአብርሃም ልጆች የተባሉት የተስፋው ልጆች ናቸው። 9“ጊዜው ሲደርስ እመለሳለሁ፤ ሣራም ወንድ ልጅ ትወልዳለች” ተብሎ ተስፋው ተሰጥቷልና።

10ይህም ብቻ ሳይሆን፣ የርብቃ ልጆች አንድ አባት አላቸው፤ እርሱም አባታችን ይስሐቅ ነው። 11መንትዮቹ ገና ሳይወለዱ፣ ወይም በጎም ሆነ ክፉ ሳያደርጉ፣ የእግዚአብሔር ሐሳብ በምርጫ ይጸና ዘንድ፣ 12በሥራ ሳይሆን ከጠሪው በመሆኑ፣ “ታላቁ ታናሹን ያገለግላል” ተብሎ ተነገራት። 13ይህም፣ “ያዕቆብን ወደድሁ፤ ዔሳውን ግን ጠላሁ” ተብሎ እንደ ተጻፈው ነው።

14እንግዲህ ምን እንላለን? እግዚአብሔር አድልዎ ያደርጋልን? በፍጹም አያደርግም! 15ለሙሴ፣

“የምምረውን እምረዋለሁ፤

ለምራራለትም እራራለታለሁ” ይላልና።

16እንግዲህ ይህ ከሰው ፍላጎት ወይም ጥረት ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው። 17መጽሐፍ ፈርዖንን፣ “ኀይሌ በአንተ እንዲታይ፣ ስሜም በምድር ሁሉ እንዲነገር ለዚህ አስነሣሁህ” ይላልና። 18ስለዚህ እግዚአብሔር ሊምረው ለሚወድደው ምሕረት ያደርግለታል፤ ልቡ እንዲደነድን የፈለገውንም ያደነድነዋል።

19ከእናንተ አንዱ፣ “ታዲያ እንደዚህ ከሆነ እግዚአብሔር እስከ አሁን ለምን ይወቅሠናል? ምክንያቱም ፈቃዱን ሊቋቋም የሚችል ማን አለ?” ይለኝ ይሆናል። 20ነገር ግን ለእግዚአብሔር መልስ የምትሰጥ አንተ ማን ነህ? “ሥራ ሠሪውን፣ ‘ለምን እንዲህ ሠራኸኝ?’ ይለዋልን?” 21ሸክላ ሠሪ፣ ከሚሠራው ጭቃ፣ አንዳንዱን ሸክላ ለክብር፣ ሌላውን ደግሞ ለተራ አገልግሎት የማድረግ መብት የለውምን?

22እግዚአብሔር ቍጣውን ለማሳየት፣ ኀይሉንም ለማሳወቅ ፈልጎ የቍጣው መግለጫ የሆኑትን፣ ለጥፋትም የተዘጋጁትን እጅግ ታግሦ ቢሆንሳ! 23አስቀድሞ ለክብር ላዘጋጃቸው፣ የምሕረቱም መግለጫዎች ለሆኑት፣ የክብሩ ባለጠግነት እንዲታወቅ ይህን አድርጎ እንደሆነስ? 24የጠራው ከአይሁድ ወገን ብቻ ሳይሆን ከአሕዛብ ወገን የሆንነውን እኛን እንኳ ሳይቀር አይደለምን? 25በሆሴዕ እንዲህ እንደሚል፤

“ሕዝቤ ያልሆኑትን፣ ‘ሕዝቤ’ ብዬ እጠራቸዋለሁ”፤

“ያልተወደደችውንም ‘የተወደደችው’ ብዬ እጠራለሁ።”

26ደግሞም፣

“ ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’፤

ተብሎ በተነገራቸው በዚያ ቦታ፣

‘የሕያው እግዚአብሔር ልጆች’ ተብለው ይጠራሉ።”

27ኢሳይያስም ስለ እስራኤል እንዲህ ሲል ይጮኻል፤

“የእስራኤል ልጆች ቍጥር በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ቢሆንም፣

ትሩፉ ብቻ ይድናል።

28ጌታ ፍርዱን በምድር ላይ፣

በፍጥነትና ለመጨረሻ ጊዜ ይፈጽማልና።”

29ይኸውም ቀደም ሲል ኢሳይያስ እንደ ተናገረው ነው፤

“የሰራዊት ጌታ፣

ዘር ባያስቀርልን ኖሮ፣

እንደ ሰዶም በሆን ነበር፤

ገሞራንም በመሰልን ነበር።”

የእስራኤል አለማመን

30እንግዲህ ምን እንበል? በእምነት የሆነውን ጽድቅ፣ ለጽድቅ ያልደከሙት አሕዛብ አገኙት፤ 31ነገር ግን የጽድቅን ሕግ የተከታተሉት እስራኤል አላገኙትም። 32ይህ ለምን ሆነ? በእምነት ሳይሆን በሥራ እንደ ሆነ አድርገው በመቍጠር ስለ ተከታተሉት ነው፤ እነርሱም፣ “በማሰናከያው ድንጋይ” ተሰናከሉ። 33ይህም፣

“እነሆ፤ ሰዎችን እንዲደናቀፉ የሚያደርግ ድንጋይ፣

እንዲወድቁ የሚያደርግ ዐለት፣

በጽዮን ላይ አስቀምጣለሁ፤ በእርሱም የሚያምን አያፍርም”

ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

罗马书 9:1-33

上帝的选民

1我在基督里说真话,绝无谎言。我被圣灵感动的良心可以作证, 2我心里极为忧愁,痛苦不止! 3为了我的弟兄——我的同胞以色列人,即使我自己被咒诅、与基督隔绝,我也愿意! 4身为以色列人,他们拥有上帝儿子的名分、上帝的荣耀、诸约、律法、圣殿敬拜和各种应许。 5蒙拣选的族长是他们的先祖,基督降世为人也是做以色列人。祂是至大至尊,永远当受称颂的上帝。阿们!

6当然,这并不表示上帝的话落了空,因为从以色列生的,不一定都是以色列人, 7亚伯拉罕的后裔不一定都是亚伯拉罕的儿女,圣经上说:“以撒生的才可算为你的后裔。” 8这话的意思是:亚伯拉罕凭血气所生的儿女并不是上帝的儿女,只有凭应许所生的才算是他的后裔。 9因为上帝曾这样应许他:“明年这时候,我会再来,撒拉必生一个儿子。”

10后来,利百加和我们的先祖以撒结婚,怀了双胞胎。 11在这对孩子还未出生,还没有显出谁善谁恶之前,上帝为了显明自己拣选人并不是按人的行为,而是按祂自己的旨意, 12便对利百加说:“将来大的要服侍小的。” 13正如圣经上说:“我爱雅各,厌恶以扫。”

14这样看来,我们该怎么下结论呢?难道上帝不公平吗?当然不是! 15祂曾对摩西说:

“我要怜悯谁就怜悯谁,

要恩待谁就恩待谁。”

16可见这并不在于人的意志和努力,而在于祂的怜悯。 17圣经记载着上帝对法老说的话:“我使你兴起是为了在你身上彰显我的权能,使我的名传遍天下。” 18总之,上帝要怜悯谁,就怜悯谁;要叫谁顽固,就叫谁顽固。

上帝的烈怒和怜悯

19这样,你肯定会对我说:“为什么上帝还指责人呢?谁能抗拒祂的旨意呢?” 20你这个人啊!你是谁啊?竟敢顶撞上帝!受造之物怎能对造物主说:“你为什么把我造成这样?” 21陶匠难道不可以从一团泥中拿一部分造贵重的器皿,又拿一部分造平凡的器皿吗?

22倘若上帝要显示祂的烈怒和权能,就尽量容忍那些祂预备要毁灭的器皿, 23以便在那些祂怜悯并预备赐予荣耀的器皿上彰显祂丰盛的荣耀,这难道不可以吗? 24那些蒙怜悯的器皿就是我们这些从犹太人和外族人中被上帝呼召的人。 25正如上帝在《何西阿书》上说:

“本来不是我子民的,

我要称他们为‘我的子民’;

本来不是我所爱的,

我要称他们为‘我所爱的’。

26从前我在什么地方对他们说,

‘你们不是我的子民。’

将来也要在那里对他们说,

‘你们是永活上帝的儿女。’”

27关于以色列人,以赛亚先知曾疾呼:

以色列人虽多如海沙,

但得救的只是剩余的人,

28因为上帝要在世上迅速、

彻底地执行祂的判决。”

29以赛亚又说:

“若不是万军之主给我们存留后裔,

我们早就像所多玛蛾摩拉一样灭亡了。”

以色列人和福音

30这样看来,我们该说什么呢?本来不追求义的外族人却因信而得到了义。 31以色列人靠遵行律法追求义,却徒劳无功。 32为什么会这样呢?因为他们不凭信心,只靠自己的行为去追求义,结果就在那块“绊脚石”上跌倒了。 33正如圣经上说:

“看啊!我在锡安放了一块绊脚石,

一块使人跌倒的磐石。

但信靠祂的人必不致蒙羞。”