ሐዋርያት ሥራ 1 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 1:1-26

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ዐረገ

1ቴዎፍሎስ ሆይ፤ ኢየሱስ ለማድረግና ለማስተማር የጀመረውን ሁሉ ቀደም ባለው መጽሐፌ ጽፌልሃለሁ፤ 2ይኸውም እስከ ዐረገበት ቀን ድረስ ለመረጣቸው ሐዋርያት በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የሰጣቸው ትእዛዝ ነው። 3ከሕማማቱም በኋላ ራሱ ቀርቦ ሕያው መሆኑን፣ ለእነዚሁ በብዙ ማስረጃ እያረጋገጠላቸው አርባ ቀንም ዐልፎ ዐልፎ እየታያቸው ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ነገራቸው። 4ከእነርሱም ጋር በማእድ ተቀምጦ ሳለ እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ “ከኢየሩሳሌም አትውጡ፤ ነገር ግን እኔ ስናገር የሰማችሁትን፣ አብ የሰጠውን ተስፋ ጠብቁ፤ 5ዮሐንስ በውሃ አጥምቆ ነበርና፣ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ።”

6እነርሱም ተሰብስበው ሳሉ፣ “ጌታ ሆይ፤ የእስራኤልን መንግሥት መልሰህ የምታቋቁምበት ጊዜው አሁን ነውን?” ብለው ጠየቁት።

7እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “አብ በገዛ ሥልጣኑ የወሰነውን ጊዜ ወይም ወቅት ማወቁ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ 8ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በሚወርድበት ጊዜ ኀይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳና በሰማርያ ሁሉ፣ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ።”

9ይህን ካለ በኋላ እያዩት ወደ ላይ ዐረገ፤ ደመናም ከዐይናቸው ሰወረችው።

10እርሱም በሚሄድበት ጊዜ ትኵር ብለው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ እነሆ፤ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች ድንገት አጠገባቸው ቆሙ፤ 11እንዲህም አሏቸው፤ “እናንት የገሊላ ሰዎች ሆይ፤ ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ እዚህ የቆማችሁት ለምንድን ነው? ይህ ከእናንተ ዘንድ ወደ ሰማይ ሲያርግ ያያችሁት ኢየሱስ፣ ልክ ወደ ሰማይ ሲወጣ እንዳያችሁት በዚሁ ሁኔታ ይመለሳል።”

ማትያስ በይሁዳ ምትክ ተመረጠ

12ከዚያም ደብረ ዘይት ከተባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፤ ይህም ተራራ ከኢየሩሳሌም የሰንበት መንገድ ያህል1፥12 አንድ ሺሕ አንድ መቶ ሜትር ገደማ ነው። ይርቅ ነበር። 13ወደ ከተማዪቱም በገቡ ጊዜ ወደሚኖሩበት ሰገነት ወጡ፤ እነዚህም ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ፣ ያዕቆብ፣ እንድርያስ፣ ፊልጶስ፣ ቶማስ፣ በርተሎሜዎስ፣ ማቴዎስ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ቀናኢ የተባለው ስምዖንና የያዕቆብ ልጅ ይሁዳ ነበሩ። 14እነዚህ ሁሉ ከሴቶቹና ከኢየሱስ እናት ከማርያም ጋር እንዲሁም ከወንድሞቹ ጋር በአንድ ልብ ሆነው ያለ ማቋረጥ ተግተው ይጸልዩ ነበር።

15በእነዚያም ቀናት፣ ጴጥሮስ መቶ ሃያ በሚሆኑ ወንድሞች1፥15 ወይም አማኞች መካከል ቆሞ፣ 16እንዲህ አለ፤ “ወንድሞች ሆይ፤ ኢየሱስን ለያዙት ሰዎች መሪ ስለ ሆናቸው ስለ ይሁዳ፣ መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ በዳዊት አፍ የተናገረው የመጽሐፉ ቃል መፈጸም ስላለበት፣ 17እርሱ ከእኛ እንደ አንዱ ተቈጥሮ በዚህ አገልግሎት የመሳተፍ ዕድል አግኝቶ ነበር።”

18ይህ ሰው ስለ ክፉ ሥራው በተከፈለው ዋጋ መሬት ገዛ፤ በዚያም በግንባሩ ተደፍቶ ሰውነቱ እመካከሉ ላይ ፈነዳ፤ ሆድ ዕቃውም ተዘረገፈ። 19ይህም በኢየሩሳሌም በሚኖሩት ሁሉ ዘንድ ተሰማ፤ መሬቱም በቋንቋቸው “አኬልዳማ” ተብሎ ተጠራ፤ ትርጓሜውም “የደም መሬት” ማለት ነው።

20ጴጥሮስም በመቀጠል እንዲህ አለ፤

“በመዝሙር መጽሐፍ፣

‘መኖሪያው ባዶ ትሁን፤

የሚኖርባትም ሰው አይገኝ’ ደግሞም፣

‘ሹመቱን ሌላ ሰው ይውሰደው’

ተብሎ ተጽፏል። 21ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ በመካከላችን በገባበትና በወጣበት ጊዜ ሁሉ፣ ከእኛ ጋር ከነበሩት መካከል አንድ ሰው መምረጥ ያስፈልጋል፤ 22ይኸውም፣ ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ኢየሱስ ከእኛ ተለይቶ እስካረገበት ቀን ድረስ የነበረ መሆን አለበት፤ ምክንያቱም ከእነዚህ ሰዎች አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር እንዲሆን ያስፈልጋል።”

23ስለዚህ ኢዮስጦስ የሚሉትን፣ በርስያን የተባለውን ዮሴፍንና ማትያስን ሁለቱን አቀረቡ፤ 24እንዲህም ብለው ጸለዩ፤ “ጌታ ሆይ፤ አንተ የሰውን ሁሉ ልብ ታውቃለህ፤ ከእነዚህ ከሁለቱ መካከል የመረጥኸውን ሰው አመልክተንና 25ይሁዳ ወደ ገዛ ራሱ ስፍራ ትቶት በሄደው በዚህ አገልግሎትና በሐዋርያዊነት ቦታ ላይ ሹመው።” 26ከዚያም ዕጣ ጣሉላቸው፤ ዕጣውም ለማትያስ ወጣ፤ እርሱም ከዐሥራ አንዱ ሐዋርያት ጋር ተቈጠረ።

Knijga O Kristu

Djela Apostolska 1:1-26

Obećanje Svetoga Duha

1Dragi Teofile, u prvoj knjizi koju sam ti napisao iznio sam sve što je Isus počeo da djeluje i poučava 2do dana kad je uznesen na nebo, pošto je odabranim apostolima dao upute Svetoga Duha. 3Još četrdeset dana nakon raspeća ukazivao se apostolima i na mnoge im načine dokazao da je živ. Govorio im je o Božjemu kraljevstvu.

4Dok je tako s njima blagovao, reče im: “Ne idite iz Jeruzalema, nego ostanite ondje dok vam Otac ne pošalje što je obećao. Sjetite se, već sam vam o tomu govorio. 5Ivan je krstio vodom, ali vi ćete uskoro biti kršteni Svetim Duhom.”

Isusovo uzašašće

6Apostoli koji su bili s njim upitaju ga: “Gospodine, hoćeš li sada obnoviti izraelsko kraljevstvo?”

7“Ta vremena i prigode određuje Otac svojom vlasti”, odgovori im on, “i nije na vama da ih znate. 8Ali kad na vas siđe Sveti Duh, primit ćete snagu da o meni svjedočite ljudima posvuda—u Jeruzalemu, po svoj Judeji i Samariji i do kraja zemlje.”

9Tek što je to rekao, uznesen je na nebo pred njihovim očima i nestao u oblaku. 10Dok su očiju uprtih u nebo gledali kako odlazi, odjednom se među njima pojave dvojica ljudi u bijeloj odjeći. 11“Galilejci, što tu stojite i gledate u nebo?” rekli su. “Isus je od vas uznesen na nebo, ali jednoga dana će se vratiti jednako tako kao što ste ga vidjeli da odlazi!”

Umjesto Jude izabran Matija

12Bilo je to na Maslinskoj gori. Vrate se zatim do Jeruzalema udaljenoga otprilike kilometar.1:12 U grčkome: jedan subotni hod. 13Čim uđu u grad, odu u kuću u kojoj su boravili, u sobu na katu. Bili su ondje Petar, Ivan, Jakov, Andrija, Filip, Toma, Bartolomej, Matej, Jakov (Alfejev sin), Šimun (zelot) i Juda (Jakovljev sin).

14Svi su se ustrajno i jednodušno sastajali na molitvu s Isusovom majkom Marijom, još nekoliko drugih žena i s Isusovom braćom.

15Kad ih je jednom tako bilo okupljeno sto dvadeset, Petar ustane i reče:

16“Braćo, moralo se ispuniti ono što piše u Svetome pismu za Judu, koji je doveo hramsku policiju da uhiti Isusa. To je odavno, kroz Davida, pretkazao Sveti Duh.

17Juda je bio jedan od nas, dionik naše službe.

18Novcem koji je dobio za svoje zlodjelo Juda je kupio polje. Ondje je pao i rasprsnuo se tako da mu se prosula sva utroba. 19Vijest o njegovoj smrti brzo se pronijela među stanovnicima Jeruzalema pa su to polje prozvali Akeldama, što na aramejskome znači ‘Krvavo polje’.

20To je pretkazano u Knjizi psalama. Ondje piše:

‘Neka njegov dom opusti,

neka nitko u njemu ne stanuje!’

i

‘Neka njegovu službu dobije drugi!’1:20 Psalam 69:26; Psalam 109:8.

21Moramo zato odabrati nekoga da zamijeni Judu—nekoga tko je bio s nama cijelo vrijeme dok smo bili s Gospodinom Isusom 22otkad ga je Ivan krstio pa do uznesenja u nebo. Taj će s nama biti svjedokom Isusova uskrsnuća.”

23Predlože dvojicu: Josipa Barsabu (kojega su zvali i Just) i Matiju. 24Svi se pomole: “Gospodine, ti poznaješ svako srce. Pokaži nam kojega si od ove dvojice izabrao 25da kao apostol zamijeni izdajnika Judu koji nas je napustio i otišao onamo kamo pripada.” 26Zatim bace kocke i kocka padne na Matiju. Tako je on postao dvanaestim apostolom.