ምሳሌ 21 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 21:1-31

1የንጉሥ ልብ በእግዚአብሔር እጅ ነው፤

እርሱም እንደ ቦይ ውሃ ደስ ወዳሰኘው ይመራዋል።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ቀና ይመስለዋል፤

እግዚአብሔር ግን ልብን ይመዝናል።

3ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ፣

በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው።

4ትዕቢተኛ ዐይን፣ እብሪተኛ ልብ፣

የክፉዎችም መብራት ኀጢአት ናቸው።

5የትጉህ ሰው ዕቅድ ወደ ትርፍ ያመራል፤

ችኰላም ወደ ድኽነት ያደርሳል።

6በሐሰተኛ አንደበት የተገኘ ሀብት፣

በንኖ የሚጠፋ ተን፣ ለሞትም የሚያበቃ ወጥመድ ነው።21፥6 አንዳንድ የዕብራይስጥ ጽሑፎች፣ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጕሞች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አያሌ የዕብራይስጥ ጽሑፎች ግን ሞትን ለሚሹ በንኖ እንደሚጠፋ ተን ነው ይላሉ።

7ክፉዎችን ዐመፃቸው ይጠራርጋቸዋል፤

ቅን ነገር ማድረግ አይወድዱምና።

8የበደለኛ መንገድ ጠማማ ነው፤

የንጹሕ ሰው ጠባይ ግን ቀና ነው።

9ከጨቅጫቃ ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖር፣

በጣራ ላይ ጥግ ይዞ መኖር ይሻላል።

10ክፉ ሰው ክፋትን አጥብቆ ይመኛል፤

ባልንጀራውም ከእርሱ ዘንድ ርኅራኄን አያገኝም።

11ፌዘኛ ሲቀጣ፣ አላዋቂ ጥበብን ያተርፋል፤

ጠቢብ ሰው ቢማር ዕውቀትን ያገኛል።

12ጻድቁ21፥12 ወይም ጻድቁ ሰው የክፉዎችን ቤት ልብ ብሎ ይመለከታል፤

ክፉዎችንም ያጠፋቸዋል።

13ሰው የድኾችን ጩኸት ላለመስማት ጆሮውን ቢዘጋ፣

እርሱም ይጮኻል፤ መልስም አያገኝም።

14በስውር የተደረገ ስጦታ ቍጣን ያበርዳል፤

በጕያ የተሸሸገ እጅ መንሻም ታላቅ ቍጣን ጸጥ ያደርጋል።

15ፍትሕ ሲሰፍን ጻድቁን ደስ ያሰኘዋል፤

ክፉ አድራጊዎችን ግን ያሸብራል።

16የማስተዋልን መንገድ የሚስት ሰው፣

በሙታን ጉባኤ ያርፋል።

17ቅንጦትን የሚወድድ ይደኸያል፤

የወይን ጠጅና ዘይት የሚወድድም ባለጠጋ አይሆንም።

18ክፉ ሰው ለጻድቅ፣

ወስላታም ለቅን ሰው ወጆ ይሆናል።

19ከጨቅጫቃና ከቍጡ ሚስት ጋር ከመኖር፣

በምድረ በዳ መኖር ይሻላል።

20በጠቢብ ቤት ምርጥ ምግብና ዘይት ተከማችቶ ይገኛል፤

ተላላ ሰው ግን ያለ የሌለውን ያሟጥጣል።

21ጽድቅንና ፍቅርን የሚከተል፤

ሕይወትን ብልጽግናንና21፥21 ወይም ጽድቅን ክብርን ያገኛል።

22ጠቢብ የኀያላንን ከተማ ቅጥር ጥሶ ይገባል፤

መታመኛ ምሽጋቸውንም ያፈርሳል።

23አንደበቱንና ምላሱን የሚቈጣጠር፣

ራሱን ከመቅሠፍት ይጠብቃል።

24ትዕቢተኛና ኵሩ ሰው “ፌዘኛ” ይባላል፤

በጠባዩም እብሪተኛ ነው።

25ታካችን የሚገድለው ምኞቱ ነው፤

እጆቹ መሥራት አይፈልጉምና።

26ክፉ ሰው ቀኑን ሙሉ ይመኛል፤

ጻድቅ ግን አንዳች ሳያስቀር ይሰጣል።

27የክፉ ሰው መሥዋዕት አስጸያፊ ነው፤

በክፉ ዐላማ ሲያቀርብማ የቱን ያህል አስከፊ ይሆን!

28ሐሰተኛ ምስክር ይጠፋል፤21፥28 ወይም የታዛዥ ሰው ቃል ግን ጸንቶ ይኖራል

እውነቱን የሚናገር ግን ጸንቶ ይኖራል።

29ክፉ ሰው በዐጕል ድፍረት ይቀርባል፤

ቅን ሰው ግን አደራረጉን ያስተውላል።

30እግዚአብሔርን ለመቋቋም የሚያስችል፣

አንዳችም ጥበብ፣ ማስተዋልና ዕቅድ የለም።

31ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤

ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Ketab El Hayat

الأمثال 21:1-31

1قَلْبُ الْمَلِكِ فِي يَدِ الرَّبِّ كَجَدَاوِلِ مِيَاهٍ يُمِيلُهُ حَيْثُمَا شَاءَ. 2جَمِيعُ تَصَرُّفَاتِ الإِنْسَانِ تَبْدُو نَقِيَّةً فِي عَيْنَيْ نَفْسِهِ، وَلَكِنَّ الرَّبَّ مُطَّلِعٌ عَلَى حَوَافِزِ الْقُلُوبِ. 3إِجْرَاءُ الْعَدْلِ وَالْحَقِّ أَكْثَرُ قُبُولاً عِنْدَ الرَّبِّ مِنَ الذَّبِيحَةِ. 4تَشَامُخُ الْعَيْنَيْنِ مِنْ غَطْرَسَةِ الْقَلْبِ، وَسِرَاجُ الأَشْرَارِ خَطِيئَةٌ. 5خُطَطُ الْمُجْتَهِدِ تُفْضِي حَتْماً إِلَى الْخِصْبِ، وَالْعَجُولُ مَصِيرُهُ الْعَوَزُ. 6ادِّخَارُ الْكُنُوزِ بِلِسَانٍ مُنَافِقٍ، دُخَانٌ مَتَلاشٍ وَفَخٌّ مُمِيتٌ. 7جَوْرُ الأَشْرَارِ يَجْرُفُهُمْ لِرَفْضِهِمْ إِجْرَاءَ الْعَدْلِ. 8طَرِيقُ الْمُذْنِبِ مُعَوَّجَةٌ، أَمَّا تَصَرُّفُ الزَّكِيِّ فَقَوِيمٌ. 9الإِقَامَةُ فِي رُكْنِ سَطْحٍ خَيْرٌ مِنْ مُشَاطَرَةِ بَيْتٍ مَعَ زَوْجَةٍ نَكِدَةٍ. 10نَفْسُ الْمُنَافِقِ تَشْتَهِي الشَّرَّ، وَقَرِيبُهُ لَا يَحْظَى بِرِضَاهُ. 11إِذَا عُوقِبَ الْمُسْتَهْزِئُ صَارَ الْجَاهِلُ حَكِيماً، وَإِنْ أُرْشِدَ الْحَكِيمُ اكْتَسَبَ مَعْرِفَةً.

12يَتَأَمَّلُ الصِّدِّيقُ فِي بَيْتِ الشِّرِّيرِ، (فَيَرَاهُ) يُلْقَى بِهِ إِلَى الْبَلايَا.

كنوز الحكيم

13مَنْ أَصَمَّ أُذُنَهُ عَنْ صُرَاخِ الْمِسْكِينِ، يَصْرُخُ هُوَ أَيْضاً وَلا مِنْ مُجِيبٍ. 14الْهَدِيَّةُ فِي الْخَفَاءِ تُخْمِدُ الْغَضَبَ، وَالرِّشْوَةُ فِي الْحِضْنِ تُسَكِّنُ السَّخَطَ. 15الْحُكْمُ بِالْعَدْلِ فَرَحٌ لِلصِّدِّيقِ، وَرُعْبٌ لِفَاعِلِي الإِثْمِ. 16الرَّجُلُ الشَّارِدُ عَنْ طَرِيقِ الْمَعْرِفَةِ يَسْكُنُ بَيْنَ جَمَاعَةِ الْمَوْتَى. 17عَاشِقُ اللَّذَّةِ فَقِيرٌ، وَالْمُوْلَعُ بِالْخَمْرِ وَالطِّيبِ لَا يَغْتَنِي. 18الشِّرِّيرُ فِدَاءٌ عَنِ الصِّدِّيقِ، وَالْغَادِرُ عَنِ الْمُسْتَقِيمِينَ. 19الإِقَامَةُ فِي أَرْضٍ مُقْفِرَةٍ خَيْرٌ مِنَ السُّكْنَى مَعَ امْرَأَةٍ مُشَاكِسَةٍ شَرِسَةٍ. 20فِي بَيْتِ الْحَكِيمِ كُنُوزٌ وَزَيْتٌ مُدَّخَرَةٌ، أَمَّا الإِنْسَانُ الْجَاهِلُ فَيُتْلِفُ مَا لَدَيْهِ. 21مَنِ اتَّبَعَ الْعَدْلَ وَالرَّحْمَةَ يَلْقَى الْحَيَاةَ وَالْحَقَّ وَالْمَجْدَ. 22الْحَكِيمُ يَتَسَلَّقُ سُورَ مَدِينَةِ الْجَبَابِرَةِ وَيُدَمِّرُ مَعْقِلَ اعْتِمَادِهِمْ 23مَنْ يَصُونُ فَمَهُ وَلِسَانَهُ عَنِ اللَّغْوِ يَحْفَظُ نَفْسَهُ مِنَ الْمَتَاعِبِ. 24الْمُتَشَامِخُ الْمُنْتَفِخُ يُدْعَى الْمُسْتَهْزِئَ لأَنَّهُ يَتَصَرَّفُ بِغُرُورِ الْكِبْرِيَاءِ. 25أَوْهَامُ الْكَسُولِ تَقْتُلُهُ لأَنَّ يَدَيْهِ تَأْبَيَانِ الْعَمَلَ. 26يَظَلُّ طَوَالَ النَّهَارِ مُتَشَهِّياً مُتَمَنِّياً، أَمَّا الصِّدِّيقُ فَيَسْخُو وَلا يَضِنُّ 27ذَبِيحَةُ الشِّرِّيرِ رِجْسٌ عِنْدَ الرَّبِّ، فَكَمْ بِالْحَرِيِّ إِنْ قَرَّبَهَا بِنِيَّةٍ أَثِيمَةٍ؟ 28شَاهِدُ الزُّورِ يَهْلِكُ، أَمَّا أَقْوَالُ الرَّجُلِ الْحَرِيصِ عَلَى الاسْتِمَاعِ فَتَدُومُ. 29الرَّجُلُ الشِّرِّيرُ يُغْلِظُ وَجْهَهُ، أَمَّا الْمُسْتَقِيمُ فَيَعْمَلُ عَلَى تَقْوِيمِ طُرُقِهِ. 30لَيْسَ مِنْ حِكْمَةٍ، وَلا مِنْ مَشُورَةٍ، وَلا مِنْ فِطْنَةٍ بِقَادِرَةٍ عَلَى مُقَاوَمَةِ اللهِ. 31مَعَ أَنَّ الْفَرَسَ مُعَدٌّ لِيَوْمِ الْقِتَالِ، فَإِنَّ النَّصْرَ هُوَ مِنْ عِنْدِ اللهِ.