1 ቆሮንቶስ 1 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ቆሮንቶስ 1:1-31

1በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ እንዲሆን ከተጠራው ከጳውሎስ፣ ከወንድማችንም ከሶስቴንስ፤

2በቆሮንቶስ ላለችው የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ተቀድሰው፣ የእነርሱና የእኛ ጌታ የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ሆነው ከሚጠሩት ሁሉ ጋር ቅዱሳን ለመሆን ለተጠሩት፤

3ከእግዚአብሔር ከአባታችን፣ ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

ምስጋና

4በክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ተሰጣችሁ ጸጋ ዘወትር ስለ እናንተ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 5ምክንያቱም በማናቸውም ነገር ይኸውም በንግግር ሁሉ፣ በዕውቀትም ሁሉ በእርሱ በልጽጋችኋል፤ 6ስለ ክርስቶስ የመሰከርንላችሁም በእናንተ ዘንድ ጸንቷል። 7ስለዚህ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ በጕጕት በመጠባበቅ ላይ ሳላችሁ፣ ማንኛውም መንፈሳዊ ስጦታ አይጐድልባችሁም። 8በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትገኙ እርሱ እስከ መጨረሻው ድረስ አጽንቶ ይጠብቃችኋል። 9ወደ ልጁ፣ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው።

በቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተከሠተ መለያየት

10ወንድሞች ሆይ፤ በመካከላችሁ መለያየት እንዳይኖር፣ አንድ ልብ፣ አንድ ሐሳብ እንዲኖራችሁ፣ እርስ በርሳችሁም እንድትስማሙ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። 11ወንድሞች ሆይ፤ በመካከላችሁ ክርክር እንዳለ ከቀሎዔ ቤተ ሰብ ሰምቻለሁ፤ 12ነገሩም እንዲህ ነው፤ ከእናንተ አንዱ፣ “እኔ የጳውሎስ ነኝ” ሲል፣ ሌላው፣ “እኔ የአጵሎስ ነኝ” ይላል፤ ደግሞም አንዱ፣ “እኔ የኬፋ1፥12 ጴጥሮስ ማለት ነው ነኝ” ሲል፣ ሌላው ደግሞ፣ “እኔስ የክርስቶስ ነኝ” ይላል።

13ለመሆኑ ክርስቶስ ተከፍሏልን? ጳውሎስስ ለእናንተ ተሰቅሏልን? ወይስ በጳውሎስ1፥13 ወይም ወደ ጳውሎስ፤ እንዲሁም 15 ይመ ስም ተጠምቃችኋልን? 14ከቀርስጶስና ከጋይዮስ በስተቀር ከእናንተ ማንንም ስላላጠመቅሁ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ 15ስለዚህ በስሜ መጠመቁን የሚናገር ማንም የለም። 16በርግጥ የእስጢፋኖስንም ቤተ ሰው አጥምቄአለሁ፤ ከእነዚህ ሌላ ግን ማጥመቄ ትዝ አይለኝም። 17ክርስቶስ የላከኝ ወንጌልን እንድሰብክ እንጂ እንዳጠምቅ አይደለም፤ የክርስቶስም መስቀል ከንቱ እንዳይሆን፣ በሰዎች የንግግር ጥበብ አልሰብክም።

ክርስቶስ የእግዚአብሔር ኀይልና ጥበብ

18የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉ ሞኝነት ነው፤ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ 19እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና፤

“የጥበበኞችን ጥበብ አጠፋለሁ፤

የዐዋቂዎችንም ዕውቀት ከንቱ አደርጋለሁ።”

20ጠቢብ የት አለ? ሊቅስ የት አለ? የዘመኑስ ፈላስፋ የት አለ? እግዚአብሔር የዓለምን ጥበብ ሞኝነት አላደረገምን? 21ከእግዚአብሔር ጥበብ የተነሣ ዓለም በገዛ ጥበቧ እግዚአብሔርን ማወቅ ስለ ተሳናት፣ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ያድን ዘንድ የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኗል። 22መቼም አይሁድ ታምራዊ ምልክትን ይፈልጋሉ፤ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፤ 23እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ መሰናክል፣ ለአሕዛብ ደግሞ ሞኝነት ነው። 24እግዚአብሔር ለጠራቸው ግን፣ አይሁድም ሆኑ ግሪኮች፣ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ኀይል፣ የእግዚአብሔርም ጥበብ ነው። 25ምክንያቱም ከሰው ጥበብ ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባል፤ ከሰውም ብርታት ይልቅ የእግዚአብሔር ድካም ይበረታል።

26ወንድሞች ሆይ፤ በተጠራችሁ ጊዜ ምን እንደ ነበራችሁ እስቲ አስቡ። በሰው መስፈርት ከእናንተ ብዙዎቻችሁ ዐዋቂዎች አልነበራችሁም፤ ብዙዎቻችሁም ኀያላን አልነበራችሁም፤ ብዙዎቻችሁም ከትልቅ ቤተ ሰብ አልተወለዳችሁም። 27ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን ያሳፍር ዘንድ የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ እግዚአብሔር ብርቱዎችን ያሳፍር ዘንድ የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ። 28እግዚአብሔር የተከበረውን እንደሌለ ለማድረግ፣ በዚህ ዓለም ዝቅ ያለውንና የተናቀውን ነገር፣ ቦታም ያልተሰጠውን ነገር መረጠ፤ 29ይኸውም ማንም ሰው በእርሱ ፊት እንዳይመካ ነው። 30በክርስቶስ ኢየሱስ ለመሆን የበቃችሁት ከእርሱ የተነሣ ነው፤ እርሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበባችን፣ ጽድቃችንና ቅድስናችን፣ ቤዛችንም ሆኗል። 31እንግዲህ፣ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው፤ “የሚመካ በጌታ ይመካ።”

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

哥林多前书 1:1-31

问候

1我是按上帝旨意蒙召做基督耶稣使徒的保罗,同所提尼弟兄, 2写信给在哥林多的上帝的教会,就是在基督耶稣里得以圣洁、蒙召做圣徒的,以及各地求告我们主耶稣基督之名的人。基督是他们的主,也是我们的主。

3愿我们的父上帝和主耶稣基督赐给你们恩典和平安!

保罗的感恩

4我常常为你们感谢我的上帝,因为祂在基督耶稣里赐给了你们恩典, 5使你们在基督里凡事富足,有全备的口才和知识。 6这样,我为基督所做的见证就在你们身上得到了证实。 7因此,你们在殷切等候我们主耶稣基督再来的期间,并不缺少任何属灵的恩赐。 8我们的主耶稣基督必扶持你们到底,使你们在祂再来的日子无可指责。 9上帝是信实的,祂呼召你们是要你们与祂的儿子——我们的主耶稣基督相交。

信徒要同心合意

10亲爱的弟兄姊妹,我奉主耶稣基督的名劝你们,要同心合意,不可结党纷争,要团结一致, 11因为革来家的人把各位弟兄姊妹的事情告诉了我,说你们中间有纷争。 12我的意思是你们有人说:“我是跟随保罗的”,有人说:“我是跟随亚波罗的”,有人说:“我是跟随彼得的”,有人说:“我是跟随基督的”。 13难道基督是分成几派的吗?替你们钉十字架的是保罗吗?你们是奉保罗的名受洗的吗?

14感谢上帝,除了基利司布该犹以外,我没有为你们任何人施洗, 15所以没有人能说是奉我的名受洗的。 16不错,我也曾为司提法纳的家人施洗,除此以外,我不记得还为谁施洗了。 17基督不是差遣我去为人施洗,而是去传扬福音,而且不用高言大智,免得基督十字架的能力被抹杀。

上帝的智慧

18因为十字架之道在将要灭亡的人看来是愚昧的,但对我们这些得救的人来说却是上帝的大能, 19正如圣经上说:“我要摧毁智者的智慧,废弃明哲的聪明。”

20这个世代所谓的智者、学者、雄辩家在哪里?上帝岂不是把这世上的智慧都变成愚昧了吗? 21上帝运用自己的智慧不让世人凭自己的智慧去认识祂,祂乐意采用世人看为愚昧的道理去拯救那些相信的人,这就是上帝的智慧。

22犹太人要看神迹,希腊人寻求智慧, 23但我们传讲被钉十字架的基督。这对犹太人来说是绊脚石,对外族人来说是愚昧的。 24但对于蒙召的人,无论是犹太人还是希腊人,基督是上帝的能力、上帝的智慧。 25因为上帝的“愚昧”也胜过世人的智慧,上帝的“软弱”也胜过世人的刚强。

26弟兄姊妹,想想你们蒙召时的情形。按人的标准来衡量,你们当中称得上有智慧的不多,有能力的不多,出身名门望族的也不多。 27但上帝拣选了世人看为愚昧的,要使智者羞愧;上帝拣选了世上软弱的,要使强者蒙羞; 28上帝拣选了世上卑贱的、被藐视的和无足轻重的,要使世人看为举足轻重的变得无足轻重。 29这样,谁都不能在上帝面前自夸了。

30上帝使你们活在基督耶稣里,祂使基督耶稣成为我们的智慧、公义、圣洁和救赎。 31所以,正如圣经上说:“要夸耀,就当夸耀主的作为。”