ምሳሌ 29 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 29:1-27

1ከብዙ ተግሣጽ በኋላ ዐንገቱን የሚያደነድን ሰው፣

በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።

2ጻድቃን ሥልጣን ሲይዙ ሕዝብ ሐሤት ያደርጋል፤

ክፉዎች ሲገዙ ግን ሕዝብ ያቃስታል።

3ጥበብን የሚወድድ ሰው አባቱን ደስ ያሰኛል፤

የአመንዝራዎች ወዳጅ ግን ሀብቱን ያባክናል።

4ፍትሕን በማስፈን ንጉሥ አገርን ያረጋጋል፤

ጕቦ ለማግኘት የሚጐመጅ ግን ያፈራርሳታል።

5ባልንጀራውን የሚሸነግል፣

ለገዛ እግሩ መረብ ይዘረጋል።

6ክፉ ሰው በራሱ ኀጢአት ይጠመዳል፤

ጻድቅ ግን ይዘምራል፤ ደስም ይለዋል።

7ጻድቅ ለድኾች ፍትሕ ይጨነቃል፤

ክፉ ሰው ግን ደንታ የለውም።

8ተሳዳቢዎች ከተማን ያውካሉ፤

ጠቢባን ግን ቍጣን ያበርዳሉ።

9ጠቢብ ሰው ከተላላ ጋር ወደ ሸንጎ ቢሄድ፣

ተላላ ይቈጣል፤ ያፌዛል፤ ሰላምም አይኖርም።

10ደም የተጠሙ ሰዎች ሐቀኛን ሰው ይጠላሉ፤

ቅን የሆነውንም ለመግደል ይሻሉ።

11ተላላ ሰው ቍጣውን ያለ ገደብ ይለቅቀዋል፤

ጠቢብ ሰው ግን ራሱን ይቈጣጠራል።

12ገዥ የሐሰት ወሬ የሚሰማ ከሆነ፣

ሹማምቱ ሁሉ ክፉዎች ይሆናሉ።

13ድኻውና ጨቋኙ የጋራ ነገር አላቸው፤

እግዚአብሔር ለሁለቱም የዐይን ብርሃንን ሰጥቷቸዋል።

14ንጉሥ ለድኻ ትክክለኛ ፍርድ ቢሰጥ፣

ዙፋኑ ዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

15የተግሣጽ በትር ጥበብን ታጐናጽፋለች፤

መረን የተለቀቀ ልጅ ግን እናቱን ያሳፍራል።

16ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ኀጢአት ይበዛል፤

ጻድቃን ግን የእነርሱን ውድቀት ያያሉ።

17ልጅህን ቅጣው፤ ሰላም ይሰጥሃል፤

ነፍስህንም ደስ ያሰኛታል።

18ራእይ በሌለበት ሕዝብ መረን ይሆናል፤

ሕግን የሚጠብቅ ግን የተባረከ ነው።

19አገልጋይ በቃል ብቻ ሊታረም አይችልም፤

ቢያስተውለውም እንኳ በጀ አይልም።

20በችኰላ የሚናገርን ሰው ታያለህን?

ከእርሱ ይልቅ ተላላ ተስፋ አለው።

21ሰው አገልጋዩን ከልጅነቱ ጀምሮ ቢያቀማጥል፣

የኋላ ኋላ ሐዘን29፥21 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም። ያገኘዋል።

22ቍጡ ሰው ጠብን ይጭራል፤

ግልፍተኛም ብዙ ኀጢአት ይሠራል።

23ሰውን ትዕቢቱ ያዋርደዋል፤

ትሑት መንፈስ ያለው ግን ክብርን ይጐናጸፋል።

24የሌባ ግብረ አበር የገዛ ራሱ ጠላት ነው፤

የመሐላውን ርግማን እየሰማ ጭጭ ይላል።

25ሰውን መፍራት ወጥመድ ነው፤

በእግዚአብሔር የሚታመን ግን በሰላም ይኖራል።

26ብዙዎች በገዥ ፊት ተደማጭነት ማግኘት ይሻሉ፤

ሰው ፍትሕ የሚያገኘው ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

27ጻድቃን አታላዮችን ይጸየፋሉ፤

ክፉዎችም ቅኖችን ይጠላሉ።

Thai New Contemporary Bible

สุภาษิต 29:1-27

1ผู้ที่ถูกตักเตือนบ่อยๆ แต่ยังทำคอแข็งไม่ฟัง

จะแหลกสลายเกินเยียวยาในชั่วพริบตา

2เมื่อคนชอบธรรมเจริญ ผู้คนก็ชื่นชมยินดี

เมื่อคนชั่วขึ้นปกครอง ผู้คนก็โอดครวญ

3ชายที่รักสติปัญญาทำให้พ่อสุขใจ

แต่คนที่คบหาสมาคมกับหญิงโสเภณีก็จะหมดเนื้อหมดตัว

4กษัตริย์สร้างความมั่นคงให้ชาติด้วยความยุติธรรม

แต่กษัตริย์ที่รับสินบน29:4 หรือให้สินบนก็ทำลายชาติ

5ผู้ที่ประจบสอพลอเพื่อนบ้านของตน

ก็กางข่ายไว้ดักเท้าของตน29:5 หรือของเขา

6คนเลวติดกับเพราะบาปของตน

แต่คนชอบธรรมโห่ร้องยินดี

7คนชอบธรรมใส่ใจในความยุติธรรมเพื่อผู้ยากไร้

แต่คนชั่วไม่แยแส

8คนชอบเยาะเย้ยทำให้บ้านเมืองโกลาหล

แต่คนฉลาดทำให้ความโกลาหลสงบลง

9หากคนฉลาดต้องเผชิญหน้ากับคนโง่ในศาล

คนโง่ก็จะโกรธจนตัวสั่น หัวเราะเย้ยหยัน และไม่มีความสงบสุข

10คนกระหายเลือดเกลียดชังคนสุจริต

และหาทางกำจัดผู้ที่เที่ยงธรรม

11คนโง่เขลาระบายความโกรธเต็มที่

แต่คนฉลาดจะสงบนิ่งได้ในที่สุด

12ถ้าผู้ครอบครองฟังความเท็จ

ข้าราชการทุกคนของเขาจะกลายเป็นคนชั่วไปด้วย

13ผู้ยากไร้และผู้กดขี่ข่มเหงก็เหมือนกันอย่างหนึ่ง

คือองค์พระผู้เป็นเจ้าประทานตาที่แลเห็นให้พวกเขาทั้งคู่

14หากกษัตริย์ให้ความเที่ยงธรรมแก่ผู้ยากไร้

ราชบัลลังก์ก็จะยืนยงเสมอ

15ไม้เรียวและการลงโทษจะให้ปัญญา

แต่เด็กที่ถูกปล่อยปละละเลยจะทำให้แม่อับอายขายหน้า

16เมื่อคนชั่วเจริญ บาปก็ทวีขึ้น

แต่คนชอบธรรมจะเห็นความล่มจมของเหล่าคนชั่ว

17จงอบรมสั่งสอนลูกของเจ้า แล้วเขาจะทำให้เจ้ามีสันติสุข

เขาจะทำให้เจ้าชื่นอกชื่นใจ

18ในที่ซึ่งไม่มีการเผยพระวจนะ สังคมก็โกลาหลวุ่นวาย

แต่ความสุขมีแก่ผู้ที่รักษาบทบัญญัติ

19จะอบรมสั่งสอนคนรับใช้ด้วยคำพูดอย่างเดียวไม่ได้

แม้เขาเข้าใจ เขาก็ไม่ยอมทำตาม

20เจ้าเห็นคนที่พูดพล่อยๆ หรือไม่?

ยังมีความหวังสำหรับคนโง่มากกว่าเขา

21การประคบประหงมคนรับใช้ตั้งแต่เด็ก

เขาจะนำความทุกข์โศกมาให้29:21 หรือเขาจะกลายเป็นลูกหรือเขาจะกลายเป็นผู้รับมรดกในที่สุด

22คนขี้โมโหก่อการวิวาท

และคนเลือดร้อนทำบาปมากมาย

23ความหยิ่งผยองทำให้คนเราตกต่ำ

ส่วนผู้ที่จิตใจถ่อมสุภาพได้รับเกียรติ

24ผู้ที่สมคบกับขโมยก็เป็นศัตรูกับตัวเอง

ต้องสาบานในศาลแต่ไม่กล้าเป็นพยาน

25ความกลัวของคนเป็นเพียงกับดัก

แต่ผู้ที่วางใจในองค์พระผู้เป็นเจ้าก็ปลอดภัย

26หลายคนวิ่งเต้นเข้าหาเจ้านาย

แต่คนเราได้รับความยุติธรรมจากองค์พระผู้เป็นเจ้า

27คนอยุติธรรมชิงชังคนชอบธรรม

แต่คนเที่ยงตรงชิงชังคนชั่ว