ሮሜ 14 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሮሜ 14:1-23

በወንድምህ ላይ አትፍረድ

1በእምነቱ ደካማ የሆነውን ሰው፣ አከራካሪ በሆኑ ጕዳዮች ላይ በአቋሙ ሳትፈርዱበት ተቀበሉት። 2የአንድ ሰው እምነቱ ማንኛውንም ነገር እንዲበላ ይፈቅድለታል፤ በእምነቱ ያልጠነከረው ሌላው ሰው ግን አትክልት ብቻ ይበላል። 3ማንኛውንም የሚበላ የማይበላውን አይናቅ፤ የማይበላውም፣ የሚበላውን አይኰንን፤ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና። 4ሌላውን በሚያገለግል ላይ የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? እርሱ ቢወድቅ ወይም ቢቆም ለጌታው ነው፤ ጌታ ሊያቆመው ስለሚችልም ይቆማል።

5አንድ ሰው አንዱን ቀን ከሌላው የተሻለ ቅዱስ አድርጎ ይቈጥራል፤ ሌላው ደግሞ ቀኖች ሁሉ እኩል እንደ ሆኑ ያስባል። እያንዳንዱ የራሱን ውሳኔ ልብ ብሎ ይወስን። 6አንድን ቀን ከሌላው የተለየ አድርጎ የሚያስብ ሰው፣ እንዲህ የሚያደርገው ለጌታ ብሎ ነው፤ ሥጋ የሚበላውም ለጌታ ብሎ ይበላል፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ያቀርባልና። የማይበላም ለጌታ ሲል አይበላም፤ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ያቀርባል። 7ከእኛ ማንም ለራሱ የሚኖር፣ ለራሱም የሚሞት የለምና። 8ብንኖር ለጌታ እንኖራለን፤ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። ስለዚህ ብንኖርም ብንሞትም የጌታ ነን።

9ለዚሁ፣ የሙታንና የሕያዋን ጌታ ይሆን ዘንድ ክርስቶስ ሞቷል፤ በሕይወትም ተነሥቷል። 10ታዲያ አንተ በወንድምህ ላይ ለምን ትፈርዳለህ? ለምንስ ወንድምህን ትንቃለህ? ሁላችንም በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ፊት እንቀርባለንና፤ 11እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፤

“ ‘እኔ ሕያው ነኝና’፤

‘ጕልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል፤

ምላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር ይመሰክራል’ ”

ይላል ጌታ። 12ስለዚህ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።

13ስለዚህ እርስ በርሳችን፣ አንዱ በሌላው ላይ ከመፍረድ እንቈጠብ፤ በዚህ ፈንታ ግን በወንድምህ መንገድ ላይ የማሰናከያ ድንጋይ ወይም ወጥመድ እንዳታስቀምጥ ቍርጥ ሐሳብ አድርግ። 14በጌታ በኢየሱስ ሆኜ በራሱ ንጹሕ ያልሆነ ምንም ምግብ14፥14 ወይም ምንም ነገር እንደሌለ ተረድቻለሁ፤ ነገር ግን አንድ ሰው አንድን ነገር ንጹሕ እንዳልሆነ የሚቈጥር ከሆነ፣ ያ ነገር ለእርሱ ንጹሕ አይደለም። 15ወንድምህ በምትበላው ምግብ የሚያዝን ከሆነ፣ በፍቅር አልተመላለስህም፤ ክርስቶስ የሞተለትን ወንድምህን በመብልህ አታጥፋው። 16መልካም ነው ብለህ የምታስበው ነገር ክፉ ተብሎ እንዲነቀፍ አታድርግ። 17የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም፣ በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ሐሤት ነው እንጂ፣ የመብልና የመጠጥ ጕዳይ አይደለም፤ 18በዚህ ሁኔታ ክርስቶስን የሚያገለግል እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፤ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው።

19ስለዚህ ሰላም የሚገኝበትንና እርስ በርሳችንም የምንተናነጽበትን ማንኛውንም ጥረት እናድርግ። 20ለምግብ ስትል የእግዚአብሔርን ሥራ አታፍርስ። ሁሉ ንጹሕ ነው፤ ነገር ግን ለሌላው ሰው የመሰናከያ ምክንያት የሚሆነውን መብላት ስሕተት ነው። 21ለወንድምህ መሰናከል ምክንያት የሚሆነውን ሥጋን አለመብላት፣ ወይንን አለመጠጣት፣ ወይም አንዳች ነገርን አለማድረግ መልካም ነው።

22እንግዲያስ ስለ እነዚህ ነገሮች ያለህ እምነት በአንተና በእግዚአብሔር መካከል የተጠበቀ ይሁን፤ ትክክል ነው ብሎ በተቀበለው ነገር ራሱን የማይኰንን የተባረከ ሰው ነው። 23ነገር ግን የሚጠራጠር ሰው ቢበላ በእምነት ስላልሆነ፣ ተፈርዶበታል፤ በእምነት ያልተደረገ ሁሉ ኀጢአት ነውና።

Knijga O Kristu

Rimljanima 14:1-23

Prigrlite slaboga u vjeri

1Prigrlite slaboga u vjeri i ne osuđujte ga zbog različitog mišljenja. 2Netko, primjerice, vjeruje da se smije jesti sve. Ali drugi će vjernik, osjetljive savjesti, jesti samo povrće. 3Oni koji smatraju da se smije jesti sve ne smiju svisoka gledati na one druge. A oni koji ne jedu neke vrste hrane ne smiju osuđivati one koji jedu jer je njih Bog prigrlio. 4Tko si ti da osuđuješ tuđega slugu? On je odgovoran svojemu gospodaru, koji mu jedini može reći što smije, a što ne. I Gospodin će mu pomoći da čini kako valja.

5Slično tomu, neki ljudi smatraju neke dane svetijima od drugih, dok drugi sve dane drže jednakima. O tomu svatko treba imati svoje uvjerenje. 6Koji imaju poseban dan za bogoslužje, iskazuju čast Gospodinu. Koji jedu sve vrste hrane, čine tako da bi iskazali čast Gospodinu jer zahvaljuju Bogu prije jela. A oni koji ne jedu sve, također žele ugoditi Gospodinu i također zahvaljuju Bogu. 7Nismo mi sebi gospodarima ni dok živimo ni kad umiremo. 8Dok živimo, živimo za Gospodina, a kad umiremo, umiremo za Gospodina. Zato i u životu i u smrti pripadamo Gospodinu. 9Krist je umro i uskrsnuo upravo zato—da bude Gospodin i živima i mrtvima.

10Zašto osuđuješ svojeg brata? Ili zašto prezireš svojeg brata? Ta svi ćemo stati pred Božji sud 11jer u Svetome pismu piše:

“‘Života mi mojega’, kaže Gospodin,

‘svako će se koljeno pognuti preda mnom

i svaki će jezik priznati Boga.’”14:11 Izaija 45:23.

12Svatko od nas će dakle za sebe položiti račun Bogu.

13Nemojmo stoga jedni druge osuđivati, nego živite tako da se braća zbog vas ne spotiču u vjeri. 14Znam i uvjeren sam u Gospodinu Isusu da nikakva hrana po sebi nije nečista. Ali vjeruje li tko da mu što nije dopušteno, onda nije dobro da to čini. 15Ako žalostiš svojega brata time što nešto jedeš, ne postupaš u ljubavi. Ne upropaštavaj zbog hrane onoga za koga je Krist umro 16da te ne pogrđuju što činiš ono za što znaš da je dobro.

17Jer Božje kraljevstvo nije u jelu i pilu, nego u pravednosti, miru i radosti u Svetome Duhu. 18Budete li tako služili Kristu, ugodit ćete Bogu, a i ljudi će vas cijeniti.

19Nastojmo živjeti u slozi i uzajamno se izgrađivati. 20Ne razarajte Božje djelo zbog hrane! Nije ona po sebi nečista, ali je zlo da ju jedete ako to koga tjera na spoticanje u vjeri. 21Dobro je ne jesti meso ili ne piti vino, ili ne činiti bilo što zbog čega bi se tvoj brat mogao spotaknuti. 22Ako si uvjeren da u tome što činiš nema ničega lošega, neka to ostane između tebe i Boga. Blago onomu koji sebe ne osuđuje zbog onoga na što se odlučio. 23Ali jede li tko a da nije siguran čini li grijeh, sam je sebe osudio jer ne postupa prema uvjerenju. Čini li tko ono za što nije siguran je li grijeh, griješi.